~በ~

                                 

         [1]-ኹለተኛ ፊደል፤ በግእዝ አልፍ ቤት በአበገደ ስሙ ቤት ጥሩ ኹለት አኃዝ ኾን ክልኤት ይባላል ዕብራውያን ግን ኹለትን መደብ አድርገው ራሱ ነቍጣ እየጨመሩ ኹለት እልፍ ይሉታል። ኹለተኛ ማለት ምስጢሩ ሰኞንና የሰኞን ፍጥረት መደብ አድርጎ ኹለተኛውን አካል ወልድን ያሳያል -(ዘፍ፩ -)

[2]-(ደቂቅ አገባብ) በቁም ቀሪ ማድረጊያ ጋራ ቸልታ ጊዜ ወደ እንደ ስለ ይኾናል። ማድረጊያ ሲኾን በኹሉ ይገባል፤ የቀረውን ባገባብ ተመልከት -(ር፳፩ ፻፱)

በሓ ባሕ -(ዐረ በኅ አይዞኽ) የሰላምታ የቡራኬ ቃል ፍሥሓ ሰላም። እንዴት ዋልኽ እንዴት አደርኽ ጤና ይስጥኽ ደስታ ላም ላን ይኹን፤ ጠላትኽን ያውድቅ ቢሰኛኽን ያርቅ ማለት ነው በሓከ በሓክሙ ክን እያለ በቅርብ በቅርቦች ይዘረዝራል ኢትበሎ ወአመ ይቤለከ በሓ በሓ በልዋ ተሳለምዋ ሓሂ ትበልዎ ባሕ ርማ ትበልዎሙ ባሕ -(፬ነገ - -፳፱ ድጓ። ፪ዮሐ -፲። ሄርማ፩ -፪። ቀሌ) በሓከ ባሮክ ባሕከ ሄርማ በሓኪ ማርያም በሓክሙ በው ቅዱሳን ባሕክን በሓክን -(ራእ - ሄርማ -ገ፳፩። ደራሲ ማቴ፳፰ -)

በሃሊ -(ሊት ልያን ያት በሀልት) ያለ የሚል የሚናገር፤ ባይ ተናጋሪ፤ አልኹ ባይ እንዲሉ። ከመ ይኩን በሃሌ ብዐልኩ ብራምሀ ኦሆ በሃሊ ወእመሰ ይቤ በሃሊ በሀልተ ጽድቅ -(ኩፋ -፲፫ ያዕ፫ -፲፯ አፈ -ተ፳፮ አዋል)

በሃም -(ምት ማን ማት) ድዳ መናገር የማይችል ድምጥ ቀር ፍሬ ቃል የማይሰጥ ኮነ ጽሙመ ወበሃመ ምአውሥኦትክሙ ትከውን ንከ በሃመ ወከመ በሃም ዘኢይከሥት ፉሁ። በሃማን ኮኖሙ ቃለ -(ግንዘ ሕዝ፳፬ -፳፯። መዝ -፴፯ ኪዳ)

በሐተ -(ዋሐደ ዐረ በሑተ ጥሩ ኾነ) ገባ ተሾመ ተዠመረ ተቈጠረ የወር ያመት ብቸኛ ኾነ ሰው ተለየ ተነጠ እንደ መባቻ ቀን አንድ ተባለ። መጽሐፍ ግን በበሐተ ፈንታ ባሕተወ ይላል።

በሀነ -(ይብህን ይብሀን ብሂን። ዕብ ባሐን ፈተነ) ነነ አለ የዶቄት ያመድ የትቢያ

በሐኵ -በሐዂ፤ -( አባሐዂ፤ አብሓ) የበግ የፍየል ተባት አውራ ርማ የሚታዘል የሚንጠለጠል። በሐ እን ይሜብል ላዕለ መርዔት። በሐኵ ወዳቤላ። ዳቤላት ወአባሕኵ አባሕኩ ባግዕ ባሕኵ ዘአባግ ወዘአጣሊ -(ምላ፳፬ -፷፮። ሕዝ፴፬ -፲፯ ፴፱ -፲፰። መዝ -፷፬። ዘፀ፴፩ - -፲፪ -፴፭)

በሕቁ [1]-በጅጉ በጥቂቱሐቂቅ ሐቀ ሐቀቀ ሕቅ።

 [2]-በጥቂቱ፤ በጅጉ ባያሌው።

በኍበኈ -(ብሕአ) ኽቦኸ ቦነቸ በሰበሰ ተበላሸ ነቀዘ ነጠነ ተላ ገማ ረፋ በሸቀጠ የንጨት የግንድ የገላ የቍስል። በኍበኈ ጋየ በዕፄያት በቍስለ ጢአት ሥጋየ በኍበኈ ወጼአ -(ኢዮ፯ - ስንክ -ነሐ፳፩) ይበልዕ ይትከዐው በማለት ፈንታ ይበኈብኍ ይላል ስሕተት ነው -(ኢዮ፲፰ -፲፫። ሕዝ፯ -፲፯ ፳፩ -)

በሕብሐ -በሕብሐ -(ዕብ ቃራጽ ቀረጸ) ሣለ መሰለ፤ ዐነጠ ቀረጠ፤ ሠራ ፈጠረ የቡሖ የጭቃ የዳቦ የብስኵት የሠምዕ የልሕኵት

በለሳን -(ዐረ በልሳን ዕብ ባሳም ጽር ሚራ። ሮማይ ባልሳኑም) የሽቱ ዕንጨት በይሁዳና በገሊላ ይልቁንም ኢያሪሖ የሚበቅል ዕፀወ ዕጣን አንዱ መዠመሪያው ሽታው ከሽቱ ንጨት ኹሉ የሚበልጥ ጳጳሳት ቅብዐ ቅዱስ ሜሮን የሚያደርጉት። ዝንቱ በለሳን ዘተከልናሁ ይነብር ዝየ ስከ ዓለም ቅብዐ በለሳን በእንተ በለሳን ወዕጣን። ተኀትመ በቅብዐ በለሳን። በለሳነ ኮነ ሀፈ ሥጋሁ በቍሎ -(ስንክ -ግን፳፬ ዲድ -፲፯ ቅዳ ግንዘ ሕዝ፳፯ -፲፯ ደራሲ)

በለስ -( በለሳት አብላስ ዐረ በለስ ዕብ ባላስ) ቁሙ የተክል ንጨት ስም ወይን ጋራ የሚተከል የሾላ ወገን ወተታም ዕንጨቱም ፍሬውም በለስ ይባላል ዘተከለ በለሰ ይበልዕ ፍሬሃ ምበለስ እምሩ ምሳሊሁ። በለስ እምርት ውስተ ዐጸደ ወይን ውያን ወአብላስ ዛፍ -(ምሳ፳፯ -፲፰። ማቴ፳፬ - ሉቃ፲፫ -፮። መጽ -ምስ) ረከቡ ምሥያጥ በለሰ ሐዲሰ ወተሣየጡ ምኔሁ። ረከበ እልኩ በለሳተ ሐዲሳነ ወመልአት ጽፍነታ ጥሕነ ወበለሰ ፍሬ -(ስንክ -ሐም፳፬። ራእ -ባሮ ዮዲ፲ -) በለስ ፍሬ በለስ በኵረ በለስ  በማለት ፈንታ ጽቀ በለስ በለሰ ማእረር ይላል ሕተት ነው -(ኤር፳፬ -) ዳግመኛም በስግላ ፈንቃ በለስ ይላል ሰግላን ተመልከት ዕፀ በለስ ተቃራሜ በለስ ሾላ -(፪ዜና - -፳፯ ዓሞ፯ -፲፬)

በለሶን -ዕፀ አእምሮ የገነት በለስ፤ አዳምና ሔዋን ፍሬውም በልተው ቅጠሉን የለበሱት፤ ኋላም የልደት ለት በታምራት መልአክ አምጥቶላት፤ ዳግሚት ሔዋን ለልጇ ለዳግማይ አዳም ያለበለችው ክደነቶ ጽለ በለሶን -(ድጓ። - ፍ፫ -) -(ሥላሴ ቅኔ) በለሰ ገነት ለአዳም ወሔዋን መቲሮተቶሙ መንክረ ልደት ምላከ መንገሌሆሙ ሰሐበ፤ ወገብርኤልሀ ዜናዌ ቀጸበ። እንተ ከመ  ዝሰ ብር ምከመ ለአዳም ተውህበ ወረከበት ሔዋን ዘኢተረክበ ካዕበ ይስሐብ ቤሆሙ በለስ ይምትርዎ ካዕበ

በለዝ -(ጽር ቦሎዝ ዕብ ቦዐዝ) የዐምድ ስም ሰሎሞን በመቅደሱ ደጅ አፍ በበረንዳው በደጀ ላሙ ካቆማቸው ኹለቱ አዕማድ አንዱ በስተስሜን ያለው የግራው ዐምድ ዕዘዝ ዕዘዝ ይሉ ወጽንዑ ዕዘዙ መቅደስ ማለት ነው ባለብሉዮች ግን ርትዕ ይሉታል -(፫ነገ - ፳፩) .

በለድ -(ትግሬ ወዐረ) የተወለዱበት አገር

()          በሊኅ -(ኃን ኃት ላኅ) የበላ የሰላ የሾለ ስል ሹል ትብ ደፋር ካኝ፤ ፈጣን ብልኀተኛ፤ ጽሩይ ረቂቅ። መላጺ በሊኅ ሰይፍ በሊኅ ቀኖት በሊኅ ያንው በሊኃን ስባራተ ማህውበሊኃት በበሊኅ ልሳን ብእሲ ሊኅ በምግባሩ በሊኅ እገሪሆሙ ክዒወ ደም። በበሊኅ ይነ ልብክን ትነጽራ -(መዝ -፶፩። ራእ፩ -፲፮። ግብ፱ -፭። አርጋ ሢራ፵፫ -፱። ስንክ -መጋ፬ ምሳ፳፪ -፳፱ መዝ - ቄር) በበላኅ ፈንታ ብልኅት ይላል ያሰኝም። ዘሩን መስሎ የሚገኝ ቅጽል ኀጺር ነዊኅ ገዚፍ ጸሊ ቢብ ሐኪም ጸቢብ ርሒብ ረቂቅ ቀጢን ይህን የመሰለ ኹሉ መንገዱ አንድ ነው ብዙዎች በቀር ላንዲቱ ሴት ምእላድ የላትም። ቅጽልነቱም ሣልስና ድስ ያለበት ቱሲ ውስጠ ስለ ኾነ ጻሪ ነዋኂ ገዛፊ ጸላሚ ባቢ ረቃቂ ወይም ንዉኅ ጥቡብ ርቁቅ ቅጡን ያሰኝም። አንዳንድ ጊዜ ግን ሣልስ ትቶ በሳድስ ብቻ፤ ኅጹር ግዙፍ ጽሉም እያለ ይገኛል።

()           በሊኅ ኆት -(በልኀ ይበልኅ ይብላኅ) መብላት፤ መስላት፤ መሾል መፍጠን ስል ሹል ፈጣን መኾን ይበልኅ  እምሰይፍ ይበልኅ  እምሠርት በልኀት ናት -(ዕብ፬ -፲፪ ፈላስ ሕዝጃ፳፩ -፲፩) ይበዝኅ ይጸንዕ በማለት ፈንታ ይበልኅ ይላል -(ዘፀ፲፱ -፲፱)

 -መበለኅ ብልኅ ዋቂ መኾን መባል እገሌ ምላጭ ነው እንዲሉ -(ዐማርኛ)

በሊል ሎት -(በለ ይበልል ይብልል ትግ በለለ። ዕብ ባላል) መብለል ማብለል ማጥፋት ማበላሸት መደባለቅ መዘባረቅ መቀላቀል ማመሳቀል፤ መንከር ማራስ ማርጠብ ማበስበስ ማማሰል መለወስ። በልየና በልበለ የዚህ ዐጽቆች ናቸው።

በሊቅ ቆት -(በለቀ ይበልቅ ይብልቅ ትግ በልቀ ዕብ ባላቅ ለየ ፈለ) መባለቅ ለዘር ብቃት ማደግ መጐልመስ በሕልም ወይም በውን ማፍሰስ ሴት መዳሰስ።

በሊን በሊኖ -(ዕብ ባልናር) ልብሰ ቤተ ምኅፃብ፤ ጠጕራም ፎጣ፤ ታላቅ መንዲል መክፌ ሠርመዲ በሊን ዘፀምር በሊኖ -(አቡሻ -፶። ሲኖዶ)

በሊዕ ዖት -(በልዐ ይበልዕ ይብላዕ። ዕብ ባላዕ። ሱር ብላዕ። ዐረ በሊዐ ዋጠ) መብላት መጕረሥ፤ መንከስ መጋጥ መግመጥ ማላመጥ መዋጥ፤ መሰልቀጥ፤ ምግብን በገዛ እጅ ጪና ተቀባይ መኾን፤ መዝገብ መሰብሰብ ቀበል መክተት የሕያው ፍጥረት አከለን እይ በሊዕ ወሰትይ። ያደዊ ብዝኀ በሊዕ ብላዕ በዐቅም -(መክ፭ -፲፯ ራ፴፯ - ምሳ፳፭ -፲፮)

 -ማቃጠል ማንደድ፤ መፍጀት ማረድ፤ ማጥፋት መጕዳት። በልዐቶሙ ሳት። በልዐቶሙ መጥባሕት።ፈኖከ መዐትከ ወበልዖሙ ብርዕ ቅናአተ ቤትከ በልዐኒ -(ሆሴ፯ -፯። ኤር፪ -፴። ዘፀ፲፭ -፯። መዝ -፷፰)

 -ማማት መንቀፍ መቀማት መዝረፍ በሊዐ ሥጋ ቢጽ በሐሜት በልዕዎ ለእስራኤል። ይበልዑ ጋሆሙ ሕዝብየ -(ቀሌ ኤር፲ -፳፭ ሚክ፫ -)

በላቲ -(ቲት ትያን ያት) የሚበልት በላች በጋማች ሥጋ ቤት ራጅ ባለወግ

በላዒ -(ዒት ያን ያት ላዕት) የሚበላ የሚያቃጥል በላተኛ ሆዳም፤ አጥፊ ዘራፊ ይወድቁ ውስተ በላዒ በላዒተ ሰብእ ንቲ በልባለ እሳት በላዒ። ሥሡዓን በላያን በላዕተ ሰብእ -(ናሆ፫ -፲፪። ሕዝ፴፮ -፲፫ ኢሳ፳፬ -፮። መቃ -ገ፱ መጽ -ምስ)

በላዪ -(ዪት ይያን ያት) የሚያረጅ የሚያልፍ የሚጠፋ እስመ ውእቱ ብር በላዪ ወዘይማስን። ዓለም በላዪ -(ጥበ፲፬ -፰። ስንክ -ጥቅ፳ ኅዳ፲፰)

በል -ትእዛዝብህለ ቤለ ይቤ ቤልከ ትቤ ትበል በል

በልሐ  -ተሳለበልኀ

በልቀም -(ዐረ በልዐም) መሬታዊ ሕርይ የሚዝል የሚደክም፤ የሚተኛ የሚጋደም ሕስሐን ተመልከት -(ፈላስ -ገ፲፮)

በልበለ [1]-አረጀ­በሊል በለ። በልየ

[2]-(የበልየና የበለ ዲቃላ ዕብ ባልቤል) አረጀ አፈጀ ለቀ ተበጣጠሰ የልብስ የምንጣፍ የመሣሪያ በልይንና በሊልን ተመልከት

()          በልቶ ቶት -(በለተ ይቤልት ይበልት። ዐረ በለተ ረጠ። ዕብ ቢልቲ ብቻ ያለ) መበለት፤ መለየት መነጠል፤ ሥጋን በየብልቱ ማውጣት። ማደኽየት ድኻ ብቸኛ ማድረግ ብቻ ማስቀረት።

በልይ ዮት -(በልየ ይበሊ ይብለይ። ዕብ ባላህ። ሱር ብሊይ። ዐረ በሊየ) ማርጀት ማፍጀት መለወጥ መበላሸት መበስበስ መበጣጠስ ማለፍ መቅረት ማለቅ መጨረስ መጥፋት መታጣት፤ ዘንዱ ይበለይ ነው፤ በለየ ካላለ ይብሊ አያሰኝም፤ ኀረየንና ፈረየን ጸገየን ተመልከት ኵሉ ዘነፍስ ይበሊ ከመ ልብስ ኵሉ ብር ይበሊ ወየኀልቅ። በልየ ሥጋየ ወማእስየ ብርየ ተወለጠ ወበልየ ወበልየ ነገ እምኔሆሙ -(ሢራ፲፬ -፲፯ -፲፱። ሰቈ፫ -፬። ዳን፲ -፰። ኢዮ፴፪ -፲፭)

በልግ -(ዐማርኛ) የበጋ ዝናም፤ ጸደይ።

በሰከ -(ዐማርኛ) ቲክ በተከ፤ በጠሰ ሰና ይዋረሳሉ፤ ይልቁንም በዐረብ በሱርስት ሶር ቶር

በሲል ሎት -(በሰለ፤ ይበስል ይብስል። ባሻል። ሱር ብሼል) መብሰል መሟ መንደርክ፤ እሳት በፀሓይ መለስለስ ተጋግሮ ተነፍሮ ታምሶ ተጠብሶ መበላት መድረስ፤ ለጥርስ መግራት፤ መሸት መጐምራት ኢበልዐት ምንተኒ በእሳት ዘበሰለ ሠዊት ዘበሰለ ዘእንበለ ደብስል -(ስንክ -ጥቅ፩ ኢሳ፲፯ -፭። ኤር፴፩ -፴፪)

በሲስ ሶት -(በሰ ይበስስ ይብስስ) መበሰስ ማደን፤ በሳስ መኾን፤ የወሬ ያውሬ በስበሰን እይ የዚህ ዲቃላ ነው ማለዘብ ማለስለስ የነገር የልብስ

በሣሪ መበሥር -የሚያበሥር አብሣሪ ወሬ ነጋሪየምሥራች ባይ። ገብርኤል መበሥር -(ሰንክ -ታኅ፳፪)

በሥሮ  -() -(በሠረ ይቤሥር ይበሥር) አው በሢር ሮት -(በሠረ ይበሥር ይብሥር ዐረ በሺረ። ዕብ ባሤር) ማብሠር የምሥራች ማለት ሐዲስ የደስታ ወሬ ማውራት መንገር፤ መልካም ንቢት መናገር። ሥጋ ማልበስ፤ ሥግው ማድረግ ምስጢረ ሥጋዌን መስበክ ማስተማር በወሬ በትንቢት ማስፈሣት ደስ ማሰኘት መጻሕፍት ግን በበሠረ ፈንታ አብሰረ ይላሉ ባስደራጊና በሳቱ ያማርኛ ነው ሆከን አወ እንደ ማለት። ገብርኤል አብሣ ትስብእትከ። ብሠራ ማርያም ብሠሮ ዘካርያስ በእንተ ልደቱ ዮሐንስ ወንጌለ መንግሥት ያበሥር -(ቄድር መዋሥ። ስንክ -ታኅ፳፪ ፈላስ) ብርስንና ምስር የሚጣፍ። በሳት ነውና ሠዉም በዚህ ምክንያት ተሳስቷል።

በስብሶ  ሶት -(በስበሰ ይበሰብስ ይበስብስ ዐረ በጸ በጽበጸ። ዕብ ባጻጽ ባጽቤጽ ፈለቀ መነጨ) መክፈት መግለጥ ማቍለጭለጭ የዐይን። መነስነስ መቍላት ማወዛወዝ የዥራት በቁሙ መበስበስ መራስ ፣መርጠብ መበላሸት -(ዐማርኛ) በኍበኈን እይ ዘሩ በሲስ በሰ በሰሰ ነው

በሶንስ በሸንስ ብሸንሶ -(ቅብጥ ፓሾንስ) የግብጦች ወር ግንቦት። ብሸንሶ ይሰመይ በሰንጹስ፤ ወካዕበ ይሰመይ ማኹን -(አቡሻ -)

በረሓ -በቁሙ ምድረ በዳ -(ዐማርኛ)

በረምሃት -(ቅብጥ) ዝኒ ማሁ ወርኅ መጋቢት። ጽርእ ፋሚኑት ይባላል። በረምሃት ይሰመይ ፋሚኑት -(አቡሻ -፰። ተረ -ቄር፳፭)

በረረ -(ሰረረ) ቁሙ፤ ሮጠ ነፈ ጣደፈ ዐለፈ ዘለቀ በሳ ነደለ ወፅአ ጺኑ በሪሮ ረገዞ ለአሐዱ ውስተ ሰንበዑ ወወፅአት ናት ሪራ እን ዘባኑ ወወግአቶ ካልኡ በረረ ቅትራት ውስተ ገሪሁ በረሮ እስ ዘባኑ ኢይበርሮ ቀስተ ብርት -(፪ነገ - -፳፪ ገድ -ተክ ንክ -ነሐ፲፬ መሳ፫ -፳፪ ኢዮ፳ -፳፬)

በረቅ -በቁሙ፤ ነጭ ዐፈር ደንጊያ ብሕካ ጠመኔ የኖራ ይነት

በረከት -(ታት) ቁሙ ማበር መበርከት አበረካከት፤ ብርከታ ብዛት። ምስጋና ምርቃት፤ ቡሩክ መባል ጸጋ ጸጋ ብት ድልብ ላባ መልካም ነገር ኹሉ በረ ኅብስት በረ አሮን ፈኑ ዕለ ሕዝብከ። ብር ወስብሐት ወበረት። ኵሉ በረ እለ ባረ እግዚ። በረከተ ግብጽ ትበልዑ ቤረከተ -(ትር -ወን። ራ፴፮ -፳፪ ራእ፭ -፲፪ -፲፫ ኩፋ -፲፱ ዘፍ፵፭ -፲፰ ኢሳ፶፭ -)

በረየ -ቁሙ -(ጥየ) በረየ በረገገ በሬኛ ወገሸ ደነበረ፤ ፈራ ደነገጠ። -(ተረት) እባብ ያየ ልጥ ቢያይ በረየ አበራየ ረባየ አኼደ አስኬደ አስረገጠ አስጠቀጠቀ። ማበራየት ያውድማ፤ ማረባየት የጤፍ ዕርሻ መሬቱ እንዲጠብቅ ከብት ይነዱበታል። በሬ በረት ባሪያ ባሬታ ማለት ዐማርኛው ከዚህ ወጥቷል፤ በዐረን እይ። የወዲያኛው ትግሬ ሐባብም ክሕደ ሲል በረየ ይላል፤ ምስጢሩ ፈራ ደነገጠ ካለው ይገባል

በረድ [1]-( አብራድ ዕብ ባራድ ሱር ባርዳ። ዐረ በረድ) ቁሙ ረዶ የዝናም ደንጊያ የውሃ ጠጠር፤ በነፋስና በደመና ወንጭፍ ከላ ከሰማይ የሚወርድ የሚወረወር ዝናመ መዐት መጠኑ የበጠጥ ከዚያም የሚበልጥ የሚዛን ዋቂ የሚያካክል -(ዘፀ፱ -፲፰ ኢሳ፴ -፴። ሕዝ፴፰ -፳፪ ራእ፲፮ -፳፩) ወገሮሙ እግ እምሰማይ በእብነ በረድ ሞፀፈ መዐቱ ያወርድ ብራደ -(ኢያ፲ -፲፩ ጥበ፭ -፳፫)

 -ሰው ሠራሽ ምድራዊ በረዶ በመኪና ውሃ ለይተው የሚያወጡት ግንድ ግርንቡድ የሳንቃ ስባሪ የሚያካክል።

[2]-በረድ -(ዕብ ሼሌግ ቄራሕ) ብትን በረዶ ውርጭ ዐመዳይ ተበትኖ ወርዶ የሚረጋና የሚጋገር ባዘቶ ንድፍ የሚመ -(መዝ -፻፵፯ -ኢዮ፮ -፲፮) በረድ ወአስሐትያ። ቈረ ከመ በረድ። ኣጻዐድዎ ከመ በረድ ረድ ይዘንም ዕለ ሰልሞን -(ጥበ፲፮ -፳፪። ኩፋ -፳፫ ኢሳ፩ -፲፰ መዝ -)

[3]-በረድ የብርሌ የብርጭቆ ይነት ንጣቱ የረጋና የተጋገረ ውርጭ የሚመስል። አርኣያ ዘሕብረ በረድ ባሕር ከመ ንተ በረድ -(ሕዝ፩ -፳፪። ራእ፬ -) የእብንን አፈታት ተመልከት

በረጽ -(ዐረብ) ለምጽ ነጭ የሚብለጨለጭ

በሪህ ሆት -(በርሀ ይበርህ ይብራህ። ዐረ በሪሀ፤ በሀረ ዕብ ባሀር) መብራት፤ መበራት መታየት መገለጥ ብርሃን መኾን ደስ ማሰኘት ምንት ይበርህ እምነ ፀሓይ ይበርሁ ከዋክብተ ሰማይ። ይበርሁ ከመ ብርሃነ ሰማይ ወይበርህ ሎሙ ብርሃነ ምላክ ወምድር በርሀት ምስብሐቲሁ ዘይገብር ምጽዋተ እን ይበርህ ገጹ በርሀ ቦሙ ወኅሊናሆሙ -(ሢራ፲፯ -፴፩ ኢሳ፲፫ - ዳን፲፪ -፫። ሔኖ፩ -፰። ሕዝ፵፫ - ቀሌ)

በሪር ሮት -(በረ ይበርር ይብርር ባራር ሱር ባር ዐረ በረ በሪረ) ምረጥ መለየት መልቀም ማጥራት ጽሩይ ጸዐዳ ማድረግ የማዕደናት። በርበረን እይ

በሪቅ ቆት -(በረቀ ይበርቅ ይብርቅ ዕብ ባራቅ ሱር ብራቅ። ዐረ በረቀ) መብረቅ ብልጭ ማለት መፍለቅ ማንጸብረቅ መወርወር መመዘዝ የመብረቅ የሰይፍ። ብርቅ ድንቅ ታይቶ የማያውቅ መኾን መታየት መገለጥ። በሪጽና በሪቅ አንድ ዘር ናቸው፤ በሪጽ በሪቅ ወጥቷል። በዕጠሱ ይበርቅ ብርሃን ወላትው ይበርቅ በረቀ ሥጋሆሙ ብተ በረቀ መብረቅ ዲቤሁ ምሰማይ -(ኢዮ፵፪ -፱። ናሖ፫ -፫። መቃ -ገ፪ ድጓ። ግብ፬ -) መበርቋት መገርጣት ያዝመራ

በሪዕ -(በርዐ ይበርዕ ይብራዕ ዐረ የሪዐ። ዕብ ያራዕ) መራድ መንቀጥቀጥ መታወክ መናወጥ መገፋት መናጥ መወዛወዝ ፍርሃት ንፋስ የተንሣ -(ማቴ፲፩ -)

በሪክ ኮት -(በረከ ይበርክ ይብርክ። ዕብ ባራኽ ሱር ብሬኽ ዐረ በረከ) መብረክ፤ መብረክረክ መንበርከክ ልበትን ማጠፍ በጕልበት መቆም፤ መስገድ፤ ተንበርክኮ መኼድ፤ ተጣጥፎ መተኛት -(ጥኰ) መኰድኰድ -(ዘኍ፳፪ -፳፯) ሶበ በጽሐ ገመል ኀበ ውእቱ መካን በረከ በብረኪሁ ወኢተንሥአ -(ስንክ -ነሐ፲፱)

በሪዝ ዞት -(በረዘ ይበርዝ ይብርዝ ዐረ። ዕብ ባራዝ) ማግለል መለየት ዕዳሪ መውጣት መናጻት መበረዝ መበጥበጥ ጠጅ መጣል ጠላ መዘለል፤ ፈሳሽን ከፈሳሽ መቀላቀል

በሪድ ዶት -(በረደ ይበርድ ይብርድ። ዕብ ባራድ ዐረ በሩደ) መብረድ መቀዝቀዝ፤ በረዶ መኾን መውረድ መርጋት የዝናም የውሃ በረዶ መምሰል በረዶ መልበስ በውርጭ በበረድ መሸፈን መታፈን የደጋ የተራራ እንደ የወልና እንደ ቧሒት

በሪጽ ጾት -(በረጸ ይበርጽ ይብርጽ ዕብ ባራጽ ዐለፈ ተረፈ ፈልቶ ገንፍሎ) ማንጸብረቅ ማሸብረቅ፤ ማወልወል ማጽደልደል የመልክ የፊት

በራ -ስመ ኪሩብ ገጸ ሰብእ፤ ወልዳዊ ወልደ ሰብኣዊ ማለት ነው። ፪ኛም ባር ብሎ ጐሽ የበረሓ እንስሳ ይላልና ገጸ ላሕምንም ያሳያል ፫ኛም ባርቡር ብሎ ዐንገተ ረዥም ወፍ ዋነተኛ የባሕር አሞራ ይላልና፤ ገጸ ንስርንም ያሳያል ኛም በርና ጓል አንድ ናቸውና፤ ዕጓላዊ ዕጓለ አንበሳዊ አሰኝቶ ገጸ አንበሳን ያሳያል በራ መራ መሊጦን ሱርትዮን -(መዋሥ)

()          በራህ -በራ መላጣበርሐ።

በራሕ -(ሓን ሓት) መላጣ ራሰ ገላጣ ጠጕ የሸሸ ከቦታው የታጣ የራሱ ርበት መሳልና ነት ሳንባና በት የሚመስል -(ዘሌ፲፫ -፵። ፬ነገ - -፳፫) ለኤልሳዕ ነዊ ቆሙ ወበራሕ ርእሱ -(ስንክ -ሠኔ፪) በረኸኛ የበረሓ ሰው ዳኝ መነኵሴ

በራሪ -(ሪት ርያን ያት) በቁሙ የሚያልፍ የሚዘልቅ

በራቂኒም -(ዕብ ባርቃኒም) ነጫጭ እሾኾች ሸሽሎች ወይም ግራሮች የግራር ይነቶች፤ አንዱን ባርቃን ይላል። አርቆሚንን እይ ዚህ ጋራ አንድ ነው -(መሳ፰ -፲፮)

በራዲ ብሩድ -የበረደ በራድ ብርዳም በረዷም በሪድ ቀዝቃዛ

በር [1]-በቁሙ ደጅ አፍ መውጫ መግቢያ መዝለቂያ ማለፊያ -(ዐማርኛ) ነቅጸን ተመልት።

 [2]-(ሱር ወዕብ ባር) ወንድ ልጅ ተማሪ ደቀ መዝሙር በር ጤሜዎስ። በር ባን -(ማር፲ -፵፮ ማቴ፳፯ -፲፮)

በርህ -(ሃት) ብርሃን ጸዳል ውጋጋን እሳት ፍሕም ነበልባል። በርህ ሠረቀ ጻድቃን በርህ ወጽልመት -(መዝ -፺፮። ዳን፯ -፵፯። ድጓ) ይስኅን መንገለ በርህ -(ማር፲፬ -፶፬። ሉቃ፳፪ -፶፮) በርህ እሳት መባሉ መላሾች በእሳት ቦታ ጣፉት እንጂ ፍችው ኹኖ አይዶለም።

በርሖ ሖት -(በርሐ ይቤርሕ ይበርሕ ዐረ በሪሐ ዕብ ባራሕ ሸሸ) መብራት መገለጥ መቦሕየት በራ መኾን መመለጥ መሸሽ ማምለጥ ሮጥ መፈርጠጥ ከዱር ከበረሓ መግባት። ስንሐንና ቀርሐን ተመልከት የዚህ ጎሮች ናቸው

በርሙዳ -(ቅብጥ) የወር ሚያዝያ በጽርእ ፊርሙ() ይባላል -(ገድ - አርጋ - -) በርሙዳ ይሰመይ ፈርሙኒ -(አቡሻ -፰። ተረ -ቄር)

በርሞስ -አስቄጥስ የነመክሲሞስ የናርሳንዮስ ገዳም፤ ደብረ ሮም ዳመ ሮም ማለት ነው -(ስንክ -መጋ፳፭)

በርበሪ -በርበራዊ የበርበር ው።

በርበሬ [1]-(ዐረ ፊልፊል ባባሪ) ቍንዶ፤ ንደዶ ጠጕ ያረረ የተኰማተረ። ቍንዶ በርበሬ መልኩ የበርበርን ጠጕር የሚመስል ንዶ መባልን ከሻንቅላ ጠጕ ወስዶታል፤ መመሳሰል የጋራ ነውና ገብር ሊም ይቤ ርኣያየ ጸሊም ወጸጕረ ርእስየ በርበሬ -(ፈላስ -)

[2]-(ጽር ፕፕሬ) ቁሙ ቀዮ በርበሪ በርበራዊ ከበርበር የመጣ የበርበር አታክልት ስሙ ፍልፍል ሲኾን ከበርበር አገር ስለ መጣ ርበሪ ይባላል፤ ይኸውም ጐንደሬ፤ በጌምድሬ እንደ ማለት ው፤ ዐደስ ከምስር አገር ስለ መጣ፤ ምስር ግብጥ ምስር እንዲባል -(መጽ -ፈው) በፕፕሬ አንጻር ፈቱት ግን ቀይሕ እሳታዊ ነበልባላዊ ማለት ነው በርበራዊነቱ ሳይቀር መልኩንም ግብሩንም ያሳያል፤ ፐፒራን ተመልከት -(ሙሾ በቴዎ ጊዜ) በሺዋ በትግሬ በወሎ በላስታ በጐዣም ያላችኹ አንድ እግር በርበሬ መንቀል ተስኗችኹ ተኵሶ ለብልቦ አቃጥሎ ይፍጃችኹ። ቍንዶውም ቢኾን እንደ ኋላ ይጥቈር እንጂ ጥንቱን ሲያፈራ ቀይ ነው ይባላል

በርበር [1]-ዘረፋ ምርኮ የብርበራ የዘረፋ ገንዘብ። እሬስየኪ በርበረ ለአሕዛብ እለ ይትካፈሉ በርበረ -(ሕዝ፳፭ -፯። ኢሳ፱ -፫። ምሳ፩ -፲፫)

[2]-ያልተማረ ያልሠለጠነ ሕዝብ ፊደልና ጽሕፈት ሕግና ሥርዐት የሌለው በቅሚያ የሚኖር ጭንጩ አረመኔ ሽፍታ ወያኔ ስመ ነገድ ስመ ሀገር፤ ከግብጽ ቀጥሎ የሚገኝ የአፍሪቃ ክፍል። የሱማሌም አገር በርበራ አቅኝውና የበርበር ራጭ ነው ይባላል፤ በርበርነቱንም ግብሩ ይመሰክራል ወመጽኡ በርበር ረማውያን ከመ ያመዝብሩ ብያተ መነኮሳት። በመጥባሕተ በርበር ተቀትሉ ዘዞ እግዚእነ ከመ ይሑር ገረ በርበር -(ስንክ -ጥቅ፳ ጥር፳፮ ኔ፳፮ መስ -)

በርቢር -(ዕብ ቦር ብኤር) ዐዘቅት የውሃ ወይም የእኽል ድጓድ ዋሻ ጐሬ መቃብር ውስጡ የተቦረቦረ -(ሕዝ፴፪ -፲፰ ፴፬ -፲፪ -፲፭)

በርባሪ -በርበራዊ የበርበር ው።

በርባር -የዛፍ ስም፤ ብርብራ ቅጠሉና ፍሬው ዓሣ የሚያሰክር ሕር የሚያሸብር

በርባሮስ -(ጽር ቦርቦሮስ) ዝኒ ከማሁ ታላቅ ድጓድ ዕመቀ ምድር መሠረተ ምድር የጥልቅ ጥልቅ መጨረሻ መቅ -(አዋል)

በርብሮ ሮት -(በርበረ ይበረብር ይበርብር በሪር በረ በረረ) መበርበር መዝረፍ፤ መበዝበዝ፤ የቤትን ድልብ በቤት ያለን ንዘብ ጐርጕሮ መውስድ ባዶ ማስቀረት ድጓድ ፋሪ ፈሩን አውጥቶ ውስጡን ባዶ እንዲያደርግ እንደዚያ ማለት ነው አልቦ ዘይክል በዊአ ቤተ ያል ወበርብሮ ዋዩ ኢቀደመ አሲሮቶ ኀያል ወእምዝ ይበረብር ቤቶ በረብሮሙ ኀይሎሙ በርብሩኒ ዋይየ -(ማር፫ -፳፯ ኢሳ፲ -፲፫ ጦቢ፩ - መዝ -፻፰)

በርዮድስ -(ጽር ፔሪዎዶስ) መር፤ የቀመር ስም፤ የጨረቃ ቢኾን ፲፱ የፀሓይ ቢኾን ፳፰ ዓመት። ሲያበዛ ርዮድሳት ይላል -(አቡሻ -፳፭)

በርደደ -በረደደ ረጋ ጸና ደነገየ፤ በርዳዳ ኾነ መታ ቀጠቀጠ፤ ሞረደ ወበአእባን ሥጋሁ በርደዱ -(ስንክ -ግን፰)

በቀለ -(ዐቢይ አገባብ) ፈንታ ብፁዕ ዘይትቤቀለኪ ቀለ ተበቀልክነ -(መዝ -፻፴፮ ር፲፱ -ቍ፷፱)

በቀል -(ላት) በቁሙ ቅጣት የክፉ ብድራት፤ ዕዳ ፍዳ ቂም ደም። እትቤቀሎሙ አርባዕተ በቀለ እትቤቀል በቀለ ህየንተ አዕይንትየ ከመ ያግብኡ በቀል ምኀበ እግ ለምድያም በቀለ እኁ -(ኤር፲፭ -፫። መሳ፲፮ -፳፰ ዘኁ፴፩ -፫። ነገ - -፳፯)

በቀልት -(ታት) ሌን ዘንባባ ፍሬው ተዘርቶ የሚበቅል ቁመታም። ዘቆምኪ ይመስል በቀልተ ወፈረየት ይእቲ  በቀልት ሠርተ ወክልኤተ ስካለ ሶቤሃ። በቀልተ ተመርት በቀልታት ወተምራት በቀልታተ ወፀበራተ ሥዐለ -(ማሕ፯ - -፰። ስንክ -ሚያ፳ ኢዮ፳፱ -፲፰። ንክ -ጥር፳፪ አርጋ -) በቀልት ግንዱ፤ ፀመርት ቅጠሉ ተምር ፍሬው። ፀምርንና ተምርን ተመልከት

ባቌላ  ባቄላ -(ዐረ ባቂለን ባቂላእ) ቁሙ ባቄላ ል፤ ያበባ እኸል፤ በቈልት የሚኾን -(የውርድ ነዥ ድብና ምላሽ) ከሰው ክፉ ዲቃላ ከእኸል ክፉ ባቄላ ከልብስ ክፉ ጠላ። ጠላት ይገፋል ዲቃላ፤ ወራት ይገፋል ባቄላ ያግደረድራል ነጠላ

በቍላዊ -የቡቃያ የተክል ተክላም ባለተክል ይል በቍላዊ ወእንስሳዊ -(አዋል)

በቍል ሎት [1]-(በቈለ ይበቍል ይብቍል። ዐረ በቀለ) መብቀል ማጐንቈል፤ ካፈር ከመሬት መዛመድ መዋሐድ መጽደቅ ሥርን ወደ ታች ቅጠልን ወደ መስደድ፤ መፀነስ መቋጠር መወለድ መፈጠር፤ መሥረጽ መውጣት ይበቍል ውስቴቱ ዕር ወሦክ በቈለ ሥርዎሙ ይበቍል ክነፊሆሙ ይበቍሉ ከመ ሣዕር ሦክ ወአሜከላ ይብቍልከ -(ኢሳ፭ - -፳፬ -፴፩ ፵፬ -፬። ኩፋ -፫። ዘፍ፫ -፲፰)

[2]-በቍል -(ላት አብቋል) ቃያ በቈልት ብቅል፤ያታክልት ፍል ችግኝ ግልግል፤ እኽል ተክል ቅጠል ሳይዘሩት የሚበቅል ማናቸውም ኹሉ ይሴሰይ በቍላተ ምድር። አሕማላተ በቍላት በቍላት ቀታልያን። ሥዕርተ ርእስከ ዘስሙር ብቋሉ -(ስንክ -ጥር፳፰ ግን፲ - ፳፫ ደራሲ)

በቂቅ ቆት -(በቀ ይበቅቅ ይብቅቅ) መሠንጠቅ፤ መተርተር፤ ዕዳሪ ማውጣት የርሻ።

በቍዔት -ልመና ምልጃ ጸሎት በጸሎትና በልመና የሚገኝ ጥቅም። አንተ ወከፍ ዘኵልነ ሰክዮተ ወበቍዔተ -(ሊጦን)

በቍዕ ዖት -(በቍዐ ይበቍዕ ይብቋዕ በቀወ) መብቃት መኾን መገባት መርባት መጥቀም ግዳጅ መፈጸም መርዳት አይዞኽ ማለት ልመናን ምልጃን መስማት መቀበል በጎ ማለት ምስክሩን በተራው ተመልከት ይሥሐቅ ይበቍዕ ለዛቲ መት። ዘይበቍዕ ምግበ ንዋዩ ምንት ይበቍዕ ሠዊዕ ለአማልክት ዐርክ ወማኅፈር ይበቍዕ በመዋዕሊሆሙ። እግ በቍዐነ በኵሉ እስእለክሙ ብቍዐኒ ብቍዐኒ ከመ ትገብር -(ስንክ -ኅዳ፱ - -፴፪። ራ፴ -፲፱ -፳፫ ዮሴፍ ፩ጴጥ - -፲፩። ፩ዕ - -፵፮) አንዳንድ መጽሐፍ በተበቍዐ ፈንታ በቍዐ ይላል፤ አያሰኝም። ትሬእዩ ከመ ልቦ ዘትበቍዑ። አልቦ ዘበቋዕኩ። አልቦ ዘይበቍዕ ዘይረቂ ፈቀደ ይትባረክ ይብቋዕ ምኔከ -(ስንክ -መጋ፳፪ ፩ቆሮ -፲፫ -፫። መክ፲ -፲፩ ፊልክ -፶፮)

በቂው ዎት -(በቀወ ይበቁ ይብቁ ዐረ በቀ ዕብ ባቃዕ ከፈተ) መክፈት መለቀቅ፤ ክፍት መኾን ዋሻ መምሰል ለመጕረሥ ለመከተት፤ የአፍ የጕድጓድ። በቀወት ምድር ወውኅጠቶ ዳታን መጽሐፍ ግን አብቀወት ይላል፤ አያሰኝም -(መዝ -፻፭) ለቀወን እይ

በቍጽ ጾት -(በቈጸ ይበቍጽ ይብቍጽ) ማንደድ ማቃጠል ማያያዝ ማጋም፤ ማፋም ማምረት ማብሰል ማንደርከክ መጫር መተርከስ፤ መዝገን ማፈሥ የከሰል የፍም ነሃ ዘይበቍጽ ፍሓመ ወይበቍጹ ፍሓመ -(ኢሳ፶፬ -፲፮ ዮሐ፲፰ -፲፰)

በቃሊ -(ሊት ልያን ያት) የሚበቀል ተበቃይ፤ ቂመኛ ደም መላሽ ብድር ከፋይ መጽሐፍ ግን እንዳማርኛው ተበቃሊ ይላል እግዚ ተበቃሊ ለእለ ይትገፍዑ ምእደ ገፋዕያኒሆሙ ይገፍዖ እግዚ ገፋዒ ወይትቤቀሎ ተበቃሊ -(መቃ -ገ፮ ቀሌ)

በቅል ልት -(ዐረ በቅል ዕብ ፌሬድ) በቅሎ፤ አጋሰስ ካህያ ከፈረስ የሚዴቀል አባቱ አህያ እናቱ ፈረስ። ባቱና እንስቱ ዘር ለመስጠትና ለመቀበል ርስ በርሳቸው የማይገጥሙ የማይሰማሙ እጅግ ቅብጥብጦች ስለ ኾኑ መውለድና መርባት የላቸውም፤ ሲገናኙ ግን ይወልዳሉ፤ አንድ የሰላሌ ሰው በቅሎው ወልዳ ምኒልክ ከነግልገሏ አምጥቶ እንዳሳየ። ፍችው መስተበቅል፤ አንዳንድ መምህራን ግን ሐዲስ ቡቃያ ይሉታል፤ ከጥንት ያልነበረ ማለት ነው። -(ተረትና ቅኔ) በቅሎ ቢወልዷት እንጂ አትወልድ እኔም እንዳላማ ልቁም ዐዋጅ ሲነገር ምንይልኽ ሰብአ ሺዋ ቅኔ ተዘርቶ በቅሎ ቢቀር ኢትኩኑ ከመ ፈረስ ወበቅል -(መዝ -፴፩)

በቅል (ሱማሌ ሐረር ራጌ) የቍጥር መቶ። ሸማኖችና ዝሓ አዝጊዎች ወይም ድር አድሪዎች መቶውን ጥንድ አንድ በቅል እንዲሉት።

()          በቅሎ ሎት -(በቀለ ይቤቅል ይበቅል ዐረ በቀረ ባቄር) መመርመር መጠየቅ፤ ግፍን በደልን መርምሮ ማወቅ፤ ማሰብ መቍጠር ከዚህ የተነሣ መበቀል መቀየም መቅጣት፤ ፍዳውን መስጠት ማስበበት። በለበቅ በጨንገር መግረፍ ማስለፍለፍ የሕፃንና የቤተ ሰብ ቅጣት መጽሐፍ ግን በበቀለ ፈንታ አብቀለ ተበቀለ ይላል ባስደራጊና በተደራጊ አንቀጽ ኹሉም ስሕተት ነው ያሰኝም፤ ያማርኛ ው። ሳብዕተ በቀለ ያበቅል ዮጊ ትክል ተበቅሎቶ ዘአበሰ ዘይትቤቀሎሙ ለጸላእቱ -(ዘፍ፬ -፲፭ ራ፯ -፮። -)

በቅበቀ -በቀበቀ ተኰተ የማሽላ።

በቋሊ -(ሊት ልያን ያት ልት) የሚበቅል የሚሠርጽ፤ በቃይ ዘር ቅንጣት

በቋዒ -(ዒት ዕያን ያት) የሚበቃ የሚጠቅም ቃሚ፤ ግዳጅ ፈጻሚ ኮነ በቋዒ ለኵሉ። በቋዔ ተድላ አኀው በምንዳቤ በቋዕያነ ይከውኑ ኮኑ በቋዕያነ ከመ ይሥርዑ ዋዮሙ -(አርጋ -፩። ዳ። ምሳ፲፯ -፲፯ - -፳፬ -) በበቋዒ ፈንታ ባቍዕ -(ዕት ዓን ዓት) ይላል ፍችው አንድ ነው ባቍዕት ባቍዓኒሃ ባቍዓን -(አርጋ -፩። ዘካ፮ - ሄርማ)

()          በበ -(ደቂቅ አገባብ) በየ እየ ደጊመ ቃል ተጸውዖ በቀር ብትን ኹሉ እየገባ ይዘረዝራል፤ ሲዘረዝር እንዳለ በቁሙ ይፈታል ባይዘረዝርም ተዘርዝሮ ወይም በደጊመ ቃል ይፈታል በበ ነገ ወበበ ዘመዱበበ ሐዱ በየ እየ በበ ነግ በበ ሠርክ ጧት ማታ ማታ። በበ ዕለት፤ በየለቱ ዕለ ዕለ ዘወትርበበ ወርኅ በበ ዓመት በበ በዓል በበ ሕቅ በበ ንስቲት እያለ እንደዚህ ይፈታል። ነሥኡ በበ ዲናር፤ ድሪም ድሪም፤ አንዳንድ ድሪም ፈነዎሙ በበ ክልኤቱ ኹለት ኹለቱን ወይም ኹለት ኹለቅ አርጎ። ወረፈቁ በበ ምእት ወበበ ኀምሳ ፻፻ው፤ ፶፶ው፤ ወይም ፻፻ና ፶፶ እየኾኑ ያሰኛል። ለለንና ዘዘን ተመልከት የዚህ ጎር ናቸው

በበ ሕቅ -ጥቂት ጥቂት የጥቂቱ በበ ሕቅ ህቀ -(ቅዳ -ድጓ)

በበ አሐዱ በበ አሐዱ አሐዱ -በያንዳንዱ፤ በየብቻው፤ በየራሱ፤ በየራስ በየራሱ -(ሱቱ -ዕዝ፲፩ -)

በበበይኑ -በበበይኑ -(በበ በይኑ) በየራሱ በየብቻው ራስ ራሱ ብቻ ብቻው በበን ተመልከት ናብስት መሠጥ ወመንኰራኵራት ዘበበ በይኑ -(ስንክ -መጋ፪)

በበይነ -( በይን) ዝኒ ዓዲ ማሁ ስለ እንደ እን አዳማቂ ነው ሥራ የለውም በበይነ ፍሱ ለዝንቱ ብእሲ በበይነ ዚኣክሙ በበይነ ወርቅ በበይነ እግ በይነ መኑ በበይነ ምንት -(ዮና፩ -፲፬ ሚክ፫ -፲፪ ኢሳ፵፰ - ፳፱ -፲፭ ፩ነገ -፲፬ -፴፰። ሚል፩ -)

በበይኑ -በብቻው በራሱ ወይም ለብቻው ብቻውንጻማዊ ወፈጻሜ መልእክት ዘበበይኑ -(ስንክ -ኅዳ፬)

በበይናቲሁ -ርስ በርሱ አንዱ ካንዱ ጋራ በበይናቲሃ ቲነ እያለ ይዘረዝራል። ተባሀሉ በበይናቲሆሙ። ተኣምኑ በበይናቲክሙ -(ዘፍ፵፪ -፳፩። ቅዳ)

በበይናት  -በኹለት ወገን በኹለት ክፍል ኹለት ወገን ኹኖ

በቢክ -ፍሬ ገነት፤ አዳም ይበላው የነበረ ወይም እንዳይበላው በትእዛዝ እሾክ የታጠረ፤ ቢበሉት ቢያክ ቢያክ የሚያሰኝ -(ገድ -አዳ)

በተነ -(ይበትን፤ ዐማርኛ) በቁሙ ተነ በታተነ ረወ ዘርዐ

በቲር ሮት -(በተረ ይበትር ይብትር። ትግ በትረ። ባታር) መቍረጥ መከርከም ማረቅ ማቅናት፤ ቀጥ ለጥ ማድረግ የንጨት። መምታት መውቃት መነረት። መተረን ተመልከት የዚህ መንቲያ ነው

በቲት ቶት -(በተ ይበትት ይብትት። በልየ) መበተት ብትቱ መኾን ማለቅ ማርጀት የልብስ። በልበለን ተመልከት

በቲክ ኮት -(በተከ ይበትክ ይብትክ ዐረ በተከ። ዕብ ባቴቅ ናታቅ) መበተክ፤ መበሰክ መቍረጥ መበጠስ አባላ መምታት መንቀል መፈንቀል መናድ ማፍረስ፤ መስበር መሠንጠር እበትክ ማኅሜከ። በተ ማእሰረ -(ነሐ፩ -፲፫ ኤር፭ -) በበተ ፈንታ ብተ ይላል ያሰኝም። ታበትክ ቃሎሙ በኀበ እግ -(ዘፀ፲፰ -፲፱) ብራይስጡ ግን ውሄቤእታ ይላል ታበውእ ታበጽሕ ታቀርብ ማለት ነው ብተክ መብተክተክ ብሰክሰክ መበላሸት ንቱ መኾን የግብር የነገር -(ዐማርኛ)

በታሮን -(ጽር ፓቴሮን) አበው፤ ከአዳም እስከ ኖኅ ያሉ ዐሥሩ አባቶች ወይም ሌሎች ደብረ በታሮን ዘውእቱ ብሂል ደብረ በው -(ስንክ ፲፰)

በትረ  ብርዕ -የሸንበቆ ምርኵዝ ኅለት ውስጠ ክፍት -(ሕዝ፳፱ -፮። ኢሳ፴፮ -)

በትረ  ወርቅ -ከወርቅ የተሠራ በወርቅ የተጌጠ የጳጳስና የንጉሥ በትር -(አስቴ፭ - -)

በትረ ኅጺን -የብረት ዘንግ ባለብረት ጅንፎ፤ ጅንፏም በትር -(መዝ - ራእ፪ -፳፯)

በትረ መሃፒል -ዐጭር ወፍራም መንዶ እንደ ንቻ እንደ መሮ መምቻ ያለ ዐጣቢ ቀለም አግቢ ልብስ የሚመታበት -(ስንክ -ጥቅ፳፯)

በትረ መዐት -መቅጫ ለበቅ ንገር ረኃብ ጦር፤ ዐባር ቸነፈር -(ኢሳ፲ -)

በትረ ነገድ -የነገድ አለቃ በኵር ሹም ግንባር ቀደም -(፩ነገ - -፳። ስንክ -ግን፲)

በትረ ያርክ  -(ጽር ፓትሪአርኻ) ጳጳስ ቀዳማዊ ወይም መዠመሪያ ታላቅ ደገኛ አባት ማለት ነው -(ስንክ -መጋ፲፫። ኅ፩)

በትር [1]-( አብትር) በቁሙ ዘንግ ሽመል፤ ምርኵዝ ዱላ ጐመድ ከንተሮ መንደርቶ ለበቅ ንገር። ትወፅእ በትር እምሥርወ ሴይ። ብትረ ልብኔ ስለ ብትር በትርከ ወቀስታምከ ዘይምህክ በትሮ -(ኢሳ፲፩ -፩። ኢዮ፵ -፲፯ ሢራ፳፰ -፲፯ መዝ -፳፪ ምሳ፲፫ -፳፬)

 -ሥልጣን አገዛዝ ቀንበር በትር እን ዲበ ሣዱ በትረ መንግሥትከ -(ኢሳ፱ -፬። አስቴ፬ -፲፩ መዝ -፵፬)

[2]-በትር፤ ወገን ነገድ ዘር ትውልድ በበ በትርክሙ ወበበ ዝብክሙ። በትረ ይሁዳ ወብንያም -(፩ነገ - -፲፱ ነገ - -)

በትበተ -(ይበተብት) በቁሙ በተበተ ቦጠቦጠ ፈለፈለ፤ ውስጥ ውስጡን በላ አቃጠለ የውሻና የዥብ የእሳት አበላል። መቦጥቦጥና መፈልፈል የእሸትና የዳቦ በሊታ -(ተረት) በገዛ ዳቦዬ ልብ ልቡን ጣኹት። ኹሉም ማርኛ ነው፤ ያማርኛ ቃል፤ ከግእዝ ሲዴቀል ተቀጥላም ኹኖ ሲነገር፤ አበቃቀሉና አወጣጡ እንዲህ እንደ ኾነ አስተውል። ሥረ ነገሩ ከሦስት ቅንጣት ደል አይበልጥም አያንስም ቋንቋነቱ ሴማዊ ነውና ፮ቍ ተመልከት።

()          በንቶ -(በነተ ይቤንት ይበንት) አው በኒት ቶት፤ -(በነተ ይበንት ይብንት። ዕብ ማናህ) መስጠት ማደል መገበር በፍቅርና በክብር በፈቃድ። ዐሥራት ማውጣት ልጅ መውለድ በሴት መበከር። ወለዘሂ ባሕተ ጸብሑ ወለዘሂ ብነተ በንቱ ዐሥራት ሹራ -(ሮሜ፲፫ -)

በአት [1]:-መግባትበዊእ ቦአ

[2]-() በአትዋሻ በዊእ ቦአ በኣት

 [3]-በአት፤ ዐቢይና ንኡስ ደቂቅ አገባብ የብትን ዋስው መግለጫ እኹል ገብ ቃልና ፊደል

በኡናህ ባውኒ -(ቅብጥ ፓዎኒ) የግብጦች ፲ኛ ወር -(አቡሻ -)

በዓለ መንበር -ባለወንበር መምህር ጳጳስ ኤጲስቆጾስ -( - -)

በዓለ ሰይፍ -ራጅ፤ ፈላጭ ራጭ ባለወግ ዳንዴ ወንበዴ -(ስንክ -የካ፮ ፊልክ)

በዓለ እድ -እጃም እጀኛ ባለእጅ እጀታ ያለው መሣሪያ ራተኛ ቀጥቃጭ ሌባ

በዓለ ኪን -ተንኰለኛ ብልኀተኛ ተግባረ እድ ያለው።

በዓለ ሐመር -መርከበኛ ባለመርከብ፤ የመርከብ አለቃ መሪ ቀዛፊ -(ዮሴፍ)

በዓለ ኅምሳ -ራቅሊጦስ የትንሣኤ -(ድጓ)

በዓለ ሕብር -ባለቀለም ልብስ አቅላሚ ቀለም አግቢ ወይም ሸያጭ ቀማሚ -( - -፳፫)

በዓለ መርዓ -ርግ፤ የሙሽሮች በዓል -(ራእ፲፱ -)

በዓለ መዛግብት -የገንዘብ ሹም ዕቃ ቤት ጠባቂ -(ዮሴፍ)

በዓለ መጽሐፍ -ባለመጣፍ ጸሓፊ ዐታሚ ሸያጭ ተርጓሚ የመጣፍ መምር -(ዮሴፍ)

በዓለ ምሳሌ -ባለተረት፤ ምሳሌ ዐዋቂ ኹሉን በምሳሌ የሚናገር -(ማቴ፲፫ -፴፬)

በዓለ ምድር -ባለርስት ራሽ ፋሪ ጃን ገበር -(ኢዮ፴፩ -፴፬)

በዓለ ርዴ -ባላራጣ ገንዘቡን በወለድ የሚያበድር -(ቄድር)

በዓለ ቤት -ባለቤት የቤት ጌታ ራዒ መጋቢ አሳዳሪ -(ሉቃ፲፫ -፳፭)

በዓለ አርብዓ -ዕርገት የትንሣኤ -(ሲኖዶ)

በዓለ እቶን -ጋጋሪ፤ የሀገር ዐበ ባለወግ ጋግሮ የሚሼጥ ወይም የሚጋግር ብቻ -( - -፳፫)

በዓለ ዕዳ -አበዳሪ ወይም ተበዳሪ ዕዳ ከፋይ -(ኢሳ፳፬ -)

በዓለ ውዴት -ነገረ ከሳ ባለጋራ -( - -)

በዓለ ጊዜ -ዘመናይ፤ ሹም ባለጠጋ ንጉሥ እንደ ወደደ የሚያደርግ። -(ተረትና ግጥም ስላጤ ) ዘመናይ ቅል ደንጊያ ይሰብራል ያን የጐሹን ገዳይ አበጀኹ ቢላችኹ ይህን ባለጊዜ ምን ትሉታላችኹ።

በዓለ ጸብኅ -ወጥ ቤት፤ ወጥ ዐዋቂ ቀቃይ አብሳይ -(ስንክ -የካ፲፪)

በዓላት ዐዋድያት -የሚዞሩ የሚወጡና የሚወርዱ ወደ ወደ ታች የሚሉ፤ ከነነዌ እስከ ምሕላ ድኅነት ያሉ መዞር ግን እንደ መሐረም ነው -(አዋል)

በዓል [1]-(ላት) በቁሙ፤ የደስታ የዕረፍት ቀን፤ ባመት በወር በሳምንት የሚከበር፤ ያለፈ ነገር የሚታሰብበት ተዝካር፤ ሕዝብ የበዓሉን ምስጢር እያሰበ ደስ ብሎትና ብሶ አጊጦ የሚዘፍንበት የሚዘምርበት እልል የሚልበት ብሸባ ጭብጨባ ቀኒጽ ነፈርዓጽ የሚያደርግበት፤ ሲያረግድ እስክታ ሲወርድ ባንገቱ የሚቀጭበት እንደ ጥጃ የሚፈጭበት ደምፁ እለ ይገብሩ በዓለ በሩ በዓለ በትፍሥሕት በዓሎሙ ለአእዱገ ገዳም በዓላት ሙራት። በዓለ ልደት ወበዓለ ጥምቀት በዓላት ዘርሑቅ እምጽድቅ -(መዝ -፵፩ ፻፲፯ ኢሳ፴፪ -፲፬። - -፲፫ - -፲፬ ጥበ፲፪)

 [2]-( በዓሊም ጽርእ ወዕብራ) ጣዖት ከነዓናውያን የሚያመልኩት ጌታ ማለት ነው  ተቀንየ በዓል ወሰገደ ሎቱ ወገብረ ምሥዋዐ በዓል። ተቀንየ በዓሊም ወሰገደ ሎሙ ወአምለኩ በዓሊመ -(፫ነገ -፲፮ -፴፩ -፴፪። ፳፪ -፶፬። መሳ፪ -፲፩)

[3] ( አብዕልት በዓልት ታት) ምት ባል ሚስት ያለው ወንድ የሴት ገዥ አዛዥ ጌታ ባለቤት (ዘፍ፫ ፲፮ ፩ቆሮ ፲፩ ) (ግጥም መጥፎ ሚስት) ያውና እዚያ ማዶ በግ ይነዳል ታላየ ታልሰማ ባላህያ ነው። ብእሲት በዓልተ ቤት። ንኡሳት ያውስባ ወይትዋለዳ ወይኩና በዓልታተ ቤት (፫ነገ ፲፯ ፲፯ ፩ጢሞ ፲፬)

በዓልተ ክልኤ ጸራይቅ [1]-ባለኹለት ጸሪቅ የጸናጽል ቫኵራ የሚመስል የናስ ቅጠል ያላት ከዚያ በቀር ሌላ ትርፍ ገንዘብ የሌላት ይህን ብሰጥ ምን እውጥ ሳትል ያንኑ ጨርሳ ከሙዳየ ምጽዋት ያገባች የድኻ ለጋስ ካኝ ራጥ ባልቴት -(ፊልክ -፶፬። ሉቃ፳፩ -)

[2] -በዓልተ የውሀት ወሰላም ገር ፍቅረኛ ቂም በቀል የሌላት (ፊልክ ፻፭)

በኣሲ -(ሲት ስያን ያት) የሚብስ የሚከፋ ጐጂ አስቀያሚ።

በዓታዊ -ታም ባተ መልካም፤ ወይም እግረ ደንዳና፤ ንብ እግር

(ጥት)        በኣት -(ታት) የመነኵሴ ጐሬ ዋሻ ፍርኵታ ውስጥ ያለው ቦታ ጋጥ በረት። በደብረ መቃርዮስ ኀበ ተሐንጸ በኣት በር በበአትከ ኮነ ይትፋለስ እምበኣት ውስተ በኣት ቤት -(ስንክ -የካ፭ ፊልክ -፳፬ ፶፮) በኣተ ፈያት በኣ መዛግብት፤ በኣታተ ኰኵ በኣታት መራዕይሁ፤ ዋሻ -(ኤር፮ -፲፩ ቀሌ። ኢዮ፴፱ -፳፫። ዜና -፴፪ -፳፰) ቦታ ማለት ከዚህ ወጥቷል ፈረንሳዊ የሚለውም ከዚህ ይሰማማል ዱብልንና ሴክልን ተመልከት።

()          በዓት [1]-ዋሻ ፍርኵታበዊእ ቦአ በኣት

 [2]-() በዓት ከቋንጃ እስከ ተረከዝ።

በዓዲ -(ዲት ድያን ያት) የሚለይ የሚያርቅ ባዕድ የሚያደርግ

በእንተ [1]-ዐቢይና ደቂቅ አገባብ። ስለ ነገር ምክንያት ቃለ ስኢል፤ ደስ አይበለው ብሎ፤ ደስ አይበለው ሲል ይኾናል። በኀላፊና በአርእስት በስም በግብር በቦታ ይገባል፤ በኀላፊ አንቀጽ ሲገባ ዘን በር ከፋች ያደርጋል። በእንተ ዘተወልደ እምኔሃ፤ የመሰለው ሉ፤ በእንቲኣየ እያለ ይዘረዝራል። አገባብነቱ ለክፉም ለበጎም ይኾናል፤ ለክፉ ሲኾን ላይ፤ ለበጎ ሲኾን ስለ፤ ይኸውም ራእይ ዘርእየ በእንተ ይሁዳ ወበእንተ ኢየሩሳሌም ባለው ያታወቃል -(ኢሳ፩ -) በእንተ ውእቱ ሕፃን። ወበእንተሰ ይእቲ ዕለት ነገር -(ማቴ፪ -፰። ፳፬ -፴፮) ይፀርፉ በእንቲኣክሙ። ይቀትሉክሙ በእንቲኣየ ምክንያት። በእንተ ማርያም ወላዲትከ ልመና፤ መሐላና ምጥንታ ሲኾን ግን ይኾናል። በእንተ ጸላኢ፤ ደስ አይበለው ብሎ፤ ሲል። አርእስት ሲኾን በረዥም ባጭርም ቃል፤ በምዕራፍ በክፍል፤ በተለየ አንቀጽ፤ በድርሳን በተግሣጽ ይገባል። በእንተ ሰብአ ሰገል። በእንተ እለ ተቀትሉ ሕፃናት። በእንተ ትምህርተ ኅቡኣት። አንቀጽ ቀዳማዊ በእንተ ቤተ ክር። ድርሳን በእንተ መልከ ጼዴቅ። ተግሣጽ በእንተ ከመ ኢመፍትው ይቅበጹ ተስፋ -(ማቴ። ኪዳ። -ነ። ቄር። አፈ - -) በድርድር ሲገባ፤ በእንተ ኀጢአት፤ ወበእንተ ጽድቅ፤ ወበእንተ ኵነኔ ይላል -(ዮሐ፲፮ -፲፩) ሲዘረዘር ደግሞ በበቂነት በቅጽልነት ይፈታል፤ ዘበእንቲኣሁ ቀብዐኒ፤ በርሱ ቅብነት። ዘበእንቲኣሁ ተመራሕነ፤ በርሱ መሪነት መምርነት እያሰኘ ሌላውን ኹሉ ያሳያል። የቀረ ቢኖር አገባብ ተመልከት።

 [2]-–ስለ፤እንተ -በ። አገባብ እይ -(ር፲፱ -ቍ፷፰)

በኵር -(ራት አብኳር። ዕብ ብኮር ሱር ቡክራ። ዐረ ቢክር) በቁሙ፤ መዠመሪያ ልጅ ፍሬ ቀዳማዊ ታላቅ ለቃ ሹም አንጋፋ ግንባር ቀደም ፊት የተወለደ የበሰለ መብሰል የፍሬ ነው ጭፍራ የሌለው አለቃ እንዳይባል ታናሽ ተከታይ የሌለውም ዋሕድ እንጂ በኵር አይባልም። እፎ ሐደ ወሊዳ ውእቱ ይቤ ዘበኵራአላ ስመ ወለደት ምድኅሬሁ -(ቄር) ኵሉ በኵር። በኵረ ወልድከ በኵሩ ለላሕም በኵሩ በገግ ወለአድግ ደቀቀ ዳዊት ብኳር ደምት። አብኳረ ስራኤል በኵረ በለስ። በኵራት ይሰዐሩ። ዓሥራት መበኵራት -(ዘፀ፲፩ -፭። ፳፪ -፳፰ ፴፬ -፲፱ - ዜና -፲፰ -፲፯ ክብ -ነገ ሆሴ፱ - ስንክ -ታኅ፳፰ - -፲፰)

በኵርና  ብኵርና -(ናት) በኵርነት፤ በኵር መኾን በፊት መወለድ፤ ልቅና ቅድምና። ተሣየጠ ምኔሁ ብኵርናሁ። ብፅዕናት ወብኵርናት -(ስንክ -ነሐ፳፰ ቀሌ ዕብ፲፪ -፲፮ አፈ -ድ፴፩) በብኵርና ፈንታ ያንዱን  በብዙ ብኵርናት ይላል፤ አያሰኝም አውፅኦ ሮቤል ምኍልቈ አኀዊሁ ወጸገዎ ብኵርናቶ ዮሴፍ -(ግንዘ)

በኵሕ ሖት -(በኵሐ ይበኵሕ ይብኳሕ ዕብ ፉዋሕ ያፋሕ ናፋሕ ነፍኀ) መንፋት፤ እፍ ማለት እሳትን በአፍ ወይም በወናፍ ከአፍ እሳት ማውጣት፤ ነበልባል መትፋት በምትሀት መጽሐፍ ግን በበኵሐ ፈንታ አብኵሐ ይላል፤ አያሰኝም፤ ያማርኛ ነው። -(ሕዝ፳፪ - -፳፩) ኵሎሙ ያበኵሑ እሳተ ምአፉሆሙ -(ገድ -ተክ) መለምለም መርጠብ፤ ከነፋስ ውሃ ጠል መንሣት

በኵር ሮት -(በኰረ ይበኵር ይብኵር። ዕብ ባኬር) በብኰ መበኰር መዠመሪያ መውለድ ማፍራት መውለድንና ማፍራትንመዠመር በካር መኾን። መጽሐፍ ግን በበኰረ ፈንቃ ተበኵረ ይላል አያሰኝም። ዕጐላት እለ በኵራ ባግዕ እለ ተበኵራ መካን ተበኵረት ዮሐንስሀ -(፩ነገ - -፯። ክብ -ነገ፸፫ መዋሥ)

 -በኵር ማድረግ፤ ማላቅ ማብለጥ፤ የብኵርና ክብር መስጠት ወልድየ ዘበኵርየ ማለት -(ዘፍ፳፯ -፳፬ ፵፱ -፰። ዘፀ፬ -፳፪ ዕብ፩ - -፮። መዝ፹፰ -፳፯ -፳፰)

 -ማብከር ማስታጐል ማቆም ማቋረጥ መተው መጽሐፍ ግን በበኰረ  ፈንታ ብኰረ ይላል ያማርኛ ነው። ሰማይኒ ለእ ብኰረት ዝናመ -(፪ዜና - -፳፮)

በኪክ ኮት -(በከ ይበክክ ይብክክ ዕብ ባቃቅ ዐረ በቀ በካእ) ማብከክ ማብከት ባዶ ብላሽ ንቱ ማድረግ ወይም መኾን እባክክ ማለት ዚህ የወጣ ነው መጽሐፍ ግን በበከከ ፈንታ በከየ ይላል የተሳሳተ ነው። ኢይሬኢኑ ፀሓየ ዘያበርህ ወይጠፍእ ወወርኅኒ ትበኪ -(ኢዮ፴፩ -፳፮)

በካዪ -(ዪት ይያን ያት፤ በከይት) የሚያለቅስ አልቃሽ እንብ አፍላሽ ልቅሶኛ ብፅዓን እን ተብህለት ሕዙናን ወለበካይያን -(ፊልክ -፸፬። ገድ -አዳ)

በኬሴል -(ዕብ ባሴቤል) ቤል ሸክም በሸክም በመሸከም ወይም ተሸክመው -(ነሐ፬ -፲፯)

በክ -በክት ሙቶ ያደረ ባዶ ብቻ ከን ብላሽዋዛ ፈዛዛ እንዲያው የዝም ብሎ። ኵሉ በቡ በክ ትንበ በከ ነበሩ ስራኤል በበክ ብድ ያፈደፍድ ቢበ በክ በክ በከመ ትሬእይዎ ዝንቱ ኅብስት -(ሔኖ፸፫ -፭። ቆሮ - -፲፩ ስንክ -የካ፳፮ ሆሴ፫ -፬። መክ፪ -፲፭ ቅዳ -ሕር)

በክይ ዮት -(በከየ ይበኪ ይብኪ ዕብ ባካ ሱር ብካ ዐረ በከ) ማልቀስ እንብ ማፍሰስ ዋይ ማለት መጮኽ መንሰቅሰቅ ደገት በክየ ብክዮ ዘሞተ ይበክይዎሙ በእንተ ኵሉ ምንዱብ በኪ -(ጦቢ፮ - ራ፳፪ -፲፩ ኤር፰ - ኢዮ፴ -፳፭)

በኳሪ -(ሪት ርያን ያት) በካር ዠማሪ፤ በኵር አድራጊ፤ አስታጓይ

በዊሕ ሖት -(ቦሐ ይበውሕ ይባሕ። ዐረ ባሐ) መታየት መገለጥ፤ መጕላት ብሩህ ጽዱል ጸዐዳ መኾን ኖራ በረቅ ብሕካ መምሰል ቡሔ ቡሓ ብሓ ማለት ከዚህ የወጣ ው። መሠልጠን፤ ሹመት መብት ማግኘት ፈቃድ ሥልጣን መቀበል ከበላዩ። ብሕተን ተመልከት የዚህ መንቲያ ነው

በዊእ ኦት -(ቦአ ይበውእ ይባእ ዕብ ቦእ። ዐረ ባእ) መግባት፤ መከተት ጥልቅ ስምጥ ማለት ማደር ወደ ውስጥ ማለፍ መኼድ ውሳጣዊ ማእከላዊ መኾን ቦአ ቤቶ ባኡ ሀገረ። ባእ ውስተ ታቦት ትባኢ ውስተ ራህተ ባዕድ -(ዳን፪ -፲፯ ኤር፬ -፭። ዘፍ፯ -፩። ሩት፪ -) በቦ ፈንታ ተባውአ ይላል፤ ስሕተት ነው -(ሮሜ፭ -፳። ገላ፪ -፬። ፪ጢሞ - -) በዊእና በዪት አንድ ሥር ናቸው

በዊዝ ዞት (ቦዘ ይበውዝ ይቡዝ) መቦዝ ፤ መፍዘዝ መቦዘን መስነፍ

በዋኢ -(ኢት እያን ያት) የሚገባ ገቢ መጪ። ጽፉቅ በዋኤ ቤታ ብዙኅ በዋኢቱ በእንተ ብዝኀ በዋእያን ወወፃእያን -(ምሳ፳፱ -፴፭ ሢራ፵፪ -፮። ፊልክ - -፳፪)

በዘ [1]-(ዐቢይ አገባብ) ፍችው ገንዘብ ምስጢሩ እንደ ንድ። በኀላፊና በትንቢት ይገባል በዘወድአ ሞት በዘቀነዮሙ ሞት ሞት ኹሉን በጨረሰ ገንዘብ፤ በገዛቸው ገንዘብ። ወትሜህር በዘታስሕቶሙ፤ በምታስታቸው ገንዘብ ገብሩ በዘያምዕዑኒ በሚያሳዝኑኝ ገንዝብ። በምስጢር እንጂ በንባብ እንደና ስለ ሲኾን ምስክር የለውም። በርሥኣኑ እንዘ አል በማለት ፈንታ በዘረሥአ በዘአልቦ እያለ ይገኛል፤ የመላሽ ሕተት ነው -(ዘፍ፳፬ -፴፮። -፲፭)

 [2]-( ) በቁም ቀሪ ቅጽልና በቂ ወይም የዘርፍ ደፊ ይኾናል ምንት ትትናገር በዘይሰምዑ ሕዝብ ሚሰሙት ቋንቋ በዘርእየ ወበዘሰምዐ ሰማዕተ ከውን ባየው በሰማው ነገር፤ እንደ ፊተኛውም ባየ በሰማ ገንዘብ ያሰኛል ምስጢሩ እንዳየ እንደ ሰማ መጠን፤ ስላየ ስለ ሰማ ያየውን የሰማውን፤ አይቶ ምቶ ማለት ነው ይህ ኹሉ የበን አፈታት ያሳያል በዘአዶኒራም ዕፅ ወበዘአቤሴሎም ብን፤ ባዶኒራም ዕንጨት ባቤሴሎም ደንጊያ፤ በቁም ቀሪና ደፊ። አንዳንድ ጊዜም ቅጽል ሲኾን አዳማቂ ኹኖ ይቀራል። ነሥአ ይፈ ዘይቀትል ልብስ በዘያስተባሪ ምክንያት በዘያስተዋርድ በንና ዘን ተመልከት -(ዕር፲፱ -ቍ፸፬)

በዚኅ ኆት -(በዝኀ ይበዝኅ ይብዛኅ) መብዛት መርባት መበርከት መውለድ መክበድ መፈድፈድ ማየል መበርታት -(ዘፍ፯ -፳፪ -፳፰ -፲፯ ዘፀ፩ -) ደንዐ ማይ ወበዝኀ በዝኀ ድምፀ ሁከት -(ዘፍ፯ -፲፰ -፲፱ ነገ -፲፬ -፲፱)

በዚዝ ዞት -(በዘ ይበዝዝ ይብዝዝ ዐረ ዕብ ባዛዝ) መዛት፤ መንዛት።

በዛቲ -(ቲት ትያን ያት) የሚያባዝት አባዛች፤ እጀ ሥራ አግቢ

በዝበዘ -(ዕብ ባዝቤዝ) በቁሙ በዘበዘ ዘረፈ ቀማ በረበረ በተነ፤ መነዘረ ባከነ በከንቱ። ዐማ ነቀፈ ደበ አዋረደ ናቀ አቃለለ

በዝቶ ቶት -(በዘተ ይቤዝት ይበዝት) ማባዘት፤ መፈልቀቅ ማፍታታት መንቀስ እጀ ሥራ ማግባት ለመፍተል እንዘ ትቤዝት ፀምረ -(ምሳ፳፱ -፴፩)

በዪል ሎት -(ቤለ ይበይል ይቢል ወይም ቤለ ይቤ ይበል። ዐረ ቃል። ዕብ ንኡም፤ አማር) ማለት መንገር መናገር ፍሬ ቃል መስጠት ማስማት በአፍ በመጽሐፍ መንበብ፤ ማንበብ። ብሂል ነገር ይኾናል፤ ንቀጽና አገባብ በአንቀጽንቱ ኣንቀጽ ይስባል ስም ይተረጕማል። ባገባብነቱ ማሰሪያ ያስቀራል አገባቡን ባገባብ ተመልከት ብሂለ ይብሉ ስመ ዴቅ ብሂል ጽድቅ ብሂል ብህለ ካልአ በከመ ብህልከ ዘብህልዎ በዊነ። ዊነ ውላጤ ዘብህሎ ቅዱስ ወግሪስ። እሳት እንተ ብህላ እግዚእነ -(ኤር፴፰ -፳፪። አፈ -ድ፲፪ ዋል። አረጋ) መሐለነ እይ የዚህ መንቲያ ነው ብህለና የክህለ አካኼድ ንድ ስለ ኾነ በካልኣያቸው እየታጣ በሣልሳያቸው ይገኛል፤ ባላገባቦች ግን ብህለን ክህለ ለይተው ይብህል ይሉታል፤ አያሰኝም። ፪ኛም በበዪል አካኼድ እንደ ሐባብና እንዳሮጌው ግእዝ ቤለ ይበይል ይቢል ወይም ቤለ ይቤ ይበል በማለት ፈንታ ብህለንና ቤለን አዛንቀው ቤለን አውጥተው በርሱ ፈንታ ይቤን አግብተው የብህለን ካልኣይ ይብልን ለይቤ ሰጥተው፤ ይቤ ይብል ይበል እያሉ አለመንገዱ ያረቡታል።መጻሕፍትም ከዚ የተነሣ በቤለ ፈንታ ይቤ ይብል ይበል ሲሉ እንጂ በብሂል አካኼድ ብህለ ብለው ይብህል ሲሉ አይገኙም። ሀሎ የሀለወ ፋይ መንቲያው ወንድሙ እንደ ኾነ ይቤም ከበዪ የወጣ፤ የቤለ ካልኣይ የይበይል ድርብ ወይም መንቲያ ትንቢት አንቀጽ ሲኾን፤ መምህራን አርእስትና ዘር ዝና ቅጽል የለውም ባር አንቀጽ ነው ብለው እኩሌቶቹም ብህለ ድርብ ነው ብለው ቀዳማይ አንቀጽ ማድረጋቸው ትንቢትነቱ ላልታወቀ ነው። በኃምስ መጕረዱም በመካከሉ ስላለበት ነው ኛም ለን የሚሉ ዎች የለ ጸያፎች፤ ብህለን ሲያረቡ ብህየ ይብይ ይበይ ይላሉና በጸያፍ አንደበት የገባ ነው ልንል እንችላለን ይብልን ይብይ እንደሚሉት፤ ይብይን ደግሞ ይቤ ብለውት ይኾናል፤ አልዚያስ ኃምስ ጐርድ ባልተገኘም። በጸያፍ አንደበት መለወጥም የግስ ልማድ ነው ረን የሚሉ ዎች የረ ጸያፎች በሐረረ ፈንታ ሐለለ ብለው ኹለተኛ አንቀጽ እንዳወጡ ባማርኛም ለን ይወርሰዋል ይልቁንም በሣልስ ቅጽል። ቀታሊ ሃሊ ሐባሊ ጠንቋሊ ገዳይ ቻይ ባይ ጠንቋይ የመሰለው ኹሉ ጐራጅነቱም ለሩቅ ወንድና ሴት ለቅርድቡ ወንድና ለአነ ንሕነ ነዚህ ላምስቱ ብቻ ነው ይህም ቤለ ይቤ ይበል ቤለት ትቤ ትበል ቤልከ ትቤ በል ቤልኩ በል። ቤልነ በል እያለ መኼዱን ያሳያል በቀሩት ግን ምስቱ ራዊት ቤሉ ቤሉ ይበሉ ቤላ ይቤላ ይበላ ቤልኪ ትቤሊ በሊ። ቤልክሙ ትቤሉ በሉ ቤልክን ትቤላ በላ እያለ ዘሩን ልን መስሎ ተካክሎ ዳል። የበ ዘርና የቤለ ካልኣይ የይበይል ወንድም ፍጹም ቢት አንቀጽ መኾኑ ነባር ቀዳማይ አለመኾኑ በ፫ ምስክር ይረዳል መዠመሪያ በሣልሳዩና ባምስቱ ራዊት ለን እየጨመረ መኼዱ ፈጽሞ ባለመጕረዱ። ኹለተኛ የትንቢት አሥራው መነሾቹ ፊደሎች የተአነ ብቻ ናቸውና ይቤ ትቤ እያለ በነዚህ ባራቱ በመኼዱ። ሦስተኛ፤ ለነባር አንቀጽ ካልኣይ ልሳይ የለውምና በዘንዱና ትእዛዙ ይታወቃል። አስተውል ነባር ቀዳማይ ወይም ትእዛዝ አንቀጽ ኹኖ ቢኾን መንገዱ እንደ ሀብና እንደ ነዐ ነበር ሀብና ነዐ ሥርወ ቀለሙን ሳይለውጥ በጫፉ ሌላ ባዕድ ፊደል ሳይጨምር ሀብ ንዑ ንዒ ተብሎ ባራት ቅርቦች ብቻ እንዲረባ ይቤም ሥርወ ቀለሙን ሳይለውጥ ለን ቤለ ከብህለ ሳይቀላውጥ ባራት ራዊት በሩቆች ብቻ ይቤ ይቡ ይቢ ይባ ተብሎ ተረባ ነበር። የብሂል አፈታት ጓዙ ብዙ ውና የቀረውን በርባ ቅምርና ባገባብ በሠምና ወርቅ ተመልከት -(፪ኛና -፲፱ኛ -፳፪ኛ -ዕር። ፳፬ -፹፫ -፻፳፭ቍ)

በዪት ቶት -(ቤተ ይበይት ይቢት ሱር ቡት ባት ዐረ ባተ) ማደር ባሉበት ቦታ ከሠርክ እስከ ነግህ መቈየት የትም ውሎ ቤት መመለስ፤ መግባት መክተት ከሰ መጠጋት። መኖር፤ ባንድ አገር መወሰን፤ መያዝ ቤት መሥራት አጽንዖ በኣት። ቤትኩ ወወዐልኩ እንዘ ጸብት ቤቱ ክልኤሆሙ በይእቲ ሌሊት። ትበይት ሌሊተ ውስተ ልቦ ብረት ዘኀበ መስዮ ይበይት። ኀቤየ ትበይት ዮም ዐደረ ተኛ -(፪ቆሮ -፲፩ -፳፭ ጦቢ፰ -፱። ኢሳ፳፩ -፲፫ ሢራ፴፮ -፴፩። ዘፍ፴ -፲፮) ይበይት ውስተ በኣታተ ኰኵ ጸጋሁ ፈጥረ ኵሉ ወበኂሩቱ ይበይት ኖረ -(ኢዮ፴፬ -፳፯ -፳፰ ቅዳ -ግሩ)

በዪጽ ጾት -(ቤጸ ይበይጽ ይቢጽ ባጻዕ ዐረ በፀዐ) መለየት መምረጥ፤ አስተካክሎ መቍረጥ። ወቤጸ ያዕቆብ ባግዒሁ በይጽ ምውስቴትክሙ ኃጥኣነ ዘይበይጽ በከናፍሪሁ ኩየ ለየ -(ዘፍ፵ -፵። ሕዝ፳ -፴፰ ምሳ፲፮ -)

 -መንጣት መገርጣት ብጭጭ ማለት ዕንቍላል ወይም የበሰለ ቅጠል መምሰል።

በያቲ -(ቲት ትያን ያት) የሚያድር ዐዳሪ ነዋሪ ቤት ሠሪ

በያኒ -(ኒት ንያን ያት) የሚበይን በያኝ፤ ዐዋቂ ፈራጅ አስተዋይ፤ ዳኛ መምር

በያጺ -(ጺት ጽያን ያት) የሚለይ መራጭ፤ ቈራጭ

በይረሙን -( -(ዐረ በይራም) ቅድሳት ዕለ ቅድሳት፤ አስተርእዮ ጥምቀት -(ስንክ -ጥቅ፲)

በይነ -(በይን ዕብ ቤን ሱር ባይናይ ዐረ በይነ ማእከል) ዐቢይና ደቂቅ አገባብ ስለ ምክንያት ዐቢይ ሲኾን ዘን በር ፋች ድርጎ ተሰብአ በይነ ዘአፍቀረ ሰበአ ተቀብዐ በይነ ዘተሰብአ ተሰምየ መሲሐ በይነ ዘተቀብዐ እያለ ይገባል -(ዕር፲፱ -ቍ፷፰) ደቂቅ ኾን እንደ ቤዛ በብትን ይገባል፤ በይነ ምንት ስለ ምን ምን ምክንያት በይኑ ይና በይንከ ክሙ ክን እያለ ይዘረዝራል

በይኑ -ለሊሁ ብቻው ርሱ ራሱ ባለቤቱ

በይናት -ኹለት ወገን፤ ኹለት ክፍል ጥንድ፤ ዘውግ መንታ እንደ እጅና እግር ያሉ ተባባሮች ተነጻጻሮች ተመሳሳዮች።

በይን -ብቻ ርስ ራስ ባለቤት እኔ የሚል የተለየ አካል -ወገን -ክፍል ፈርጅ ነጠላ ቀንጃ።

()          በይኖ ኖት -(በየነ ይቤይን ይበይን ዐረ ባነ ዕብ ባን) መበየን መለየት መምረጥ ማስተዋል መመልከት ለይቶ ማወቅ መረዳት አስተውሎ መፍረድ። ይቤይንዎሙ ወያነጽሕዎሙ ምንት ትቤይን ምውስቴቶን እለ የዐብያሆን ወሠርዌ ዘውስተ ዐይንከ ትቤይን ይቤይኖ ኃጥእ እንበለ ይግበር ኀጢአ -(ዳን፲፪ - ሄርማ ማቴ፯ -፫። ቅዳ -ኤጲ) በይኖ ፈንታ አበይኖ ይላል፤ አያሰኝም። ሕቱ በአበይኖ -(ቅዳ -ት። ፩ቆሮ -፲፬ -፲፮)

በደለ -(ትግሬ ወዐረ) ለወጠ ቀየረ። -(ዐማርኛ) በቁሙ በደለኛ ኾነ በመልካም ፈንታ ክፉ ሠራ ምስጢሩ ከዚያው ይገባል

በደዶ -ፈንጣጣ፤ ኩፍኝ ልዩ ብቸኛ በሽታ የሚገድል የሚያቈስል ፊት የሚነቍር ይን የሚያሳውር የዕከክ ይነት ሕማመ ደዶ -(አዋል)

በዲር ሮት -(በደረ ይበድር ይብድር። ዐረ በደረ ረጠ። ዕብ ባዴር በተነ) መሮጥ መፍጠን መንገድን በሩጫ መቍረጥ። ከዚህ የተነሣ መቅደም ልፎ መኼድ ፊተኛ መኾን ይበድሩ እምተኵላተ ረብ ይበድሩ ምአንስርት ፍራሲሆሙ። ከመ ይብድር ምረዋጺ ሮጠ ፈጠነ -(ዕንባ፩ -፰። ኤር፬ -፲፫ ቅዳ -ዮሐ) ሕቀ በደሩክሙ ትበድር ይእቲ ወትመውእ ለከ ጸላኢከ ብድሮሙ ተንሥእ ይበድረኒ ኀበ ገነት። በደሮ ጴጥሮስ በጺሐ መቃብር ቀደመ -(፪ነገ -፲፯ - ራ፳፱ -፲፫ ፴፬ -፳፩ ፊልክ -፫። ዮሐ፳ -)

 -ማበደር ማለቃት፤ አስቀድሞ መስጠት ኋላ ለመቀበል -(ዐማርኛ)

 -መውደድ፤ መምረጥ፤ ማክበር ማብለጥ። ኢኮነ ዘበደረ ወለዘሮጸ -(ሮሜ፱ -፲፮) መጽሐፍ ግን በበደረ ፈንታ ብደረ ይላል፤ አያሰኝም። እመ ብደሩ ዘአነ እፈቅድ ምጽዋተ በድር መሥዋዕት ብደሩ ሞተ ምሕይወት። አብደረ ይሕምም ምስለ ሕዝቡ ዘያበድር ርእሶ እምነ እግዚኡ ስመ ኀረያ እግ ወአብደራ -(ኢሳ፶፭ -፬። ሆሴ፮ -፮። ኤር - - ዕብ፲፩ -፳፭። ዲድ -፳፭። መዝ -፻፴፩)

በዲቅ -(በደቀ። ዕብ ባዳቅ) ማደስ መጠገን። እስከ ማእዜኑ ትቤድቁ ቤቶ ለእግ -( - - -ገ፺)

በዲን ኖት -(በድነ በደነ ይበድን ይብድን) መብደን መፍዘዝ መሞት መገነዝ፤ መኾን መግማት መበስበስ መፍረስ ሥጋ ትበድን በንዋም ዘምዉት ነፍስት ፀአተ ነፍስ ይበድን -(መጽ -ምስ)

በዲው ዎት -(በድወ ይበዱ ይብዱ ትግ በድዐ በዳ) መውደም መጥፋት መፈታት፤ መፍረስ መደምሰስ ውድማ ረሓ ባዶ ባድማ ምድረ ባዳ መኾን ያገር የመዲና የድንግል ምድርክሙኒ በደ በድወት የሩሳሌም ንኅለት ወበድወት ብያቲሆሙ ድዋ ወተመዝበራ -(ኢሳ፩ -፯። ስንክ -የካ፩ አቡሻ -)

በዲድ ዶት -(በደ በደደ ይበድድ ይብድድ። ዕብ ባዳድ) ለየ ነጠለ ብቻ አስቀረ ብቸኛ አደረገ በድበደ በዲድ በደ ካለው የወጣ ነው -(ዲቃላ -ግስ)

በዳ -ዝኒ ማሁ ትሑር ፍኖተ በዳ ትከውን ምድረ ግብጽ በዳ ወበድወ -(ሢራ፴ - ሕዝ፳፱ -)

በዳሪ -(ሪት ርያን ያት፤ በደርት) የሚሮጥ፤ የሚቀድም ሯጭ መንገድ ራጭ

በድራ -(ዐረ በድረት) ሚዛን የሚዛን ስም ጥሩና ልኩ በየሀገሩ ይለያያል እልፍ ድሪም ቪሕ ድሪም ቪሕ ይሉታል ርግጡ ኣልተገኘም። ሺሕ ማለት ይለያል እንጂ ሺሕ ማለትና እልፍ ማለት ሊታረቅ ይችላል እልፍን መልከት። ኹለተኛም በድራ ማለት ብድር ማለት ይሰማማል። ወወሀቦሙ ሠለስተ ምእተ በድራ ወርቅ -(ዮሴፍ)

በድር -ቅድድም ፍክክር ሩጫ ፍጥነት፤ መልካም ሥራ ገድል ሩፋት። በድርየኒ ፈጸምኩ ፈጸመ ድሮ ሠናየ። -(፪ጢሞ - -፯። ስንክ -ታኅ፲፬ ጥር፲፬ -፳። የካ፱ ግን፱)

 -የጾመ አይሁድ ድሮ ቅበላ ጹመው ሚውሉበት ጾማቸው ቀን የሚቀድም ዋዜማ ድራር ማታ የሚዠመር። ይኸውም የጥቅምት ጨረቃ በበቀለች በ፱ ቀን ነው -(ዘሌ፳፫ -፳፯፴፪) ወጾመ ቢድሮሙ በእንተ ያዕቆብ -(መጽ -ምስ)

በድበደ -(በድወ። ዐረ ባደ) መመ ሞተ ጠፋ ተበላሸ ዛገ መረተ። ወርቆሙኒ በድበደ -(ሆሴ፱ -) አብደን ተመልከት የዚህ ጎር ነው። ትግሬ ግን በድበደ ብሎ ደበ አዋረደ ይላል

በድን -( አብድንት) በቁሙ ሙት ሳ፤ ነፍስ የተለየችው የማይላወስ የማይንቀሳቀስ የፈዘዘ የተገነዘ ባዶ ሥጋ፤ አስክሬን። ዘአንሥአ ድነ ምነ ሙታን። መዊቶሂ ተነበየ ድኑ አልቦ ቤት ዘአልቦ ድን ውስቴታ። በዝኃ ብድንቲሆሙ ወተንሥኡ ብዙኃን ብድንቲሆሙ ጻድቃን -(ሢራ፵፰ - -፲፫ ኩፋ -፵፱። ኢሳ፭ -፲፫ ማቴ፳፯ -፶፪)

በድው -ምድረ በዳ ውድማ ባድማ ደረቅ በረሓ ባዶ በድወ ፋራን በምድረ በድው ልቦ ወማይ። ባሕር ድወ ይመስሎ ድወ ትከውን ኵላ ምድር ድው ውእቱ ምሰብ ወእንስሳ -(ኩፋ -፲፯ መዝ -፷፪። ኢዮ፵፩ -፳፪ ኤር፬ -፳፯ -)

በገነ -(ዕብ ናጌን) ቃኘ ነዘረ፤ መታ ደረደረ የንዋየ ማሕሌት። ሲጠብቅ ግን ነደደ ተቈጣ ያሰኛል።

በገና -በቁሙ፤ መዝሙር -(ዐማርኛ)

በገን -(ትግሬ) ጨብጥ የሽንት ምጥ ፀበጠን ተመልከት።

በጊር ሮት -(በገረ ይበግር ይብግር። ዕብ ባጋር) ማደግ መጐልመስ ልጅነት ወዳዋቂነቅ መውጣት ታላላቆች መጨመር፤ ብሮ መቈጠር አቶ እገሌ መባል በቁሙ መበገር መሞከር መንደፍ የሥዕል ብግር ማውጣት ብግራም መኾን ብግር ወገን ነው፤ የውርዛዌና የደዌ

በግዕ -(ዕት። ዕብ ባግ) የምግብ ክፍል ዕድል ፈንታ ድርሻ መቍነን ድርጎ በቁሙ ተባት በግ የክርስቶስና የውነተኛ ክርስቲያን ምላሌ በጎ ማለት ከዚ ወጥቷል በግ ዘተኀጥአ ወመጽአ ይጠባሕ በግዕ ሐቲ በግዕት -(ኢሳ፲፫ -፲፬ ፶፫፤ ፯። ሕዝ፵ -፲፭ - -)

በግዖ ዖት -(በግዐ ይቤግ ይበግ) በጋ መንጋ መኾን መንጋጋት ወደ ወሰዱት መኼድ መነዳት በጋ የጊዜ የወራት መንጋ የሰው የከብት ምስጢሩ ግን በጎነትና ቅንነት መሥዋዕትነት፤ እንደ ይሥሐቅ እንደ ዮፍታሔ ልጅ።

()          በጢሕ -(ሓት ዐረ በጢኅ) በቁሙ የዱባ ዐይነት ተክል ውስጠ ቀይ ክብ እንክብል ማር ማር የሚል በጥተው ይተው የሚገዙት በምጥዋ ብርጭቅ ይባላል

በጢሕ ሖት -(በጥሐ ይበጥሕ ይብጣሕ ዕብ ባጻዕ ሱር ብዛዕ ዐረ እበፀዐ) ብጣት መፍታት፤ መተፍተፍ መሠንበጥ ለፈውስ ወይም ለጌጥ። -(ተረት) ሲያጌጡ ይመላለጡ። ጠቢባን ሶበ ይበጥሑ በጽኑዕ እስከ ይረክብዎ ሕማም ይጠበቡ ሶቤሃ ዘያዐርፍዎ ለሕሙም ምተሀውኮ ወእምድንጋፄ ፍስ ወኢይበጥሑ መ፤ አላ ይወድ ፈውሰ። መጠነ ይጼዐሉ እለ ይበጥሑ እምእለ ይበጥሕዎሙ። ኢትብጥሑ ሥጋክሙ -(አፈ -ተ፴። ሌ፳፩ -)

በጢል ሎት -(በጠለ ይበጥል ይብጥል። ዕብ ባጣል። ሱር ቤጤል። ዐረ በጠለ) መቦዘን ማረፍ፤ መስነፍ ሥራ መፍታት መጥፋት መፍረስ መሻር መቅረት፤ ንቱ ብላሽ መኾን። ኢበጠለ ጸልዕ አላ ጸናዐ። በጠለት ትንቢት በስብከተ ሐዋርያት። ትበጥል እን መከርኩ። በጠለ ዐቂበ ትአዛዝ ምኔየ በጠለ ተአምኖቱ ቦቱ። ዘስሕተታት በጠላ በትእዛዝከ -(መጽ -ምስ ክብ -ነገአርጋ -፭። - -፵፱ -፫። ኪዳ) በበጠለ ፈንታ ተበጥለ ይላል፤ አያሰኝም። እመ ትትቤጠል ሪት በሃይማኖት -(ቄር ገድ -አዳ)

በጢስ ሶት -(በጠሰ ይበጥስ ይብጥስ) መበጠስ መበጣጠስ፤ መቍረጥ መቈጥቈጥ፤ የቅጠል የዐጽቅ።

በጢር -(በጠረ ይበጥር ይብጥር) መበጠር ማበጠር፤ ማንጠርጠር ማንፈስ መንቀስ የእኽል የጠጕር የነገር። ከግእዝ ወዳማርኛ ስለ ባለቅኔዎች አይገሱትም።

በጢጥ ጦት -(በጠ ይበጥጥ ይብጥጥ) መበጠጥ በጠጥ ፋንድያ መጣል፤ ባጥ እንጣጥ ማለት ለመራገጥ የእንስሳ መዝለል ጮቤ መምታት መራገጥ የጐበዛዝት በጥ ለጥ ሰጥ ብሎ በልብ መተኛት ዠርባን ለገራፊና ለረጋጭ አስመችቶ መስጠት ትግሬ በጥ በል ማራ ውደቅ ወይም ጣለው እንዲል

በጣሒ (ሒት ሕያን ያት) የሚበጣ በጭ በጪ በጣሕያን (አፈ ተ፴)

በጣሊ -(ሊት ልያን ያት በጠልት) የሚጠፋ ጠፊ፤ ፈራሽ ቀሪ ላፊ። መንግሥተ ምድር በጣሊ መርዓ በጣሊ -(ስንክ -ሐም፰። መስ፳፯)

በጣጣ በጣጥስ -(ዐረብ) ድንች የድንች ወገን

በጥሐ -(ዕብ ባጣሕ) እመነ ተወከለ ተስፋ አደረገ ዐረፈ ተዘለለ፤ ገላውን ደደ ምን አለብ አለ፤ የድውይ የባለጤና።

በጥሪቃ -(ሮማ ፓትሪሺያ። ዐረ በጥሪቀት) ታላቅ ወይዘሮ ባላባት የነገሥታት ወገን ልዕልት እግዝእት ዛቲ ይእቲ ቀዳሚት በጥሪቃ ዘሀገረ ስጥንጥንያ -(አዋል። ገድ -ዳን)

በጥበጠ -ቁሙ በጠበጠ ጣለ የኮሶ የድፍድፍ የጠጅ። ጥሕለን ተመልከት። ለቤተ ክሲያንም ይኾናል። ደብረ በጥብጥ እንዲሉ።

በጸል -(ዐረ በጸል። ዕብ ባጻል ቤጽላ) ቀይ ሽንኵርት የቀይ ንኵርት ይነት የሚላጥ የሚመለጥ ኹለንተናው ተልጦ የሚያልቅ የሚሸለቀቅ ኢይባርኩ ላዕለ በጸል -( - -፲፯)

በጸወ -አንቀላፋበፀወ

በጺሕ ሖት -(በጽሐ ይበጽሕ ይብጻሕ። መጽአ ለጸቀ) መድረስ መምጣት መቅረብ መለጠቅ መንካት፤ ማግኘት የእጅና የእግር የራስ የመሌሊት። ኑኁ በጽሐ ሰማየ። ዘእንበለ ይብጽሑ ምድረ በጽሐ ብርሃንኪ ዘበጽሐ ምኤዶም በጽሐ ማኅፈርነ ይበጽሕ ደመናተ ርእሱ ጽሐቶሙ ምሳል ዘመሰሉ ዘበጽሐ ምትድምርት -(ዳን፬ -፲፯ -፳፬ ኢሳ፷ -፩። ፷፫ -፩። ራ፳፱ -፳፯። ሕዝ፴፩ -፫። ጴጥ - -፳፪ አቡሻ -)

 -ማደግ መጐልመስ፤ አካለ መጠን ማድረስ መኾን መደረግ፤ መምላት መፈጸም መጨረስ የትንቢት የዘመን መርታት ድል መንሣት፤ የውጊያ የሙግት። እምከመ በጽሐ ቃሉ ወኢኮነ በከመ ይቤ። በጽሐ በከመ ነገ ከመ ይብጻሕ ቃለ ቢያት። ዳዊትሰ ህቀ ወበጽሐ መዋዕሊሁ፤ መላ ተፈጸመ -(ዘዳ፲፰ - ኩፋ -፵። ማቴ፳፮ -፶፮። ፳፯ ፩ዜና -፳፫ -) ጌጋይ በዘኢይክሉ በጺሖቶ ልቦ ኩይ ዘበጽሑ ሎቱ። ረታ -(ግብ፳፭ - -፲፰)

 -መውጣት፤ ተለይቶ መያዝ ሰጠት፤ የዕፃ የሹመት የርስት የቦታ የመሰለው ኹሉ። ወበጽሐ ዕፃ ዕለ በትረ ብንያም -(፩ነገ - - -፳፩ ፲፬ -፵፩። ኢያ፲፰ -፲፩ ፲፬ -) ለከ ይበጽሐከ ርስታ፤ መክፈልት ቡርክት በጽሐት ለሴም -(ጦቢ፯ -፲፪ ኩፋ -)

በጺል ሎት -(በጸለ ይቤጽል ይብጽል ዐረ በጸለ። ዕብ ፋጼል) መላጥ መምለጥ መቅረፍ መሸልቀቅ መግፈፍ መገሽለጥ መበጨቅ መጋጥ መንጨት፤ መሳብ መጐተት ከለባት ይቤጽልዎሙ -(ኤር፲፭ -)

በፂዕ ዖት -(በፅዐ ይበፅዕ ይብፃዕ ዕብ ባፃዕ ዐረ -በፀዐ ቤጸ) መቍረጥ መወሰን መገምገም መገመት ይህን ያኽል ማለት የዋጋ የስለት። በቁሙ መብፃት ብፃዐት መግባት በገንዘብ በመሷዕት ወይም በራስ በሰውነት መሳል ይህን እሰጣለኹ እንዲህ አደርጋለኹ ማለት ከዚያ በኋላ ንደ ውሉ ራስን ገንዘብን መቀደስ መለየት ለባለቤቱ ማቅረብ መስጠት፤ የተናገሩትን መፈጸም። ይበፅዕ ካህን ወበከመ በፅዖ ማሁ ይከውን ወእመ በፅዐ ብእሲ ቤቶ ለእግ ወቀደሳ ዘበፅዐ ብፅዐተ በፃዕከ ብፅዐተ። እንበል ትብፃዕ ስተዳሉ ብፅዐቲከ በፃዕኩ ለኢየሩሳሌም። በፃዕነ ንጹም በፃዕከ ትሕንጽ ብእሲት ዘበፅዐት ከመ ትትወሰብ ዘበፅዐት ርእሳ ለእግዚአብሔር -(ዘሌ፳፯ - -፲፬ ዘፀ፴፭ -፳፬ ዘፍ፴፩ -፲፫። ራ፲፰ -፳፫ መዝ -፻፴፮ ፩ዕ - -፵፱። -፵፭። - - -፲፮ -፲፪)

በፂው ዎት -(በፀወ ይበፁ ይብፁ ዕብ ባጤእ፤ ነበበ ዐረ በጡአ፤ ኖመ) ማሸለብ ማንቀላፋት፤ መተኛት መጋደም ብሎ መዘርጋት። መቃዠት መቀባጠር መጫዎት ማቧለት ያልኾነ ነገር መናገር። ብላዕ ዕረ ወልበስ ሣዕረ ወብፁ ዲበ ዕር -(ፊልክ -፸፮) ነፀወን እይ የዚህ መንቲያ ነው።

በጻሒ -(ሒት ሕያን ያት) የሚደርስ ደራሽ መጪበጻሕያን ብጽሐቶሙ -(ግንዘ)

በጼቃ -(ዐረ ቡጻቅ ዕብ ባጼቅ ሊጥ ቡሖ) ነጭ ደንጊያ በረቅ ብሓ ብሕካ መኔ ኖራ የሚመስል። ከመ ርእየተእ በጼቃ -(አዋል) ባዜቃን ተመልከት፤ የዚህ ሞክሼ ነው።

በጽሒ -(ትግሬ) ዝኒ ከማሁ ውርዝው ወሬዛ ሕፃን ብጹሐ አምጣን

በጽዐ -ብጽዐት ገባበፂዕ በፅዐ

ቡሩክ -(ካን ካት ርክት) ቁሙ የተባረ የተመስገነ ክቡር ምስጉን ምሩቅ ሙሴ ዘቡሩክ ዝክሩ። ቡሩክ አን ምላክነ ቡርክት አንቲ ምአንስት ወቡሩክ ፍሬ ርሥኪ ቅብዕ ቡሩክ ቅዱስ -(ሢራ፵፭ - ዮዲ፲፫ -፲፯ ሉቃ፩ -፵፪። ዘፀ፳፱ -፳፩)

ቡራት ቡራቴ -(ጽር ብራቲ። ዕብ ብሮት) ስመ ብርቱ ጠንካራ ዕንጨት የጥድ የዶቅማ ዐይነት እንዳዝጋሮ ያለ ምዑዝ ዐዚዝ። ወይም ርሲው ራሱ ጥዱ ቅማው ቤሩሽን እይ ዕብራይስጡ ብሮሽን ሲያበዛ ብሮት ይላልና ቡራቴ ውስጠ ብዙ ነው ምስጢሩም ብሩርና ብርት ይሰማማል።

ቡራኬ -(ክያት) ቢና ጥሬ ዘር መባረክ -(ጥባ) መባረክ አበራረክ፤ በቁሙ ቡራኬ፤ ምስጋና ምርቃት። ባር አባ ወልድ ዝኬ እስመ ልማዱ፤ ለመምህር ቡራኬ ጸሎተ ቡራኬ። ቡራኬሁ ለሴ ቡራኬ ወመርገም ጽናስ ኮነ መርገመ ወብዕልሰ ኮነ ቡራኬ -(ደራሲ ቅዳ። ያዕ፫ -፲። አፈ -ተ፲፰)

 -የመክፈልት ወግ ታላቅ ዕድል ለባለወጎች የሚሰጥ። እሊሁም መሪጌታና ቄስ ቃቢ ናቸው

ቡቅ -( አብዋቅ) ቀንዳ መለከት ሥሥ ውስጠ ክፍት ወይትነፋኅ ቀርን ወብዕዛት ወአብዋቅ -(ሥር -አኵ) አንቦቀቦቀ ተንቦቀቦቀ ቦቅቧቃ ማለት ዚህ ወጥቷል

()          ቡባ -አሻነጕሊት በወንድ ወይም በሴት ልጅ አምሳል የሚሠራ የልጅ የሕፃን መጫዎቻ ልጅን ልዘልኽ ሲሉ እንቡ እንቡቡ ማለት ዚህ የወጣ ነው።

ቡአት በአት -መግባት፤ አገባብ መባት፤ አባባት በበአትከ ወበፀአትከ በአተነ ወፀአተነ በሰላም ቀብ ጥንት ወበአት ውስተ ትሥጉት ዛቲ ዕለት ኮነ በአቱ ውስተ ቤተ መቅደስ። በአተ ረምት። በአተ ሰንበት ለተ ሌሊ በአተ ጾም -(ዘዳ፳፰ -፮። ግንዘ። ቄር -ጰላ። ስንክ -የካ፰ ሠኔ፳፭። ማር፲፭ -፵፪። አቡሻ - መር -ዕዉ)

ቡዓዴ -መለየት አለያየት ልዩነት ርሕቀት ሥላሴ ድሙር በአቡዓዴ ወኢቱሳሔ አልቦ መክንዮ ወኢቡዓዴ ለኀ ዚኣሁ ህላዌ። ኅቡራን በኢቡዓዴ ወፅሙራን በኢቱሳሔ። ኢውላጤ ዘእንበለ ቱስሕት ወኢቡዓዴ -(ሃይ -አበ። ቅዳ -ግሩ ሳታት)

ቡዲር -(ትግሬ) ዱሮ ቀድሞ፤ ጥንት ኹሉ በፊት

ቢሓት ብሔያት -ማሮች ማሬዎች ክይስት ወዐናብርት ወሐርገፃት ወዐናጉግ ወቢሓት ወቈርነናዓት -(መቃ -ገ፲፪)

ቢሕ ብሔ -(ዕብ ብሄሞት) ማሬ፤ የወንዝ የባሕር ውሬ። ብህመን እይ ጠምቀ በማይ ራቁ ከመ ርነናዓት ወዐንጐጕ ወብሔ -(መጽ -ምስ)

ቢስ [1]-(ዐማርኛ። ሱር ቢሳእ) ቁሙ፤ ክፉ ንፉግ ቡዳ ባላይነ ወርቅ ቢስ አይይኽ ቢሰኛኽን ያርቅ ልበ ቢስ ልበ ቢስ እንዲሉ

[2]-በቁሙ፤ ንፉግ ባጭብእሰ ብኢስ

ቢሶም -(ዕብ ቦሼም ባሳም) የሽቱ ዕንጨ ዛፍ፤ መልካም ሽታ ያለው ማናቸውም ኹሉ በየስሙና በያይነቱ ባለብሉዮች ግን ለይተው ሾላ ብሳና ይሉታል -(ኩፋ -፳፩)

ቢሶስ ቢሶን -(ጽር ቢሱስ። ዕብ ቡጽ ሱር ቡጻ ዐረ በዝ) ክታን ልብሰ ክታን ልዝብ ለስላሳ፤ ወይም ነዶው ፈትሉ ቢሶስ ክዑብ -(ዘፀ፳፭ -፬። ፳፮ - -፴፩ -፴፮። ሉቃ፲፮ -፲፱) ሲያበዛ ቢሶሳት ይላል። አልባሰ ቀጠንት ወቢሶሳት ወሢራያት -(መቃ -ገ፳፪)

ቢረሌ -(ልያት። ጽር ቢሪሊዎን) ዕነቍ ርጥ የብርሌ ብርጭቆ ደንጊያ -(ዘፀ፳፰ - ጦቢ፲፫ -፲፯) ሳምን በቢረሌ ወታስዕ በወራውሬ። ናቅጽኪ ዘቢረሌ -(ራእ፳፩ -፳። ኢሳ፶፬ -፲፪) በቁሙ፤ ብርሌ ብርጭቆ ነጭ ጥሩ ሰትዩ ወይነ በማህው ወቢረሌ ምስክ ውስተ ቢረሌ ቢረልያት ብዙኃት -(ዓሞ፮ - - -፴፫ -፬። ልክ -፻፴፮)

ቢራ ባሪ -(ዕብ ቢራህ ጽር ባሪ) ስመ ሀገር፤ መዲና የንጉሥ ተማ ታላቅ ሕንጻ ጽኑ አንባ ርድ ምሽግ -(ዳን፰ -፪። ፩ዕዝ - -)

ቢዖላ -(ዕብ ብዑላ) ባል ያላት ሴት ባለባል፤ ክብርት ብዕልት። ምድርክሙኒ ቢዖላ -(ኢሳ፷፪ -)

ቢዝው -(ዋን ዋት ዙት) የዳነ የተዋጀ ውጁ፤ ቤዛ ያገኘ

ቢዶን -(ዕብ ኪዶን ጽር ጋይሶ) ጦር ዘገር ረምሕ፤ የሚወረወር ዐጭር መጠነኛ። ባለብሉዮች ግን ገጽ ያለው የብረት በሎታ መድፍ ነፍጥ በድል ነጐድ ይሉታል -(ኤር፶ -፵፪) በዕብራይስጥ ቤትና ካፍ ተመሳሳዮች ስለ ኾኑ በኪ ፈንታ ተጽፏል

ቢጽ -(ዐረ ጻሕብ፤ ቀሪብ ሺሪክ። ዕብ ሐቤር ሬዕ) ባልንጀራ እኩያ አምሳያ ወንድም መንቲያ፤ ወዳጅ ዘመድ ወገን ጎረ ቤት ጓደኛ ባልደረባ አቻ ሚስት ዘማች ወታደር ራዊት፤ ኅብረት ንድነት ትክክልነት ያለው ማናቸውም ኹሉ። ባለመጣፎች መጣፋቸውን ተከትለው ቢጽ እንደ ብእ ውስጠ ብዙና አስተጋባኢ ነው ላንድም ለብዙም ለወንድም ለሴትም ይነገር ይላሉ፤ ባለቅኔዎች ግን ቢጽና ፀር ንድ ብቻ እንጂ ለብዙ አይኾንም ይላሉና ፀርን ተመልከት ፍቅር ቢጸከ ከመ ነፍስከ ኢኮንኩ አነ እግዚእ አላ ቢጽከ ዘያፈቅር ቢጾ ውስተ ብርሃን ይነብር ወዘሰ ይጸልእ ቢጾ ብእሲ ምቢጹ ንግበር ሎቱ ቢጸ ቢጸ እስራኤል ወቢጸ ይሁዳ -(ዘሌ፲፱ -፲፰ ዕር ኢሳ፰ -፭። ፩ዮሐ - - -፲፩ መክ፬ -፬። ዘፍ፪ -፲፰ ፩ነገ -፲፭ -)

ባህል -(ላት) በቁሙ፤ ነገር ክርክር አባባል፤ አነጋገር የነገር ልት ትርጓሜ ምስጢር ድርሳን ልማድ ሕግ ሥርዐት የሃይማኖት ትምርት ቃል ድምፅ። ባህለ ልሳን ከሠትከ ባህለ መጻሕፍት ክዱነ። ወካዕበ ይቤ ርሎስ በውስተ ሐዱ ምባህላት። ይቤ በእንተ ትርጓሜ ባህላት። ያስተናክሩ ሥነ ባህሎሙ ባህለ ብካይ ሰሚዖ -(መዝ - ስንክ -ጥር፱ - -፬። ማር -ይሥ፩ ቄር -ጰላ። ስንክ -ጥቅ፩)

ባሕረ ሐሳብ -ቍጥር ያለው ዘመን ዓመተ ዓለም። ሐሳበ ባሕር የዘመን ጥር ወበመስፈርት ሰፈሮ ባሕር -(ሱቱ -ዕዝ፪ -፵፮)

ባሕረ ብርት -የብርት ውሃ፤ በብርት ምዕቃል የተመላ መታጠቢያ ኩሬ ሰሎሞን እንደ ባሕር አስፍቶ የሠራው -(ኤር፶፪ -፲፯ ፬ነገ -፲፮ -፲፯)

ባሕረ እሳት -በቁሙ፤ ረቂቅ ሰማያዊ እሳት ወይም ፍል ውሃ -(መቃ -ገ፱)

ባሕረ ጥበባት -ስመ ስርጋዌ ዮሐንስ ወንጌላዊ -(ድጓ)

ባሕረረ -(ዐረ በሒረ) ተቀጥላ ግስ ባነነ በረገገ ደነገጠ ደነበረ ከባሕር ልግባ አለ

ባሕሩስ -ቀለም የጐሽ መቃ፤ የሸንበቆ የሰንበሌጥ ዐይነት ቀጫጭን ውስጠ ክፍት ዐረቦች ብርዕ አድርገው የሚጥፉባት፤ በወንዝ ዳር በባሕር ረፍ የሚበቅል። ቅልጥሙ ቀጥ ያለ የተካከለ ስለ ኾነ ንገትና ለጣት ምሳሌ ኹኖ ይነገራል ጣተ መቃ ዐንገተ መቃ እንዲሉ። -(ሙሾ፤ ጣተ መልካም እቱ ስለ ሞተች ወንድሟ) ትመታኝን ብዬ ሴቲቱ ወንዱን፤ በመቃጣቷ ነው እኔስ የማዝን። ብርዐ ባሕሩስ። በትረ ባሕሩስ -(ኢሳ፩ -፴፩። ፬ነገ -፲፰ -፳፩) ጽሕድ በማለት ፈንታ ብሮሽ እንደማለት ባሕሩስ ይላል፤ የተሳሳተ የዐይ ባሕሩስ። ኀጺን ኮነ ብዙኀ ከመ ዕፀ ባሕሩስ ወከመ ብርዐ ገዳ -(ዘካ፲፩ -፪። ክብ -ነገ)

ባሕራዊ -የባሕር የምዕራብ፤ ምዕራባዊ።

ባሕር [1]-( አብሕርት ዐረ በሕር ሱር ባሕራ) በቁሙ መካነ ማይ ምቋመ ማይ ዓለመ ማይ ምእላደ ማይ ሰፊ ጥልቅ ዕሙቅ ውሃው የማያልቅ የማይደርቅ ስፋቱ የብስ የሚበልጥ እጅ የሚልቅ -(ዘፍ፩ - -) ባሕር ዐቢይ ባሕረ ርትራ። ብሕርት ወቀላያት -(ዳን - - ፀ፲ -፲፱ ኩፋ -) ስፋት ለሌለውም ለታናናሹ ሐይቅ ለኩሬ ይቀር ለወንዝ ለፈሳሽ ይነገራል። ባሕረ ው፤ ባሕረ ገሊላ ባሕረ ዟይ ባሕረ ጣና እንዲሉ ባሕረ ኒል። ተከዜ ዮርዳኖስ ባሕር -(አቡሻ -፰። ስን -ሠኔ፬ መስ፪)

[2]-ምዕራብ ግራ -(ዘፍ፲፪ -፰። ፲፫ -፲፬ ፳፰ -፲፬ ዳን፰ -) እመንገለ ባሕር ባሕረ ወአመንገለ ጽባሕ ጽባሐ -(ሕዝ፵፭ -)

 -ንኡስ ማእዝን በሰሜንና በምዕራብ ማኽል ያለ የሰሜን ምዕራብ የሊባ አፋዛዥ ትይዩና አንጻር ባሕረ ወሊባ -(ቅዳ)

ባሕርያዊ -የባሕርይ ስምን ግብርን አካልን ያሳያል

ባሕርይ [1]-(ያት። ዐረ በሕሪይ) ሕራይ ባሕራዊ፤ የባሕር ንቍ ሉል ከሰደፍ የሚገኝ ደረቅ ራራ ንካራ እብናዊ የወፍ ንቍላል የሚመስል፤ ታናሽ እንክብል ድብልብል፤ የሚበርቅ የሚያንጸበርቅ ዕንቍላል ቅሉ ዕንቈ ሉል ማለት ነው ስሙን ሉል ወስዷል፤ መመሳሰል የጋራ ውና -(ማቴ፯ -፮። ፲፫ -፵፭ -፵፮። ራእ፳፩ -፳፩) እስመ ሰደፍ ይወልዶ ለዕንቍ። ተናገር ዕንቈ ባሕርይ ወክሥት ህላዌከ ባሕርይ ያንጸበርቅ እማንቱ ዕንቈ ባሕርያት ክቡራት። መጽሐፈ ባሕርይ -(ማር -ይሥ፳፰ ሃይ -አበ -ኤፍ። አርጋ - ስንክ -ሚያ፰ ድር)

 -ክቡር ደንጊያ፤ የየብስ ንቍ ሉል የሚመስል፤ ባሕርያዊ። እብነ ባሕርይ -(ሔኖ፲፰ -፯። ጥበ፯ - ፲፰ -፳፬ ዮሴፍ)

[2] -(ዐረ ጀውሀር። ዕብ ) በቁሙ፤ የነገር ኹሉ ሥር መሠረት ምንጭ መውጫ መፍለቂያ መገኛ ባይዕ ህላዌ ክዋኔ ጀውሀር በዐረብ ዔጼም በዕብራይስጥ፤ ባሕርይም አካልም ይኾናል እንደ ህላዌና እንደ ጠባይዕ ነው ባሕርይ ግን በግእዝ ቋንቋ አካላዊ ፍጹመ አካል ባል እንጂ አካል ይባልም ካልም ባሕርያዊ ሕያወ ባሕርይ ቢባል እንጂ ባሕርይ አይባልም በምድር ያለ የፍጥረት ኹሉ ሥር ማይ መሬት ነፋስ እሳት ናቸው እሊህ አራቱ ባሕርያትም ጠባይዓትም ይባላሉ ባሕርይ ብሕረ እንደ ወጣ ጠባይዕም ጠብዐ ይወጣል ባሕር ለታውፅእ ተብላ ብዙ ሥነ ፍጥረት እንዳስገኘች ባሕርይም መገኛ ማስገኛ ስለ ኾነ የአካል የስም የህላዌ ጥንት የሥራ ምንጭ የግብር መሠረት ይባላል፤ ይኸውም አንቀጽና ቅጽል ብትን ጥሬ ኹሉ ዘር እንዲገኝ እንደዚያ ማለት ነው። ከባሕርይ ለሚገኝ ባሕርያዊ ሥራ ሠሪው አካል መሣሪያው ባሕርይ ነው፤ አካል ሠሪ እንዲባል ባሕርይ ደግሞ ሠሪ አይባልም ማጭድ ማጨጃ እንጂ ዐጫ እንዳይባል፤ ሠሪም ቢሉት ምስጢሩ ዚያው መሣሪያነት ይገባል፤ የሥራ ባለቤት ወትሮ አካል ነው። ወአካላኒ -(ሠሪዋ ፈጻሚዋ) እግዚአብሔር ውእቱ -(አረጋ -ድ፲፰) አካልን ባሕርይ ገባሪን ግብር በየስሙና የስልቱ ለይቶ የማያውቅ መምህር ግን አካል ሉት ባሕርይ ባሕርይ ሲሉት አካል እያለ የግእዝን ቋንቋ የመጻሕፍትን ቃል የሊቃውንትን ባህል ትርጓሜና ምስጢር ያበላሻል። እስመ ብሂሎቱ የሰ መላእክት ዘይኤምር ባሕርዪሁ ዘእምአብ ስመ ባሕርየ መለኮቱ ዘኮነ ሥጋ አላ ተወልደ ወባሕቱ ይኤምር ኀበ ባሕርየ ሥጋዌሁ -(አፈ -ድ፩ ዕብ - -) የፈጣሪ ባሕርይ እንደ ፍጡር ባሕርይ ባት ወደ ልጅ ማይወርድ ሊቀዳ ሊከፈል ወይም ሊበረዝ የማይቻል ንድ ሥር ንድ ነቅ ስለ ኾነ፤ ወልድ በተለየ አካሉ የኛን ባሕርይ ነሥቶ ፍጹም ኾነ ዜ፤ ሰው የኾነው አካሉ ነው እንጂ ባሕርዩ ልኾነምና ዘኮነ ሥጋ አለው በተዋሕዶ ወልድ ዋሕ አንድ አካል አንድ ልጅ ብሎ በተዐቅቦ ኹለት ባሕርይ ማለት ስለዚህ ነው መለኮት የሚሉ ን፤ ጥንቱን ተዋሕዶ ፊት ወይም ተለውጦ የኾነ አይዶለም ብለው እንደ ባህላቸው ይፈቱታል ባህላቸውም ባሕርዩ ኹኖ ንድ ባሕርይ ኹኗል ማለት ነው። ቅዱሳት መጻሕፍት ሊቃውንት አሐዱ ያሉትን የሥላሴን ሕርይ ፋፍሎ ሠለስቱ ማለት፤ በተዐቅቦ ክልኤቱ ያሉትን የወልድን ባሕርያት ቀላቅሎ አሐዱ ማለት ያሉታና የሸፍጥ የምፀት ቃል ነው እውነተኛ ትርጓሜና አፈታት አይዶለም ምንም ለተርጓሚው ቀኝ ቢኾን ለሰሚው ግራ ነው ይወልደዋል ብሎ ይቀድመውም አይበልጠውም ማለት ባሕርይ ይከፈል ነውና፤ ባሕርዩ ቢኾን አባቱ መንፈሱ ሳይቀሩ በግድ ሥላሴ ሰው ኾኑ ያሰኛል፤ እንደ አካላትም ሠለስቱ ቢሉት በግድ ሦስት አማልክት ያሰኛል ኹሉም የተነቀፈና የተወገዘ ነው። ሰው ነው መኾንና ሥጋ መልበስ አካቶ ፈጽሞ ለአካል ብቻ እንጂ ለባሕርይ ሊነገር አይቻልም። ናወግዝ ይብሉ ይኄልዩ ከመ ሥሉስ ቅዱስ ዘውእቶሙ ሠለስቱ ካላት ተሠገዉ፤ በብሂሎትሙ መለኮት ኵለንታሁ ዘንሬኢ ውእቱ በአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ተሠገወ ወናወግዝ ዓዲ እለ ይብሉ ሠለሰተ መለኮተ እን ዘአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ። ወለእመ ትቤ መለኮት ሞተ አንተ ትከውን ቀታሊሆሙ ለሥሉስ ቅዱስ ስመ ባሕርየ ሥላሴ ሐዱ ውእቱ ውእቱ መለኮት -(ሃይ - -ዮሐ -እስ -ወዘአን አግና) ከዚህ የቀረውን የባሕርይን ምስጢርና አፈታት በህላዌና በጠባይዕ በመለኮት ተራ ተመልከት።

ባሕቀቀ ተባሕቀቀ -አወከ ታወከሐብቀቀ።

ባሕቀወ -አንባሕቀወአፋሸገበቀወ

ባሕተወ -(በሐተ) ብቸኛ ኾነ፤ ተለየ፤ ተነጠለ ባሕተወ መለኮቱ ምትስብእቱ ወኢትስብእቱ እመለኮቱ -(መጽ መስ) ዘነ አለቀሰ ፈራ ተጨነቀ፤ ብቻ መኾን የተነሣ ምናሴ ሠሠ ገጸ አግዚአብሔር ወባሕተወ በሕቁ ምቅድመ ገጹ ለአምላከ በዊሁ ወጸለየ -(ዲድ - ዜና -፴፫ -፲፪) በባሕተወ ፈንታ ተባሕተወ ይላል፤ በዐገለ ፈንታ ተዐገለ እንዲል ፍችው አንድ ው፤ አይለወጥም ወአመ ወለዶ ተባሕተወ ቡሁ ሎቱ አመ ይትባሐቶ ወይትባአስ ምስለ ጎልያድ እለ ይትባሐተዉ ውስተ ድባር ወየዐይሉ ውስተ ዳማት -(ቅዳ -ግሩ መዝ -፻፶፩ አፈ - -)

ባሕቱ -(ባሕት) ብቻ እንጂ ግን ግና ነገር ግን። እንጂ ሲኾን ቢይ አገባብ ነው እንደ አኮኑና እንደ ዳእሙ በፊትም በኋላም ይገባል። በዝንቱ ባሕቱ ብቻ። ባሕቱ ዘንተ ረከብኩ። መበለተ ባሕቱ ታውስብ፤ ግን -(ዘፍ፴፬ -፲፭። መክ፯ - ዘሌ፳፩ -፲፬) ብቻ የሚኾን ገባብ ባሕቱ ብቻ ነበረ በመጽሐፍ ግን ዳእሙ አብቶት እጅግ ይገኝም። ያባተበትም ምክንያት መላሽና ጣፊ በባሕቱ ፍራ ትፍራህ ተአመን ዳእሙ ወለዘሂ ቈላ በአሚን ዳእሙ ያጸድቆ እሉኑ ዳእሙ ደቂቅከ እያሉ ስላገቡት ነው የዳእሙን ፍች ተመልከት -(ዕር፲፱ -ቍ፹፩)

ባሕቲት -(ዕብ ልባድ) ብቻ፤ ብቸታ ብቻነት፤ ጥራት ጥሩነት። ቅጽልና ዐጸፋ ይኾናል ባሕቲቱ ቶሙ ቶን ባሕቲትየ እያለ እስካሥር ይረባል፤ ሳይዘረዘር ግን በሳድስነት አይገኝም እንደ ለልና እንደ ሕቱ ነው። ኖኅ ባሕቲቱ ጢአት ባሕቲታ ለከ ለባሕቲትከ እሉ ባሕቲቶሙ አነ ባሕቲትየ። ኪያሁ ባሕቲቶ። ባሕቲቶ ዘበልዐ ስመ ይመውት ባሕቲቶ -(ኩፋ -፭። ውዳ - መዝ -፶። ዮሐ፲፯ - ኢዮ፩ -፲፭ ማቴ፬ - ቅኔ) በፈቃደ ባሕቲቱ፤ በራሱ በብቻው ፈቃድ በባሕቲቶሙ ተስእልዎ ብቻቸውን ኾኑ ጊዜ ኹነው ሠሐቀት በባሕቲታ በራሷ በሰውነቷ ብራይስጡ ግን ብቂርባ ይላል በሆዷ በልቧ በሐሳቧ ብቻ፤ ጥርስ ሳይገጥ ንፈር ይገለጥ ማለት ነው አቀሞን እን ባሕቲቶን፤ ለብቻቸው፤ እየብቻቸው ብቻቸውን እየ የእንተ ፍች ነው -( - -፮። ማር፬ - ዘፍ፲፰ -፲፪ ፳፩ -፳፰)

ባሕታዊ -(ዊት ውያን ያት) ብቻውን የሚኖር፤ ባታይ ባተሌ፤ ብቸኛ ስደተኛ፤ የዘመድ ድኻ እስመ ባሕታዊ ወነዳይ አነ። ዖፍ ባሕታዊ ርድአኒ ለተ ለባሕታዊት ተሣሀልኮሙ ክልኤ ባሕታውያን -(መዝ -፳፬ ፻፩ ስቴ፬ -፲፯ ጦቢ፰ -፲፯ መዝ -፷፮)

 -በቁሙ መናኝ መነኵሴ ዝጉሕ፤ ከዓለም ከሰ ተለይቶ ከአራዊት ጋራ በዱር በጣሻ በገደል ዋሻ የሚኖር፤ ቀድሞ ዎች እንደ ኤልያስ እንደ ዮሐንስ ኋላ ዎች እንደ ጳውሊና እንደ እንጦንስ ያለ ጳውሊ ዘመን ሰው ሳያይ በበረሓ ኑሯል፤ ስለዚህ ሊቀ ባሕታውያን ይባላል -(ስንክ -የካ፪) ባሕታዊ ዘሞቅሐ ርእሶ በጾማዕቱ መነኮስ ባሕታዊ። ወነበረ ሐቅለ ምስለ ራዊት -( - - -፯። ስንክ -ታኅ፳፫ ማር፩ -፲፫)

ባሕትዎ  ተባሕትዎ -ብቻ ብቸኛ መኾን ብቸኝነት። ወፂ ማኅበር ወተባሕትዎ ውስተ በኣት -(ፊልክ -፵፬)

ባህን ባህናን -ብናኝ ትቢያ ጕድፍ

ባህንኖ ኖት -(ባህነነ ይባሀንን ይባህንን) መብነን መባከን ብን ብን ብንን ብንን ማለት ማነስ መጕደል፤ መጥፋት መበላሸት፤ ከንቱ መኾን መጽሐፍ ግን በባህነነ ፈንታ ተባህነነ ይላል አያሰኝም ይኄይሰኒ መዊት ምይትባሀነነኒ ምዝጋናየ -(፩ቆሮ - -፲፭። ስንክ -መስ፭)

 -በቁሙ መባነን መበርገግ ደንግጦ ከንቅልፍ መነሣት -(ዐማርኛ)

ባሉጥ -(ዐረ በሉጥ ሱር ባሉጣ) የዛፍ ስም ጥኑ ጠንካራ ድሜያም ዛፍ ብዙ ቪሕ ዓመት የሚኖር፤ ጥንካሬው ዕፀዋት ኹሉ የሚበልጥ ዕንጨቱም ሰሉም በውድ የሚሼጥ ዐብ ብሎ በለጠ ማለት ዐማርኛው ዚህ የወጣ ነው ድርስንና ባላንን ተመልከት ድሜያምነቱም ሊታወቅ በአብርሃም ዘመን የነበረው ይደርቅና ይፈልስ ሳይገረሰስ እስከ ዛሬ አለ ዛሬም ርሱ ስላረጀ ዚያው ሥሩ በርሱው አምሳል ጽቅ ያለው ንድ ወጥ ኹሉ እየኼደ ያየዋል ዮሴፍም በታሪክ ጥንት ፍጥረት የነበረ ቀዳማዊ ነው ይላል ዐሠርቱ ወክልኤቱ ዕፀወ ባሉጥ -(ስንክ -ጥቅ፳ ሆሴ -፲፫) ብራይስጥ ግን ዛፉን ሎን ብሎ ፍሬውን ብቻ ሉጥ ይላል

ባላሒ መባልሒ -የሚያድን አዳኝ ታዳጊ ባላሔ ኵልነ። ባላሒ ለዕጓለ ማውታ መባልሒት -(ቅዳ። ኪዳ። አርጋ)

ባላቅ [1]-(ትግሬ) ብዙ ደንጊያ፤ ጕር፤ የደንጊያ ክምር ገዎቻ ጥኝ፤ ኰኵሕ አለት። የሰው ስም ሲኾን ግን እንደ ዕብራይስጡ ፋሊ ነሣቲ ማለት ነው -(ዘኍ፳፫ -)

[2]-( አብላቅ ጽር ፕላኬስ) የደንጊያ ሰሌዳ ገበታ ጽሌ። ወአልቦ ዘሀሎ ውስተ ይእቲ ታቦት ዘእንበለ ክልኤቱ ብላቅ ዘአንበረ ሙሴ በደብረ ኰሬ -(፪፳ዜና - -)

[3]-(ዐረ፤ ሩኃም። ዕብ ይሽ ጽር ማርማሩ) ነጭ ደንጊያ እብነ በረድ ዕማደ ባላቅ ኀጺነ ወባላቀ -(ማሕ፭ -፲፭ ራእ፲፰ -፲፪)

[4]-(ዕብ ሾሀም። ጽር ኦኒኪ) ክቡር ደንጊያ ንቍ አንክዮንንና ሶምን ርድዮንን እይ፤ ከዚህ ጋራ አንድ ነው ኢበባላቅ ቅድው ወኢበሰንፔር ምኀበ ብላቅኑ እምኀበ አእባን -(ኢዮ፳፰ -፲፮ አፈ -ድ፩)

ባላን -(ጽር ባላኖስ። ዕብ አሎን ዐረ በሉጥ) የዛፍ ም። ድርስንና ባሉጥን ተመልከት ዚህ ጋራ ነው ባለብሉዮች ግን ግራር ይሉታል። ታሕተ ዕፀ ባላን -(ዘፍ፴፭ -፰። መሳ፱ - ኩፋ -፲፫)

ባልሖ ሖት -(ባልሐ ይባልሕ ይባልሕ። ዕብ ባሎሕ መዝለል መንጐራደድ) ማዳን ማውጣት መታደግ መቤዠት ተያዙ ገቡ በኋላ ይባልሖ ለንጹ ይክልኑ ባልሖ ልቦ ዘያድኅን ወዘይባልሕ ባልሖትየ -(ኢዮ፳፪ -፴። ኢሳ፶ -፪። መዝ -፯። ስንክ -ጥቅ፳፬)

ባማ -(275) -(ዕብራ) የቦታ ልዑል ዳጋ ሊልታ፤ ተራራ ረብ በተራራ ላይ የተሠራ ቤተ ጣዖት ምሧዐ ዖት የመቃብር ቤት ባማ ለርኩስ እንጂ ለቅዱስ አይነገርም፤ ሲያበዛ ባሞት ይላል ምንት ውእቱ ባማ ዘተሐውሩ አንትሙ ህየ ወተሰምየ ስሙ ባማ -(ሕዝ፳ -፴፱)

ባሲላዊ -(ጽር ባሲሌፍስ) ጉሣዊ የንጉሥ ወገን ባሲላውያን -(ቀሌ)

ባሲልያ -መንግሥት፤ ጌትነት ንጉሥነት። መጽሐፍ ግን ባሲልያሱ በማለት ፈንታ ፋሲልያሱ ይላል ዝርዝር ነው ከ። አምንስቲቲን እይ።

ባስልዮስ -የሰው ም፤ ንጉሥ ንጉሣዊ ማለት ነው

ባሦር -(ዕብ ባሣር ሱር ቤስራ) ሥጋ የሥጋ ክፍል። ወገብረ ርእሱ ባሦረ ሩመ ወለብሰ ምኔሃ ድንግል -(ቀሌ) ዐረቡ ግን በሸር እብን እልበሸር ብሎ ሰብእ ወልደ ሰብእ ይላል

ባረከ -ቁሙ ማተበ ጸሎተ ቡራኬ ደገመ። አአኰተ -(አኰተ) ባረ ወፈተተ ኅቡረ ይባርኩ ማእደ በውስተ ጸሎት። ኢይባርኩ ላዕለ በጸል -(ቅዳ። ግብ፪ -፵፪። - -፲፯)

 -መረቀ መልካም ጦታን ሰው ተመኘ ተናገረ፤ አዘዘ ሰጠ በረ ሾመ አበዛ አበረከተ -(ዘፀ፩ -፳፪ -፳፰ - -፫። ፲፯ -፲፮) ወዘእንበለ ካሕድ ዘየዐቢ ይባርኮ ለዘይን ብሔር ኀበ በልዑ ኅብስተ ዘባረከ እግዚእነ -(ዕብ፯ -፯። ዮሐ፮ -፳፫)

 -ደበ አዋረደ ነቀፈ ረገመ ካደ ውስተ ገጽ ይባርከከ። ባርኮ ለእግዚ ወሙት ባረካሁ ለእግ ወለንጉሥኒ -(ኢዮ፩ -፲፪ - -፱። ፫ነገ -፳፩ - -፲፫። ስንክ -ታኅ፩)

ባሪ -(ጽርእ) መዲና ግንብ አዳራሽ ቢራን ተመልከት ከዚህ ጋራ ነው ሱሳ ዘባሪ -(ዳን፰ -)

ባርኮ ኮት -(ባረከ ይባርክ ይባርክ) ማመስገን ከመንበርከክ ጋራ ወይም ተንበርክኮ ምስጋና ማቅረብ። ባርኮና በሪክ በሴም ቋንቋ ኹሉ አንድ ዘር ነው የዱሮ ዎች አበው ቀደምት ነቢያት ህናት የፈጣሪን ስም ሲጠ ሲጸልዩ ሲያመሰግኑ ግደው ተንበርከው ነበረና ባረከ ማለት የኹሉንም ስልት ያሳያል። ይባርክዎ ብረ እግዚ ለእግ ወባረኩ ቡራኬ ባርኩ ስሙ በኵሉ -(ዳን፫ -፶፯ ፹፰። ፀ፲፭ - ራ፴፱ -፴፭)

ባርዮ ዮት -(ባረየ ይባሪ ይባሪ። ዐረ በረይ) መለወጥ መተካት ማፈራረቅ ማስተጋገዝ ማስተራረፍ። መግዛት ሪያ ማድረግ። መጻሕፍት ግን በባረየ ፈንታ አስተባረየ ይላሉ። ያስተባሪ ክረምተ በሐጋይ ወመፀወ በጸደይ። ኀምስተ ራዘ በዘያስተባሪ ያስተባሪ ወርኅ ምልአተ ወሕጸተ ውደ ብርሃኑ ይዕጥኑ በአስተባርዮ ደው ከመ ዘያስተባሪ የማኖ ልዑል -(መጽ -ምስ ዘፍ፵፭ -፳፪ አርጋ -፩። ግንዘ። መዝ -፸፮) አባረየ አስተባረየ ቢል አድራጊ ኹኖ ከባረየ ቢደረብ እንጂ ብቻው አስደራጊ አይኾንም።

-(ዓት) በቍዔት፤ ጥቅም ትርፍ፤ የሚበቃ ዋጋ ጻማሆሙ ዘእንበለ ባቍዕ ልባቲ ባቍዕ ይሁብ ብድ ዘአልቦ ባቍዕ ዘአልቦ ባቍዕ ወሀብኩ ይልየ -(ጥበ፫ -፲፩ ዕብ፯ -፲፰ ራ፳ -፲፬ ኢሳ፵፱ -)

ባቅቡቅ -(ዕብ) ታናሽ የውሃ ቅል መንቀል ርሙዝ አፈ ባብ ንገተ ረዥም ጋላም ቅሉን ቡቄ ይለዋል

ባበለ -ተቀላቀለ፤ ተዘባረቀ። ተዘራ ተበተነ በባበለም ፈንታ በልበለ ይላል ችው ነው ወተሰምየ ውእቱ መካን ባቢሎን እስመ ባቲ ተበልበሉ ልሳናት -( - - -፲፫)

ባበየ ቤበየ -(ይቤቢ) ሠየ፤ ጐመዠ ሮጠ ናወዘ ተቅበዘበዘ፤ የዝሙት በበ ሠርክ ትቤቢ በውስተ ፍናዊሃ -(ኤር፪ -፳፫) ብራይስጡ ግን ፈጣን ቀላል፤ መንገዷ ታን የሚመስል ይላል

ባቡቴ -ክብ እንክብል ኅብስት ሴቶች በዔሊ አምሳል የሚጋግሩት ይልቁንም የቡልጋ ዎች ሙታን መክፈልት የሚያደርጉት ዳቦ ድፎ ነብሩቴ ባቡቴ እንዲሉ።

ባቡት -ዔሊ ደንጊያ ልብሱ ሽልምልም

ባቢል -(ዐረ አባቢል) ዖፍ የተረት ወፍ እንደ ፊንክስ ያለ፤ በፍጥረታት ውስጥ የሌለ ያልነበረ ያልተፈጠረ፤ ሙሐመዳውያን ሱር በሚባለው መጣፋቸው የሚያወሩት የሚናገሩት ወይም ባቢሎን ታመልከው የነበር አዕዋፈ ባቢል ዘውእቱ ጎርጋናት ሠለስቱ ምእት -(አዋል)

ባቢሎሳን -ቱሱሓን ኅዉሣን ዝርዋን። ባቢሎሳን -(ዲድ)

()           ባባ -ያት ቅድም አያት አበ አበው የሮም ጳጳስ ፓፓ -(ሐረርና ዐረብ) እንዳማርኛ ግን ጠብቆ ነገር አንቀጽ ኹኖ ባባ አባባ እያሰኘ ፈሪነትንና ብቡነትን ያሳያል

ባባህ -(ዐረ ቅብጥ ፓዎፒ ፖፔ ፋዎፊ) ስመ ወርኅ የግብጦች ኹለተኛ ወር ጥቅምት ቃሉ የቅብጥ ፊደሉ የዐረብ ስለ ኾነ ለበ ተለውጧል ግበሩ በዓለ በመንፈቀ ባባህ -(አቡሻ -) በዕብራይስጥ ግን ብንተ ይን ያይን ሚሚቶ ብሌን ማለት ነው።

ባቤል -(ዐረ አባቢል) ዖፍ የተረት ወፍ እንደ ፊንክስ ያለ፤ በፍጥረታት ውስጥ የሌለ ያልነበረ ያልተፈጠረ፤ ሙሐመዳውያን ሱር በሚባለው መጣፋቸው የሚያወሩት የሚናገሩት ወይም ባቢሎን ታመልከው የነበር አዕዋፈ ባቢል ዘውእቱ ጎርጋናት ሠለስቱ ምእት -(አዋል)

ባብ -(ዐረብ) በር፤ ደጅ አፍ፤ መዝጊያ። ነደበን እይ

ባተለ -(ዐማርኛ) በቁሙ፤ ባተሌ ኾነ ደነገለ

ባቱል -(ዕብ ብቱላ) ድንግል ወንድ ያላወቃት ሴት ልጅ ልጃገረድ -(አዋል)

()          ባት -(ዕብራ) የርጥብ መስፈሪያ የዘይት ገንቦ ማድጋ መስፈርተ ባት። ባተ ጽድቅ -(፫ነገ -፲፭ -፲፩ ሕዝ፵፭ - -፲፩)

ባእ -ስንዝር፤ባዕ።

ባዕ -ስንዝርበዊዕ ቦዐ

 -ስንዝር  ውስጥ እጅ ባለብሉዮች ግን ክንድ ይሉታል -(ዘፀ፳፴፮ -፲፮)

ባዕላይ -ባለብዙ ዋይ፤ ባለጠጋ፤ ወይም ባለጠጎች። ላንድም ለብዙም ይነገራል ማእከላ ነው። ኮን ከመ ዳይ ባኖስ ክቡር ወልደ ባዕላይ ኢይምሕሮ ነዳይ ወኢየኀፍሮ ባዕላይ ባዕላይ ኢአምኑ ወነዳያኒ ሰምዑ -(መዋሥ። ድጓ)

ባዕል -(ልት አብዕልት) ቅጽልና ጥሬ ባለጠጋ ሀብታም በርቴ ጌታ ባዕል ደንጻዊ። ብእሲት ክብርት ወባዕልት። አብዕልትኒ ወነዳይኒ አግብኦ ለአብዕልቲሃ -(ሢራ፳፭ -፪። ስንክ -ሐም፲፭። መዝ -፵፰። ጦቢ፫ -፲፫) ባዕል ቅጽልና ጥሬ ስለ ኾነ በጥሬነቱ ዓልን ይመስላልና በበዓል ፈንታ ባዕል ይላል ፍችው ጌታ ባለቤት ባል ማለት ነው ባዕለ ዋይ። ባዕለ ሕም። ባዕለ ቤት ባዕለ ብሔር ባዕለ ዕዳ ባዕለ -(ዘሌ፭ -፳፬ ዘፀ፳፩ -፳፰። ፳፪ - ዘፍ፵፪ -፴፫። ኢሳ፳፬ -፪። ስንክ -መስ፳፰)

(ሳት)         ባእስ -ብርቱ ጥል ብ፤ ሙግት ክርክር፤ ስድብ። ቦኑ ባእሰ ተባአሰ ምስለ እስራኤል። በባእስ ወበዝጓጔ ይፌንዎሙ። ጋእዝ ወባእስ -(መሳ፲፩ -፳፭። ኢሳ፳፯ -፰። ምሳ፲፯ -፲፬)

ባዕድ [1]-(ድት ዳን ዳት) ዝኒ ማሁ ቅጽልና ጥሬ በቁሙ ልዩ ሌላ ነኪር ባዕድ ሰብ ልቦ ባዕድ ዘእንበሌሁ ይዘግብ ባዕድ በብሔረ ባዕድ። ወቦ ባዕዳንሂ። ወባዕዳትሂ ብዙኃት -(ዘፀ፴ - ዘዳ፬ -፴፭። ሢራ፲፬ -፬። ኤር፭ -፲፱ ግብ፲፯ -፴፪። ማር፲፭ -፵፩)

[2]-(ጥሬ ዘር) የፊደል አገልጋይ ፊደል የጥሬ ተውሳክ ቅጽል ጥሬ እየተጨመረ መነሻ ኹኖ የሚነገር ባዕድ የሚኾኑ ፊደላት ዋነኞቹ ናቸው አመተነ ግእዛቸው ብቻ ስለ ተነገረ ቀር ካዕባቸው ራብዓቸው ሳድሳቸውና ሳብዓቸው ተለይቶ አይቀርም የማድረግና የማስደረግ ልማድ እየኾነ በቀዳማይ አንቀጽ ይገባና ወዲያው ለጥሬው ባዕድ ይኾናል -(ማስረጃ) ርእየ ርአየ ርኣያ ከለለ አከለለ፤ አክሊል። መሰለ ምሰለ አምሳል ሰትዐ ስትዐ ስትዓ ገዝአ አግዝአ እግዚእ ለትሐ ልትሐ፤ ልታሕ ነገ ንገደ ንግዳ የመሰለው ኹሉ ባዕድ ሲኾን ቀደሰ መቅደስ በረ መንበር ደበለ መድበል ውሕዘ ሙሓዝ፤ ወፅአ ሙፃእ ወረደ ሙራድ። መረ ማእምር፤ ሒበ ማሕየብ፤ ሐረጸ ማሕረጽ። ም፤ ብረ ምግባር ሖረ  ምሕዋር፤ ምቅዋም ::  ወሠረ ሞሠርት ወፈጠ ሞፈጥ፤ ወፀፈ ሞፀፍ ይላል ሙና ካዕብና ሳብዕ መኾናቸው ወን ስለ ጐረዱ ነውና በወ ሚንሣ ግስ በቀር በሌላ አይገኙም ደግሞ የመደረግና የመደራረግ ልማድ እየኾነ በቀዳማይ አንቀጽ ይገባና እንደ ወዲያው ለጥሬው ባዕድ ይኾናል ይኸውም ጥሬ ዘር ኹሉ ከሚመስለው እንጂ ከማይመስለው አንቀጽ እንዳይወጣ በግልጥ ያስረዳል -(ማስረጃ) ገሠ ተገሠጸ ተግሣጽ። ወለጠ ተወለጠ ተውላጥ። ሜጠ ተመይጠ ተምያጥ ፈጸመ ተፈጸመ፤ ተፍጻም። ቀረመ ቀሠመ ተቀርመ ተቀሥመ ተቅራም ተቅሣም የመሰለው ኹሉ  ሐጸ ተሓጸ ታሕጻጽ። ኀሠ ተኀ ታኅሣሥ መሰ ተኀመሰ፤ ታኅማስ  መክሐ ተመክሐ ትምክሕት ሠለሰ ተሠለሰ ትሥልስት። ሠገወ ተሠገወ ትሥጉት። ደመረ ተደመረ፤ ትድምርት ወፈየ ተወፈየ ትውፊት የመሰለው ኹሉ  ነ፤ ባዕድ ሲኾን በነ ሚነሣ ከነ ግስ በቀር በደጊመ ቃል ግስ እየገባ ተለይቶ ይቀርና የጥሬ መነሻ ይሆናል። -(ማስረጃ) በልበለ ንበልበለ በልባል። በስበሰ ንበስበሰ ነበስባስ ጐድጐደ አንጐድጐደ፤ ነጐድጓድ ገርገረ ርጐረ፤አንገርገረ አንጐርጐረ ነገርጋር ነጐርጓር። ቀጥቀጠ ቀልቀለ አንቀጥቀጠ ንቀልቀለ ቀጥቃጥ ቀልቃል የመሰለው ኹሉ አን አስተም በአ ምክንያት ልማድ እየኾኑ ይገቡና ለጥሬ ለቅጽል ባዕድ ይኾናሉ እንዳለና እን እየኾነ ደጊመ ቃል ግስ ሲገባ፤ በስበሰ ንበስበሰ፤ አንበሳ። ገለገ አንገለገ ንግልጋ ሶሰወ አንሶሰወ እንስሳ ጎገወ ንጎገወ እንጉግው። ጌገየ አንጌገየ እንጌግይ፤ የመሰለው ኹሉ። የቀረውን በአንና በእን ተመል ዚያ ነግሯል። አስተ እስት እየኾነ ሲገባ፤ ፍሰ አንፈሰ ስተንፈሰ ስትንፋሰ። ገብአ አግብአ ስተጋብአ ስትጉቡእ ስተር ስትርኩብ፤ የመሰለው ኹሉ ደግሞ አን እየጐረደ አስተ በገባበት ይገባል ይህም ስተፍሥሐ መስተፍሥሕ፤ አስተመክሐ መስተመክሕ፤ ስተስረየ መስተስርይ ምስትስራይ እያለ ሌላውን ኹሉ ያሳያል

ባውኒ -የወር ስምበኡናህ

ባውላ - ጭፍራ ቡልዮስ ቄሳ የወጣ -(ዮሴፍ)

ባዚቃ -(ዕብ ባዛቅ) መብረቅ ነጸብራቅ -(ሕዝ፩ -፲፬)

ባዜቃ -(ዐረ ዘይበቅ) በቁሙ ፈሳሽ የማዕደን ዐይነት የሚዝቦቀቦቅ። ጥሩ ብር ቅልቅል የሌለው። እንዘ ትሰወጢ ባዜቃ -(ደራሲ)

ባዝራ -(ዐማርኛ) ቁሙ እንስት ፈረስ ፍሬያማ ፍሬያም መፍርዪት።

ባዝግና -ዝርግፍዘጊን ዘገነ።

ባዶስ -(ጽር ባቶስ። ዕብ ባት) የልክ የመስፈሪያ ስም፤ የርጥብ መስፈሪያ የዘይት ገንቦ። ምእተ በመስፈርተ ባዶስ ቅብዐ -(ሉቃ፲፮ -) መስፈሪያነቱም የሖሜርን ፲ኛ ክፍል ያነሣል፤ የባትና የኢፍ ልካቸው አንድ ነውና ኢፍን ተመልከት -(ሕዝ፵፭ -፲፩) ከዚህ የተነሣ ባዶስን ቤዶ ፥ላዳን የቤት ይሉታል ቤዶ የወሎ የተንታ የደላንታ ነው። ወአሐቲ ስፈሬዳ ታገምር ርባዕተ ባዶሰ -(ገድ -ተክ) 

ባጎር -ጐበዝ ልማሳ ብግራም፤ ሕፃንነቱን የጨረሰ አካለ መጠን ያደረሰ፤ ባለአእምሮ የካያ ዓመት ልጅ ወይም የሚበልጥ። ጥበበ ባጎር ወልደ ብዙ -(ጥበ -) ባጎር ሎሞን ብኵ ዳዊት

ባጦስ [1]-እምባ() የሚቈረጥ የሚቈጠቈጥ ለጋውን ልጆች እየላጡ የሚበሉት። -(ዘፈን) ስለሚያለቅስ ልጅ፤ እናትኽ ውሃ ወርዳለች፤ እምባጮውን መጣልኻለች።

[2]-(ጽር ባቶስ። ዕብ ስኔ) ጳጦስ ሳቤቅ፤ የሾኽ ቍጥቋጦ እሾኻም ዛፍ ፍሬው ቀይ መዐዛው ናይ ዕፀ ባጦስ -(ዘዳ፴፫ -፲፮ ሉቃ፳ -፴፯) ሳቤቅንና ጳጦስን እይ

ቤለ ይቤ ይበል -አለብህለ ይብል ይብሀል።

ቤል -(ዕብ) የባቢሎን ፊል ስመ ጣዖት ባቢሎናዊ፤ ናቡከደነጾር ያቆመው ምስል። ባለብሉዮች ግን የፈረስ ምስል ይሉታል -(ኢሳ፷፮ -፩። ዳን፫ -)

 -ቤልየባቢሎን ከፊልበዪል

ቤልሖር -(ጽር ቤሊአር ዕብ ብሊያዐል) ይጣን የሰይጣን ለሰውም ይኾናል ክፉ ጥፉ ልክስክስ ምናምንቴ ሕገ ወጥ ቀንበር ሰበር ዳንዴ ወንበዴ ቀማኛ ሽፍታ ማለት ነው መኑ ዘያኀብሮ ክርስቶስ ምስለ ቤልሖር ወኢይኰንኖሙ መንፈሰ ቤልሖር -(፪ቆሮ - -፲፭ ኩፋ -)

ቤሩሲም በርሲም -(ዕብ ብሮሽም) ዝኒ ማሁ ጥዶች ዕፀወ በርሲም -(፫ነገ - -)

ቤሩሽ -(ዕብ ብሮሽ ጽር ኪፓሪሶስ) ጥድ፤ የጥድ ዐይነት ዛፍ ወፍራም ረዥም መለሎ ለየዐውዩ ቤሩሽ ስመ ወድቀ ዘግባ -(ዘካ፲፩ -)

ቤርሳቤሕ -(ዕብ ብኤር ሻባዕ) ዐዘቅተ መሐላ የመሐላ ድጓድ -(ዘፍ፳፩ -፴፩)

ቤርሴክታን -(ጽርእ) ሣጥን ታቦት የገንዘብ የሬሳ  ኤርጋብን እይ -(፩ነገ - -)

ቤቃ - አምላክ፤ እንደ ኣካዕ ያለ ኹለተኛ ካል ቃል ቀዳማዊ፤ በሌላው ንቀጽ መቅድመ ቃል ይፈታዋል -(ሔኖ)

ቤበየ -ሠየ ጐመዠባበየ

ቤተ መዋጽሕት -ፈኛ መክደኛ ጐባባ -(ዘፀ፳፭ -፳፱)

ቤተ እግር -መጫሚያ፤ ሹራብ ሱሪ ገንባሌ ድርማንቅ ቦለሌ።

ቤተ ክርስቲያን -( አብያተ ክርስቲያናት) በቁሙ ቤተ ክሲያን፤ የምእመናን መሰብሰቢያ ቤተ ክርስቲያንሰ ቤተ ሎት ይእቲ -( - -)

 -የክርስቶስ መንጋ ጉባኤ ማኅበር ሕዝበ ክርስቲያን ኒሳን እይ ዚህ ጋራ ነው ንግራ ቤተ ክርስቲያን ሰብዑ ብያተ ክርስቲያናት -( - -፩። ማቴ፲፰ -፲፯ ራእ፩ -)

ቤተ ወይን -የጠጅ ቤት የወይን በበርሚል በጋን የሚሾምበት -(ማሕ፪ -)

ቤተ ድዉያን -በሽተኞች እስኪድኑ የሚተኙበት ሐኪምና ፈውስ ያለበት ንጹሕ -(ቀኖ -ኒቅ)

ቤተ ግዝእ -የድግስ የመሸታ ቤት ዎት ስካርና ዝሙት ያለበት -(መክ፯ -)

ቤተ ሐኖት -ቤተ ዝሙት የገበያ ቤት መብል መጠጥ የሚሸጥበት -(ስንክ -ግን፲፪)

ቤተ ላሕ -የሐዘን ቤት ማልቀሻ እንብ ማፍሰሻ -(መክ፯ -)

ቤተ ልሔም - ሀገ ቤተ ኅብስት -(ዘፍ፴፭ ፲፱)

ቤተ ልብስ -ጋን ጥን ዕቃ ቤት የቤተ ክሲያን ልብስ የሚከተትበት -(ትእ -ጴጥ)

ቤተ መምህራን -ታላቅ የተማሪ ቤት የፈላስፎች ምርት ያለበት -(ስንክ -ግን፲፪)

ቤተ መቅደስ -በቁሙ እግዚ መቅደሰ ሪት፤ መቅደሰ ወንጌል ቤተ ክሲያን

ቤተ መበስላን -የወጥ የንፍሮ ቤት ማብሰያ መቀቀያ

ቤተ መዛግብት - ግምጃ ቤት ቃና ልብስ በሣጥን መልቶ የሚቀመጥበት -(ዳን፩ -)

ቤተ መያሲ -የመሸታ ቤት ከዚያው እየጠጡ የሚሰክሩበት -(ኢሳ፭ -፲፩)

ቤተ መጻሕፍት -የመጣፍ ቤት መጣፍ ኹሉ በያይነቱ የሚገኝበት -(ቢብሊዮቴክ) ትርጓሜ የሚነገርበት የመጣፍ መክተቻ ጥን ማኅደር ቤት ዋሻ -(ገድ -አዳ)  

ቤተ ሙታን -መቃበር የመቃበር ቤት ሲኦል -(ስንክ -የኳ፰)

ቤተ ማይ -ሠገራ፤ ዐዘቅተ ኵስሕ -(ስንክ -የካ፳፩)

ቤተ ምሳሕ -አዳራሽ፤ ግብር ማግቢያ ምሳ ማቅረቢያ -(ዳን፭ -)

ቤተ ምሥያጥ - መደብር የንግድ ቤት -(ዮሐ፪ -፲፮)

ቤተ ምርፋቅ -የምግብ ቤት ዳስ ደጀ ስላም፤ ቤተ ልሔም።

ቤተ ሞቅሕ -የግዞት ቤት፤ ወንጀለኞች የሚታሰሩበት -(መክ፬ -፲፬)

ቤተ ስምዕ -ደብተራ ስምዕ የሙሴ ድንኳን፤ -(፩ዜና - -፴፪። ፪ዜና - -)

ቤተ ስታይ -የድግስ የመሸታ ቤት ያረቄ መደብር መጠጥ ኹሉ በያይነቱ የሚገኝበት -(ሢራ፴፭ -) ቤት በነገር ኹሉ እየተናበበ በዚህ አምሳል እንደ ዘርፉ ስልት ደፈታል ዘርፍና ቅጽል ባለቤትን ወይም ስምና ግብርን እንዲገልጥ አስተውል።

ቤተ ርእስ -ቆብ ባርኔጣ፤ የካባ የበርኖስ ንጮ

ቤተ ብለኔ -የውሽባ ቤት፤ መታጠቢያ ሽቱ መዝገቢያ -(ቀሌ)

ቤተ ነግድ -እንግዳ የሚያርፍበት ተት ብሎ የሚገባበት ልኳንዳ፤ ሆቴል -(ስንክ -ነሐ፲፭)

ቤተ አማልክት -የጣዖታት ቤት ብዙ ዐይነት ጣዖት ያለበት መስጊድ።

ቤተ አፈው -የሽቱ መደብ የበቀለበት የተተከለበት -(ማሕ፮ -)

ቤተ እድ -እጅጌ እጀ ባብ የእጅ ቤዛ ሹራብ። የዕቃ ) ቀለበት -(ዘፀ፳ -፳፭)

ቤተ እግዚ -የሙሴ ድንኳን መቅደሰ ሎሞን ቤተ ክሲያን ጉባኤ ምእመናን -(ቀሌ)

ቤተ ክሣድ -ዐንገትጌ የቀሚስ አፍ ራስ ማግቢያ።

ቤተ ዝሙት -የዝሙት መደብር ያመንዝሮች ቤት ኀፍረት በቀር ሌላ ነገር የማይሸጥበት -(ሕዝ፲፮ -፴፱)

ቤተ ጣዖት -የሰይጣን ቤት ይጣን በጣዖቱ ድሮ የሚመለክበት -(ኩፋ -፲፪)

ቤተ ጸሎት -ታናሽ ምኵራብ፤ የሥዕል ቤት፤ ጸሎት በቀር ሧዕ የማይቀርብበት ወይም ታላቅ መቅደስ ቤተ ሲያ -(ሳ፶፮ -)

ቤተ ፍሥሓ -የሰርግ የመሸታ ቤት -(መክ፯ -)

ቤተ ፍንዱቅ -ዝኒ ማሁ፤ ቤተ ነግድ -(ትእ -ጴጥ)

ቤታዊ አብያታዊ -የቤት ቤታም ባለቤት ቤት ባት፤ አዛዥ መጋቢ ቤተ ሰብ ዘመድ የቤት ውልድ። ብረ ጉሥ ሰበእ ብያታዊ -(ዮሐ፬ -፵፮ -፵፱)

ቤጤልዋ -ስመ ሀገር -(ዮዲ፬ -)

ቤት [1]-( አብያት። ዕብ ባይት። ሱር ቤታ። ዐረ በይት) ቁሙ ማደሪያ መኖሪያ፤ ሥራ መሥሪያ በደንጊያ በብረት በጡብና በንጨት በኖራ በጭቃ በሣር በጨፈቃ የሚሠራ። ውስጠ ክፍትነት ያለው ዕቃ ቦታ፤ ዋሻ ፍርኵታ፤ ጐሬ ጓድ ታላቁም ታናሹም ማናቸውም ኹሉ። እቀትሎ ቤተ ምክራም ወለቤተ ሐጋይ ይትሀጐሉ ብያት ዘቀርነ ወይተከሉ ብያት ካልኣን ይቀሥፎ ዐቢይ ቤት በድቀት ወለንኡስ ቤት በንፅኀት ባእ ቤተከ ቤት ምሩግ -(ዓሞ፫ -፲፭ -፲፩ ኢሳ፳፮ - ምሳ፳፩ -)

 -ወገን ነገድ፤ ዘር ትውልድ፤ ጉባኤ ማኅበር ፍራ ወታደር በያለቃው። ርስዒ ሕዝበኪ ወቤተ አቡኪ ቤተ ያዕቀብ ቤተ ዳዊት ቤተ ስራኤል ቤተ ክርስቲያን ቤተ ከህነት ቤተ መንግሥት

[2]-ገንዘብ ዘመድ ቤተ -(ማቴ፳፫ -፲፬ ፀ፩ -፳፩)

 - ፊደል ካልእ ቅርጹ ቤትና ደጅ አፍ የሚመስል -(መዝ -፻፲፰ -፲፮ ሰቈ፩ - - -፭። -) ስሙንና መልኩን ቤት ወስዷል

[3]-በቁሙ ስመ ፊደልበዪት ቤተ

ቤዘ -ተቤዠበዪዝ ቤዘ።

ቤዘወ  -ተቤዠበዪዝ ቤዘ።

ቤዛ (ዛት) [1]-በቁሙ፤ ዋጋ፤ ካሳ፤ ለውጥ ምትክ ላፊ ዋቢ፤ ዋስ፤ መድን ተያዥ ጥላ ጋሻ የመሰለው ኹሉ ቤዛ ፍሱ ብእሲ ጥሪተ ብዕሉ በቤዛ ቤዛ ኵሉ ኀጢአትከ ማእስ ቤዛ ማእስ -(ምሳ፲፫ -፰። ኢሳ፵፭ -፲፫ ኤር፲፭ -፲፫ ኢዮ፪ -)

[2]-(ደቂቅ አገባብ) ለ፤ ፈንታ ምክንያት። እሜጡ ፍስየ ቤዛ ባግዕየ ስለ በጎቼ ዐይን ቤዛ ዐይን ወስን ቤዛ ስን በዐይን ፈንታ በጥርስ ፈንታ። ተሰቀለ ቤዛነ ስለኛ በኛ ምክንያት፤ ወይም ቤዛችን ተብሎ በቂ ይኾናል ቤዛሁ እያለ ይዘረዝራል በብትን እንጂ በአንቀጽ አይገባም።

ቤዛዊ -(ዊት ውያን ያት ዘውት) የሚቤዥ፤ የሚታደግ ታዳጊ ማርያም ቤዛዊተ ዓለም። እስመ ቤዛዊሃ ነፍስየ አን -(ደራሲ)

ቤዝ -( ቤዛት አብያዝ) ልሕ ኮከብ ኮከበ ጽባሕ ብርሃኑ የሚቦዝ የሚበዘብዝ። አን ቤዝ ኮከበ ጽባሕ አዕይንቲሃ ይመስል ሥርቀተ ቤዝ። በሰዓተ ሞታ ደመነ ቤዝ በከመ ኮከበ ጽባሕ ይፈደፍድ ብርሃነ እምዘተርፉ ቤዛት ሰላም ለአዕይንትኪ ዘተመሰላ ብያዘ -(ቄድር። ገድ -ተክ ስንክ -መስ፲፩ ፊልክ -፪፻፸ ደራሲ አርጋ -፮። ኢዮ፮ -)

ቤዝዎ  ዎት -(ቤዘወ ይቤዙ ይቤዙ ዐረ -ባዘ ሸሸ ዕብ ፋዳ) መቤዠት ማዳን መታደግ ማስጣል ከጭንቅ ባርነት ማውጣት ባለዳ እጅ መግዛት መዋጀት ለውጥ መስጠት፤ ገንዘብን ወይም ራስን እንደ ክርስቶስ በወርቅ እቤዝወክሙ። በነፍስክሙኑ ትቤ ዝውዋ ለነፍስየ መጽአ ይቤዝወነ ምኵሉ በሳነ -(ኢሳ፶፪ -፫። ኢዮ፲፮ - መዋሥ። ዘፀ፲፫ -፲፫ ፴፬ -) በቤዘወ ፈንታ ተቤዘወ ይላል፤ አያሰኝም፤ ያማርኛ ነው ተቤዘውዎሙ ለፂዉዋን። አልቦ ዘይክል ተቤዝዎትየ። ያድኅን ወርቅ ወኢይትቤዘው ብሩር -(ዲድ -፳፩ አርጋ ስንክ -ሐም፬ ዘሌ፳፭ -፴፩ -፴፫ ጴጥ - -፲፰) ቤዘወ የቤዘ ቅጥይ እንደ ኾነ አስተውል

ቤዴቅ -(ዕብራ) የግንብ ንቃቃት ነቁ ሥንጥቁ ወይም ሊናድ የቀረበ፤ ያረገዘ ያዘበዘበ የቤት ግንብ። ያጥር የቅጥር ካብ። ማናቸውም የሚታደስና የሚጠገን ኹሉ ወያጸንዑ ቤዴቀኪ -(ሕዝ፳፯ -፱። ፬ነገ -፲፪ -)

ቤጣ [1]-ስመ ፊደልበየጣ

[2] (ጽር ቤታ) ፊደል ቤት በጽርእና በቅብጥ። ልፋ ወቤጣ። ምንት ውእቱ ቤጣ (ሥር ጳኵ። ኪዳ)

ቤጻ ብጻ -ብጫ ብጫቴ፤ ዐይነቱ የንቍላል ስኳል ደይ የሚመስል አስፈርን እይ

ብሁል -(ላን ላት ብህልት) የተባለ የተነገረ ንግር። አላ ብሁል -(አፈ -ድ፲)

ብሁም -(ህምት) ድዳ የኾነ አፍ እያለው የማይናገር። ብእሲት ብህምት -(ስንክ -ም፰)

ብሑት [1] -(ታን ታት ሕት) ዉሕ የሠለጠነ የተሾመ፤ መብ ያለው። ወደቂቀ ሮንሰ ብሑታን በበ ብሬቶሙ ሳቁኤል ብሑት ዲበ መናፍስት ዛቲ ዕለ ብሕት ህሉት ከመ ወልድ፤ ስፍንት ከመ መንፈስ ቅዱስ -(፩ዜና -፳፬ -፩። ስንክ -ሐም፭ ቅዳ -አት)

[2] -የባተ ብቸኛ የኾነ ብቸኛ ብሑተ ልደት። ብሑት ዘእንበለ ዝማድ። መነኮስ ብሑት ገዳማዊ ብሑት (ኪዳ። ቅዳ ኤጲ ልክ ፫። ስንክ የካ፯)

ብሑእ -(ኣን ኣት ሕእት) የቦካ፤ የበሰለ የሖመጠጠ ምስለ ኅብስት ዘብሑእ ኢትግበርዎ ብሑአ ትዝባሕ በብሑእ ደም ያደረ -(ዘሌ፯ -፲፫ -፲፩ ዘፀ፳፫ -፲፰) በብሑእ ፈንታ ብሒእ ይላል አያሰኝም። ብሒእ ወይን ብሒእ ሜስ ሐምለ ብሒእ -(ዘኍ፮ -፫። -፲፩። ዘፀ፲፪ -)

ብሂል ሎት -(ብህለ ይብል ይብሀል። ዐረ በሀለ፤ ተረገመ። ዕብ ባሄል ደነገጠ) አው

 -ብሂል በዪል መምታት፤ በበትር ማለት መደብደብ፤ ወይም አስቀድሞ መስደብ በነገር መቀንደብ ጽዕለትን ተመልከት። ብሂላና ብላዕ፤ ባማርኛ ይተባበራሉ፤ ብላ ብላ

ብሂም ሞት -(ብህመ ይብህም ይብሀም) ድዳ መኾን፤ አለመናገር ልናገርም ቢሉ አለመቻል እንደ ብት መኾን ይኄይስ ብሂም ምነቢብ በሐሰት። ይብህም ልሳን ብህመ ልሳኑ። ሜጥኩ ገጽየ ወብህምኩ -(ፈላስ ግንዘ። ስንክ የካ፯ ዳን፲ -፲፭)

ብሒር ሮት -(ብሕረ ይብሕር ይብሐር። ዐረ በሐረ ዕብ ባሐር መረጠ) መስፋት መንጣለል፤ መዘርጋት ሰፊ ዝርግ ወርዳም ረዥም መኾን፤ የቦታ የመሬት የርስት የግዛት።

ብኊባኌ -ብኅባኄ ግማ ክርፋት ታው የሚያሰቅቅ የሚጐፈንን። እሬኢ ንስኀተ ሥጋየ ከመ ብኅባኄ አንበሳ -(ኢዮ፮ -) ባለብሉዮች ግን ይል ብርታት ይሉታል

ብኊብኊ -ብሕቡኅ የኖኸቦኸ፤ የቦነቸ ከመ ዕፅ ብኅቡኅ -(ኢዮ፳፬ -፳። ፵፩ -፲፰)

ብሒት ቶት -(ብሕተ ይብሕት ይብሐት፤ ቦሐ) መሠልጠን መሾም መብት ችሎት ምቾት ማግኘት እን ትብሕት አንተ በኵለሄ ወሶበ ብሕትኩ አልእክ ዘይጼውዐከ -(አርጋ - ግብ፳፬ -፳፭).

ብሒእ -ርሾ ሎሰን እይ መጣጣ ይብ ከል የተበላሸ ጠጅ ሖምጣጤ ትጸብ ኅብስተኪ በብሒእ። ወአስተዩ ሒአ ጽም ብሒ ይደልዎ ለቍስል። ወቦ ፃም ብሒእ ዘምሉእ ወመልኡ ፍነገ ምብሒእ -(ሩት፪ -፲፬ መዝ -፷፰ ምሳ፳፭ -፲። ዮሐ፲፬ -፳፱)

ብሒእ ኦት -(ብሕአ ይብሕእ ይብሐእ ዕብ ቦሄእ እጅግ ፈራ ተደነቀ) መቡካት መሖምጠጥ፤ መብሰል። ሐሊብ ዘኢብሕአ ይፈርሆሙ ኢይብሐኡ ስመ ሕብ ዘቅቡል ፍጡነ ይብሕእ -(ግንዘ። ሄርማ -ገ፵፰) በብሕአ ፈንታ ተብሕአ ይላል አያሰኝም። ስከ ይትበሐእ -(ሆሴ፯ -፬። ዘፀ፲፪ -፴፬) በኍበኈ ተመልክት የዚህ መንቲያ ነው

ብሄማ -(ዕብራ። ዐረ በሀኢም) ከብ እንስሳ ኢነባቢ።

ብሄሞት [1]-(ዕብራ) ማሬ የወንዝ አውሬ የባሕር ፈረስ፤ በአፍሪቃ ወንዞች በየሐይቆቿ የሚገኝ፤ ከውሃ እየወጣ ሣርና ቅጠል የሚበላ ታላቅ ገናና ርበተ ወፍራም ንገተ ደንዳና ርበቱ ርባጅ ዐለንጋ የሚኾን መልኩ ያንድስ ድምጡ የፈረስ ያሽካካ ፈረስ የሚመስል። ዲኖ ጅን የባሕር የበረሓ ጐሽ፤ ጠባዩ ያውሬ መልኩ የበሬ ናሁኬ ብሄሞት ዘገበርክዎ ምስሴከ ይበልዕ ሣዕረ ከመ ሕም -(ኢዮ፵ -፲፭)

[2]-በቁሙ፤ የየብስ ዐንበሪ ከባሕር ተፈጥሮ በየብስ የሚኖር ግሩማን አራዊት የሚፈሩትና የሚገዙት ከአራዊት ኹሉ የሚበልጥ መጨረሻ ግዙፍ የእንስሳት ራስ የአራዊት ጉሥ በኵራቸው ቀዳማያቸው በተፈጥሮ የሌዋታን ወንድም ባሏ መስሏ። የሌዋታንን ፍች ተመልከት ባለብሉዮች ግን ዝኆን ይሉታል። ወይትከፈሉ በይእቲ ዕለት ልኤቱ ዐናብርት ዐንበሪ አንስቲያዊት ዘስማ ዋታን ከመ ትኅድር በልጐተ ባሕር ወለተባዕታይ ስሙ ብሄሞት ዘይእኅዝ በእንግድዓሁ በድወ ዘኢያስተርኢ ወስሙ ዴንዳ በምሥራቀ ገነት -(ሔኖ፷ -)

ብሔሞት -በቁሙብሂም ብህመ

ብሔር -(ራት በሓይርት፤ በሓውርት ዐረ ቢሓር በሕረት) ቦታ ፈር ስፍራ በሀገር ውስጥ ያለ ናናሽ ክፍል ይጸብበነ ብሔር በሪ ለነ ብሔረ ንነብር ብሔር እምኀበ ይወፅእ ብሩር። ይቴ ብሔራ ጥበብ ዳም ውአቱ ብሔር። ወበጺሖሙ ብሔረ ዘስሙ ጎልጎታ ወወፅአ ስሙዓቱ በኵሉ በሓውርተ ድያም -(ኢሳ፵፱ - ኢዮ፳፰ - -፲፪ ማቴ፲፬ -፲፭ ፳፯ -፴፫። ሉቃ፬ -፴፯) ብሔር ጥሉል ወፍራም ሥብ ውሃማ መሬት ተክል የተመቸ ብሔር ሥዑር ሣራም የሣር ቦታ መስክ ጨፌ ልከል -(ኢሳ፭ -፩። መዝ -፳፪)

 -ምድር፤ ሀገር ተማ ገጠር፤ አውራጃ ግዛት ታላላቅ ክፍል በስምና በሹም በወሰን በደንበር የተለየ መላይቱ ምድር፤ የብስ ዓለመ ሰብእ አይቴ ብሔርከ ብሔረ ሕያዋን፤ ብሔረ ብንያም መሀኮሙ በሓውርት ኀበ ነበረ ሎጥ በሓውርተ ሕዛብ ውእቱ ተርፈ ብሔር ነሥእዎ ምነ ብሔር -(ዮና፩ -፰። መዝ -፶፭። ኤር፩ -፩። ሢራ፲፮ -፰። ኢሳ፲ -፲፫ ራ፵፬ -፲፯ ፵፬ -፲፬)

 -ሰው፤ ወገን ነገድ፤ ሕዝብ አሕዛብ በቋንቋ በመንግሥት በሕግ በሥርዐት የተለየ። ኵሉ ብሔር መስሐ መፍቅደ ብሔር አንከሩከ በሓውርት መጽኡ ኵሉ ሓውርት ውስተ ብጽ ኵሉ በሓውርት ዘቤተ እስራኤል። በበ በሓውርቲክሙ ደቂቀ ዕጓለ -(፩ነገ -፲፬ -፳፬ ሢራ፴፰ -፴፬። ፵፯ -፲፯ ፍ፵፩ -፶፯ ኤር፪ -፬። መዝ -፵፰)

 -ማይና ምድር ሰማይ ነግሉ ምድር ነልብሱ መላው ዓለም። ላዩም ታቹም ያንድ አምላክ ግዛት ስለ ኾነ በምሳሌ ብሔር ተብሏል ይቤ እግዚአ ብሔር -(እግዚአብሔር) ሰማይኒ መንበርየ ወምድርኒ መከየደ ገርየ ስመ ዚኣየ ውእቱ ኵሉ ዓለም በምልኡ -(ኢሳ፷፮ - -፪። መዝ -፵፱)

 -ጊዜ ሰዓት፤ ወራት ባመትና በወር በዕለት ያለ ፍል ክረምት ብሔር ስመ ግህ ብሔሩ። ወጸቢሖ 'ብሔር እስ ጸብሐ ብሔር ጽልመት ብሔር መስየ ብሔር -(፩ዕዝ - -፲፫ ግብ፪ -፲፭ ፳፯ -፴፫። ፩ነገ -፳፭ -፴፮ ሢራ፳፫ -፲፰ ገድ -ተክ)

 -የመጽሐፍ ክፍል ታላቅ ዐቢይ አንቀጽ አንድ ክፍል መጽሐፍ ለብቻው አንድ ተብሎ የሚቈጠር ውስጡ ብዙ ምዕራፍ ያለበት፤ እንደ ኦሪትና እንደ ነገሥት፤ እንደ ወንጌል እንደ ሐዲሳት ያለ ይቤ በኦሪት ውስተ ልስ ብሔር ዘሌዋውያን በውስተ ዳግም ብሔረ ሪት ለኦሪት ባቲ ምስቱ ብሔር። አርባዕቱ ብሔረ ነገሥት ክፍል ኃምስ እምዳግም ብሔር ዘመጽሐፈ ገሥት -( - - - - -፩። አብጥ -፹፩። አቡሻ -፲፱)

ብህመት -ድዳ መኾን ድዳነት ብህመተ ሳን። ተፈትሐ ልሳኑ ምብህመት -(መጽ -ምስ ስንክ -)

ብሕባሔ -መፍጠር መፈጠር፤ አፈጣጠር ፈጠራ ተፈጥሮ ዕብራይስጡ ሜሖሜር ቆራጽቲ ያለውን፤ ግእዙ ተቀረጽኩ ተገለፍኩ ማለት ፈንታ እምጽቡር ብሕባሔከ ወእምኔሁ ቅሳሜነ ይላል፤ -(ኢዮ፴፫ -) ከዚህ በቀር በሕብሐ ብሎ ፈጠረ የሚል አይገኝም

ብኅባኄ -መፈጠርበሕብሐ።

ብኍባኌ ብኅባኄ -ግማ ክርፋት ታው የሚያሰቅቅ የሚጐፈንን። እሬኢ ንስኀተ ሥጋየ ከመ ብኅባኄ አንበሳ -(ኢዮ፮ -) ባለብሉዮች ግን ይል ብርታት ይሉታል

ብሕታዌ -ብቻ መኾን ብቻ ብቸታ ብቻነት ትምህርት መዜንው በውስተ ሐዊር ወበብሕታዌ ሰላም ብሕታዌሁ። ብሕታዌ ብረት -(ፈላስ። ስንክ -ጥር፳፪ ግን፲፭)

ብሕትው -(ዋን ዋት ቱት) ብቻውን የኾነ ብቻውን የሚኖር፤ ብቸኛ ለብቻው የቆመ የተለየ ገላ አካል ውነት ትኩን ብሕቱተ በእንተ ጸሎት ብሕቱትየ -(ኪዳመዝ -፳፩ ፴፬)

ብሕትውና -ባሕታዊነት፤ ብቸኝነት ፍጹም ምናኔ በእን ዘከመ ይኄይስ ሥርዐተ ብሕትውና ምሥርዐተ ማኅበር ለመደ ብሕትውና በኣተ ብሕትውና -(ፊልክ -፩። ስንክ -ሐም፲ - - -)

ብሕትውናዊ -የብሕትውና፤ የባሕታዊነት፤ ግብር አናዎር ሕግ ሥርዐት። ምንኵስና ብሕትውናዊት -(ገድ -ተክ)

ብህኑን -(ናን ናት ንንት) የባነነ የበነነ የባከነ፤ ብኑን ከንቱ በናና በካና ፍሉጥ ብዑድ ቃላተ ሕስወ ወብህኑነ ታርኢ ይሜህሩ ብህኑነ ሥጋዌ ዘእንበለ ፅምረተ መለኮት ብህኑን ትስብእቱ አምድማሬ መለኮቱ ወኢብሕትው መለኮቱ ምትስብአቱ -(ቄር -ጰላ። መጽ -ምስ)

ብሕአት -መቡካት፤ አቦካክ ቡሖነት ርሾ -(ማቴ፲፮ -፲፩ -፲፪)

ብሕእ -(ኣት) ቡሖ ርሾ -(ሉቃ፲፪ -) ብሑእ ፈንታ ብሒእ እንደሚል በብሕእ ፈንታ ብሑእ ይላል ጥሬን በቅጽል ቅጽልን በጥሬ መለዋወጥ የጣፊና የመላሽ ሕተት ነው። ወለእመ ኮነት ቀዳሚሃ ቅድስተ ወብሑእኒ ቅዱስ ከማሁ ቡሖ ሊጥ። ኅዳጥ ብሑእ ብዙኀ ሐሪጸ ያብሐእ አንጽ እንከ ሑአ ብሉየ ምኔክሙ ሑአ ዘነሥአት ብእሲት ወኀብአቶ ውስተ ሐሪጽ ርሾ -(ሮሜ፲፩ -፲፯ ፩ቆሮ - - -፯። ማቴ፲፫ -፴፫)

ብሕውስ -(ዕብ ባእሻህ) አብሾ አስተናግር የዶሮ ስ፤ ግማታም ቅጠል በባድማና ድብድባ የሚበቅል ቋያ መጥፎ ቡቃያ ወኮነት ሀገር ድወ ወበቈለ ላዕሌ ወአሜከላ ወኮነት ብሕውሰ ወምጕሕያ -(መቃ -ገ፲፫)

ብለኔ -(ጽር ባላኔዎን ዐረ ሐማም) መታጠቢያ መነከሪያ የውሽባ ቤት ፍል ውሃ ወይም ዐጣቢው ባለቤቱ። ኢይባእ ቤተ ብለኔ ይበውእ ቤተ ብለኔ ዘይትኀፀብ ምስለ ንስት በቤተ ብለኔ -( - -፳፮ -፭። ቀሌ ቀኖ -ሎዶ -፳፱)

ብሉሕ -(ሓን ሓት ልሕት) የዳነ የወጣ ያመለጠ። ብሉሕ መቅሠፍት -(አዋል)

ብሉል -(ዕብ ባሉል) ቅይጥ፤ ውጥንቅጥ ነከርት የራሰ የለዘዘ ርጥብ

ብሉር -(ዐረ በሉር ሱር ቤሉራ ጽር ቢሪሊዎን) ብርሌ ብርጭቆ። ዕንቍ ፈርጥ የብርሌ ይነት -(ክብ -ነገ -፲፯) ቢረሌን መልከት ከዚህ ጋራ አንድ ነው

ብሉቅ -(ቃን ቃት ልቅት) የባለቀ ያደገ የላቀ ለዘር የበቃ። -(ተረት) ያታወበ እጅ ያልባለቀ ልጅ

ብሉት -(ታን ታት ልት) የተበለተ የተለየ ልዩ ብቸኛ

ብሉዕ -(ዓን ዓት ልዕት) የበላ የጠገበ የተበላ፤ የተቃጠለ -(ሄርማ -ገ፷፯፷፱)

ብሉየ መዋዕል -ዘመኑ ያረጀ ዘመን ያስረጀው የዘመን አሮጌ ሽበታም -(ዳን፯ -)

ብሉየ መዋዕልና -ቀዳማዊነት ቅድምና ዓለም ይፈጠር ዘመን ይቈጠር ቅድመ ዓለም መኖር ዕሩያን በመለኮት ወበህላዌ ወበብሉየ መዋዕልና ባሕርይ በአካል በቅድምና -(ሃይ -አበ)

ብሉይ -(ያን ያት ሊት) ቁሙ ያረጀ ያፈጀ አሮጌ አንቲካ ጥንታዊ ቀዳማዊ የዱሮ የቀድሞ የፊት፤ ሕግ ኪዳን መዋዕል ዘመን፤ መሣሪያ ልብስ መጽሐፍ የመሰለው ኹሉ ብሉይ መጽሐፍ። ብሉይ ብእሲ። ሕግ ብሊት መጻሕፍተ ብሊት። ጻድቃነ ብሊት። ብሉያተ ረሰይኮን መዋዕልየ -(ሮሜ፯ -፮። ኤፌ፬ -፳፪ - - -፩። ስንክ -ሐም፲፩ ነሐ፰ መዝ -)

ብላተንዓሻ -(ዐረ በናት ሺን) ብላተ በናት አዋልድ ታናናሽ ዋክብት ንዓሻ ነዕቪን ታላቅ አባት ኮከብ፤ ወቦ የሚባል ባለብዙ ጭፍራ። ባለብሉዮች ጨረቃ ይሉታል። ተአምርኑ ዜሃ ብላተንዓሻ -(ኢዮ፴፰ -) ዕብራይስጡ ግን ታወፅእኑ ማዛሮተ በጊዜሁ ወትመርሖኑ ዐይሽ ምስለ ዋልዲሁ ይላል ማዛሮት መገብተ አውራኅ ናቸው

ብላታ ብላቴና -(ዐማርኛ) ሥልጡን ስብቅል አሽከር ብሳቴን ጌታ እግዚእ ሥሉጥ መልአከ ምክር መጋቢ

()          ብላዕ -(ዓት) ብላቶ ትራፊ ብላዐ ርዌ።ብላዐ ቍንቍ ብላዐ -(ዘሌ፭ -፪። -፳፬ ኢዮ፳፯ -፲፰ ናሆ፩ -) በብላዕ ፈንታ ብልዕ ይላል ያሰኝም።

ብሌን -(ዐረ ሚል ጽር ሚሊ) የኵል መኳያ ሣር ወይም ሌላ ነገር ለዚሁ ብቻ የተሠራ ያይንን ማሚቶ ብረቲቱን ብሌን ማለት ዚህ የወጣ ነው። እንዳይን ብሌን ይጠብቅኽ እንዲሉ። ድባራተ ኵል የኀልቁ በብሌን ወከማሁ ድሜሁ ብእሲ በዕለታት -(ትእ -ጴጥ)

-ስመ ነገድ ቋንቋ በሐማሴን ክፍል ውስጥ ያለ

ብልኅ -(ኃት) [1]- ስለት ሹለት የሰይፍና የጦር አፍ አንደበት። ብልኀ ሰይፍ ትነድድ ቅትሎሙ በብልኀ ሰይፍ። በብልኀ ሰይፍ ሙንቱ ረከቡ ክሊለ ብልኀ ናት ዘተረግዘ ቦቱ እግዚእነ በብልኀ ናት ቦሁ ደጐጸ -( - -፵፮። አፈ -ተ፲፩ ስንክ -ኅዳ፭ ግን፳፭)

[2]-ብልኅ -(ዐማርኛ) በቁሙ አስተዋይ ዐዋቂ።

ብልኀት -ቁሙ መስላት መሾል መፍጠን አሰላል አሿሿል አፈጣጠን ስለት ሹለት ፍጥነት ብልኅነት ፈጣንነት ወእምቅድመ ያስተርኢ ብልኀተ መብረቅ፤ ስለቱ ፍጥነቱ ብልጭታው -(ቅዳ -ግሩ)

ብልባሌ -ማርጀት ማለቅ እርጅና አሮጌነት። ጨርቅ፤ አሮጌ ማቅ፤ ላቂ ውዳቂ ረንጮ ቅርንጥስ የሐዘን የድኽነት ልብስ። ወኣቀንተክሙ ብልባሌ ውስተ ሐቌክሙ -(ዓሞ፰ -፲። ኢሳ፳፪ -፲፪ ጥበ -ጦቢ አርጋ -)

ብልቲት -ብልጩት እዝኅ ሥጋ የሚቈርጥ የሚበልት ስለታም ደንጊያ፤ እዝኅን እይ

ብልዐት -መብላት፤ መበላት፤ አበላል። ብልዐተ እክል። ብልዐት ብልዐተ ዕፄ ረከቦሙ -(መዝ -፶፪ ኩፋ -፳፫ ኢዮ፬ -፲፬)

ብልየት -ማርጀት፤ እርጅና አሮጌነት። ሐደሶ ቤት ምብልየቱ ተሐደሳ እምብልየት ብያተ ክርስቲያናትርቱዕ ናሰስል ምላዕሌን ዘንተ ብልየተ -( - -፴፫ -፬።ስንክ -ግን፩ አፈ -ተ፲፬)

ብሉት -(ታን ታት ልት) የተበለተ የተለየ ልዩ ብቸኛ

ብሱል -(ላን ላት ስልት) የበሰለ የተቀቀለ ቅቅል ረከቦ ውእቱ ጸብኅ ፍሉሐ ወብሱለ -(ስንክ -ታኅ፲፩) ኢብሱል በማለት ፈንታ ብሱል ይላል -(ዘፀ፱ -፴፪)

ብስሎ -ብስል ቅቅል አንፊላ ብስሉን ቅቅሉን። ጥራዮ ወኢብስሎ በማይ -(ዘፀ፱ -)

ብሥራታዊ -ለምሥራች፤ ወንጌላዊ ሠናየ ዜና። ሰላም ብርኤል ብሥራታዊ። ብሥራታዊ ማርቆስ -(ደራሲ አቡሻ -)

ብሥራት -(ታት) ቁሙ ምሥራች ዲስ ገር ደስ የሚያሰኝ ወሬ ስብከት ትንቢት፤ ወንጌል ትሥጉተ ቃል ብሥራተ እግ በልሳነ ገብርኤል ዘአብሠራ ቅድስት ድንግል ብሥራተ ማቴዎስ -(አቡሻ -፴፰። ማቴ -) ብሥራት እያለ ይዘረዝራል የምሥራች ደስ ይበልኽ ማለት ነው ብሥራት ንጉሥ -(ገድ -ተክ) ንኡስ ገባብ -(ዕር፲፫ -ቍ፻፲፩)

ብስራት -ባሶርበሢር በሠረ ብሥራት ባሦር

ብረት -(ዐማርኛ) በቁሙ፤ ጺንን ተመል ብርቱ ማለት ዚህ ወጥቷል።

ብሩህ -(ሃን ሃት ርህት) የበራ የጠራ ነጭ የታየ ግልጥ  ደመና ብሩህ ካህናት ብሩሃን ከመ ፀሓይ ከመ ይኩና አዕይንቲከ ብሩሃተ ዕለ ዝንቱ ቤት። ጽዕዱት ወብርህት -(ማቴ፲፯ -፭። መዋሥ ፪ዜና - - ማሕ፰ -)

ብሩር [1]-(ራን ራት ርርት) የተመረጠ የተለየ ልቅም ጥሩ ነጭ ማዕደን

[2]-( በራውር ብሩራት) ብር ክቡር ገንዘብ የወርቅ ምክትል ብሩር ጽሩይ ብሩር ኅሩይ ሠላሳ ብሩር። ህየንተ ወርቅ ወብሩር ጸዐዳ -(መዝ -፲፩ ምሳ፰ -፲፱ ማቴ፳፮ -፲፭ ደራሲ)

ብሩክ -(ካን ርክት) የበረከ የተንበረከከ እንብርክ

ብሩዝ -(ዛን ዛት ርዝት) የተበረዘ የተቀላቀለ፤ ቅልቅል፤ ቱሱሕ

ብራና -(ዐማርኛ። ጽር ሜምብራና) ቁሙ ብርሃና በርሀን ተመል ኅልፍ ሐደ ብራና ወእምዝ ኀሊ ሰመንተ አዕማደ ወዐሠርተ ወሠለስተ መሥመራተ ትረክብ መትልወ ዝንቱ ቃል -(አዋል)

ብሬት እብሬ -ፈረቃ ፈንታ፤ ተራ ሞን፤ የጊዜ ክፍል አመ በጽሐ ዕለ ብሬታ ለአስቴር ከመ ትባእ ንጉሥ ወፈጺሞ መዋዕለ ብሬቱ ተወ ቤቶ ሊቀ ካህናት ዘእብሬቱ ይእቲ ዓመት። መዋዕለ ብሬትከ እብሬተ ርትዕ ወሣህል ብሬተ ሰዐታት -(አስቴ፪ -፲፭ ሉቃ፩ -፳፫ ዮሐ፲፩ -፵፱። ስንክ -ጥር፯ ዜና -፳፫ -፴፪) አንዳንድ ጊዜም በበእንተ ፈንታ እየገባ ለና ምክንያት ይኾናል ከመ ትሕየው ፍስየ በእብሬትኪ። ይትቀነይ ሎቱ በእብሬትከ -(ዘፍ፲፪ -፲፫ ዮዲ፲፩ -)

ብርሐት -በራ ቡሓ መኾን ቡሕነት በራነት መላጥነት። ሽሽት በረሓ መግባት -(ዘሌ፲፫ - -፵፫) ብርሐት ትፃእኪ። ውስተ ኵሉ ርእስ ብርሐት። ጴጥሮስ ቦቱ ብርሐት -(ኢሳ -፳፬ ፲፭ -፪። ቀሌ)

ብርሃነ ልብ -ጥሩ ዕውቀት፤ ጥበብ ትምርት መንፈሳዊ ሀብት -(ፊልክ)

ብርሃነ መብረቅ -ነጸብራቅ ብልጭታ፤ ብልጭልጭታ -(ዕን -፲፩)

ብርሃነ ስብሐት -የክብር ብርሃን ጮራ ምዕዛር -(ዕብ፩ -)

ብርሃነ ዐይን -ማሚቶ ብሌን ጥራት ሩነት -(መዝ -፴፯)

ብርሃነ ገጽ -ይቅርታ ቸርነት፤ ባለሟልነት የደስታና የፍቅር ምልክት -(መዝ -)

ብርሃና -ብራና የተፋቀ የተራመመ ነጭ ሰሌዳ ማእስ ወይም ወረቀት ርታስ ብርኒንና ብራናን ተመልከት የዚህ ዘሮች ናቸው

ብርሃናዊ -ብርሃናም ተፈጥሮው ከብርሃን የኾነ ንጹሕ ብሩህ ጽሩይ ጸዐዳ። መልአክ ብርሃናዊ። ብርሃናውያን። ብርሃናዊት -(ቅዳ -ሕር ክብ -ነገ ገድ -)

ብርሃን -(ናት) ዝኒ ከማሁ በቁሙ፤ መዓልት መብራት፤ ፀሓይ ጨረቃ ኮከብ፤ የእሑድና የረቡዕ ፍጥረት -(ዘፍ - - - -፲፬፲፰) ወይከውን ብርሃነ ወርኅ ከመ ብርሃነ ፀሓይ ብርሃነ ማኅቶት ወበእደዊሆሙ ይጸውሩ ብርሃናተ ሳት -(ኢሳ፴ -፳፮ ቃ፰ -፲፮ ተረ -ኤር)

 [1]-ዐይን ማየት። ጸጎከ ዕዉር ብርሃነ -(ስንክ -ነሐ፲፭)

[2]-ብርሃን -(ዐረ ቡርሃን) መምህር አብነት፤ መፈክር መተርጕም ገልጦ የሚያስረዳ -(ማቴ፭ -፲፬ አቡሻ -፶፫)

ብርህርህት -ብርህርህት የለምጽ ቃያ ነጫጭ ነቍጣ ጠብጣብ -(ዘሌ፲፫ -፴፰)

ብርስኔ -ብርስኔባርሰነት፤ምርስኔ።

ብርስን -ብርስን -(ዐረ ቡልስን ዐደስ ዕብ ዐዳሻ) ምስር ጥሩ ያበባ እኸል ወጥ የሚኾን ቅንጣቱ ታናናሽ ቀይ ምስራዊ ዘእምስር ማልት ነው፤ የግብጥ ብርስን ካገር ኹሉ ብርስን የሚያምር የሚበልጥ በውድ የሚሼጥ ስለ ኾነ የሻም ዐረብ ደስ መስሪ እንዲል ምስራዊ ሲል ተርሙስ ግብጦ እንዲባል ብርስንም ምስር ይባላል፤ ጥንተ ስሙ ደስ ምርስኔና በብርስኔ ሞክሼ ወደ ባርሰነት ኺዷል። ፪ኛም ስለ ቅላቱ ግብጥ ይባላል ግብጥ ምስር እንዲሉ። ልባም ሴት በጥሩ ዐዋዜ ርታ ስታቀርበው በቅላት ላይ ቅላት ተጨምሮለት መልኩ ጁሕ ጃዊ እንድኪ ፍሕሶ ረብ አንቀልባ የሲፍ አበባ ይመስላልና፤ የምሥራች ለሚል ምስር ብላ ማለት ለዚህ ነው የምሥራች ቅሉ ምስር ወጥ መጥቷል ሽማግሎችም የምስር ወጥ ብኵርና የሚያሼጥ ይሉታል -(ዘፍ፳፭ -፴፬ ኩፋ -፳፪)

ዐተረ ወብርስነ ገራህት ዘምሉእ ብርስነ -(፪ነገ -፲፯ -፳፰ ፳፫ -፲፩ ሕዝ፬ -) የምስር ይነት ነው ከዚህ ሌላ ያይጥ ምስር የገመል ምስር የሚባል አለ ይበልዑ ሠለስተ ብርስነ -(ስንክ -ኅዳ፲፫)

ብርቅ -ቁሙ ወትሮ የማይታይ በኹሉ የማይገኝ ድንቅ ሥራ ታምራት መንራት።

ብርቡር -(ራን ራት ብርት) የተበረበረ የተዘረፈ፤ ውስጠ ክፍት ባዶ

ብርባሬ -(ሳቢና ጥሬ ዘር) መበርበር -(ጥበ) መበርበር አበራበር ብርበራ ብዝበዛ ዘረፋ ወረራ -(አዋል)

ብርት -(ታት በሪር በረ፤ ብሩር) ቁሙ የብረት ወገን የብር ምክትል ብርቱ  ማዕደን መዳብ ንሓስ መዳብ ቀዩ ንሓስ ብጫው ብረ ብርት ወኀጺም ብርት ርሱን ብርተ ሊባኖስ። ፍጽም ዘብረት -(ዘፍ፬ -፳፪ ሕዝ፵ -፫። ራእ፩ -፲፭ ኢሳ፵፰ -)

ብርትኳን -(ዐረብ) በቁሙ፤ በኵረ ሎሚ ጥሩ ጥፍጥ ተክል

ብርኒ -ድመት የጽርኒ ይነት። ዐይነ ብር ይናማ ማለት ነው ለድመት ያበሩላት እንዲሉ።

ብርእ -–መቃ ሸንበቆ፤በሪዕ በርዐ ብርዕ

ብርዕ -( አብራዕ) ሸንበቆ የጐሽ መቃ የሸንበቆ ይነት ውስጠ ክፍት ገዳ ቅልጥም ቁሙ የጸሓፊ ብር የገብስ የስንዴ ብር ገለባ ቈሻሻ። በትረ ብርዕ ብርዐ ባሕሩስ አብትር ፅቡሳን ወአብራፅ ቅጥቁጣን

ምዳ ወአብራዒሃ -(ኢሳ፴፮ -፮። -፴፩። መጽ -ምስ ዘፀ፳፭ -፴፩፴፮) ሰብዐቱ ሰብል ዘሠዊት ሠረጹ እምአሐዱ ብርዕ ብርዐ ይመስሎ መፍጽሕ ሣዕ ወብርዕ ዘይየብስ እሳ እንተ ትበልዕ ብርዐ -(ዮሴፍ። ኢዮ፵፩ -፳። ፲፫ -፳፭ ዮኤ፪ -፭። ዓብድ -፲፰ ዘፀ፭ -፲፪ ፲፭ -) ብርእ ተብሎ እንደ ዕብራይስጡ በአልፍ ጣፍ ግን የማግስኞ ፍጥረት ያሰኛል -(ዘፍ፩ -፲፩ -፲፪)

ብርኵታ -(ዐማርኛ) ቁሙ ፍም የሚበስል ርሚጦ ቂጣ ሲበሉት የሚያጠግብ የሚመክት የሚበረክት፤ የጭብጦ ዐይነት። በላዕሌሁ ያስተርኢ ብረ በሊታ፤ ዘዕውሩ ተወልደ ብርኵታ -(ቅኔ)

ብርኵት -የደንጊያ ግርንቡድ፤ ወይም የብረት ባድ ወቦኡ ልኤቱ ምአግብርቲሁ በሌሊት ወአንበሩ ዲበ ገጹ ለበም ንጉሠ ርስ ብርኵተ ወነበረ አሐዱ እምኔሆሙ ዲበ ርእሱ ወካልኡ ገሪሁ እስመ ውእቱ ረጋዊ ዐቢይ ወሞተ ሶቤሃ -( - - -ገ፵፰)

ብርክ -( ብረክ አብራክ) ልበት ጭን ማቀፊያ መታጠፊያ መንበርከኪያ። አዕደወኒ ስከ ብርክ ወደክመኒ ብረክየ በጾም። ብራኪከ እለ ውተራ ስግደተ ሐቂፍ በአብራክ። በእንተ ብራኪሃ እለ ሐቀፋከ -(ሕዝ፵፯ -፬። መዝ -፻፰ ደራሲ አርጋ ፩። ሳታት) ብራኳ ብርኵማ ማለት ከዚህ የወጣ ነው

ብርዝ -(ትግ በቲሐ) በቁሙ ተሓ ለጋ ጌሾ ያልበዛው ያልበሰለ

ብርያል -(ጽር ቤሪያል) የሰይጣን ቤልሖርእን እይ ከዚህ ጋራ ንድ ነው -(ዕር -ኢሳ፩ -፰። -፬። -፲፩ -፲፫ - -፲፮ -፲፰ - -፲፭ )

ብርያሚን -ሕጹጻንድርያሚን

ብርፎሪኮን -(ጽር ፕሮፎሪኮስ) የትቢትና የስብከት የተግሣጽ ቃል ጩኾ ንት አሰምቶ የሚናገሩት። ወብርፎሪኮንኒ ውእቱ ቃል ዘሰምዕዎ ቢያት ምእግዚ ወውእቱ ቃለ ትንቢት -(ሃይ -አበ -ጎር)

ብቁዕ -(ዓን ዓት ቍዕ) የበቃ የተጠቀመ ባለጥቅም -(ሄርማ) ዳግመኛም በብቁዕ ፈንታ ባቍዕ ይላል አያሰኝም። ባቍዐ ረስየኒ ባቍዐ ሎቱ ጸግዎ -(ሄርማ። መስተ)

ብቁጽ -(ጻን ጻት ጽት) የተጫረ የመረተ፤ የበሰለ  የሟከከ የተንደረከከ ረከቡ ፍሕመ ብቁጸ አንጻሕኮ ለኢሳይያስ በፍሕመ አሳት ብቁጽ -(ዮሐ፳፩ - ጥበ - ስንክ -ታኅ፳፯። ሠኔ፲፬ መጽ -ምስ)

ብቍዐት በቍዔት -(ታት) መብቃት፤ ብቃት መጥቀም መጠቀም አጠቃቀም ጥቅም ትርፍ ረብ ርባታ ጠቀሜታ ኢይክል በቍዔታ ለነፍሱ ኢይከውነከ ለበቍዔትከ ተፈጸመ ነሢአ በቍዔት ባቲ። ምስለ በቍዔታት። ስመ ጾም በቍዔት ባቲ ከመ ያርዒ በየ በቍዔታ ሕማማት -(ሢራ፴፯ -፲፬ ፪ነገ -፲፰ -፳፪ - -፳፰ ድጓ አፈ -ድ፰)

ብቃው -አፍ ክፍቱ ዋሻው የሚጮኸው የሚናገረው።

ብቅወት -መከፈት፤ አከፋፈት ፍትነት።

ብቅው -(ዋን ዋት ቁት) የተከፈተ የተለቀቀ ክፍት ልቅ ለቃቃ አፈ ብቅው ለውኂጥ ብቅወ ርዔ ወአፍ -(አርጋ -፩። ደራሲ)

ብቱል -(ላን ላት። ዐረብ) ድንግል፤ ያላወቀ ወንድ ባተሌ ፈት መዐስብ ሚስቱ ሙታ ወይም በነውር ተፈታ ብቻውን የሚኖር ድንግላይ ማለት ነው

ብቱክ -(ካን ትክት) የበተከ፤ የተበተ የተቈረጠ የተበጣጠሰ ብጥስጥስ። መሥገርት ብቱክ አሣእን ብቱክ -(ኢሳ -፲፱ -፬። ኢያ፱ -)

ብትከት -መቍረጥ መቈረጥ መበጠስ፤ አበጣጠስ ብጠሳ ብጥስነት በይብሰት ፈንታ ብት ይላል ስሕተት ነው እለ አልቦሙ ብት -(መሳ፲፮ - -)

ብትክ -አባላ የተመታ ጥንብ ውዳቂ ርዶ የሰነበተ -(ዘሌ፲፬ - ግብ፳፩ -፳፭)

ብነት -(ዕብ ምናት ሱር ምናታ ክፍል ዕድል) ዐሥራት፤ እጅ መንሻ በረከት በፈቃድ የሚሰጥ ስጦታ እንቍጣጣሽ ገብረ ላም ያክፋይ የጦም የባል የሸማኔ የቀጥቃጭ የመጣፍ ገላጭ ይህን የመሰለ ኹሉ -(ግብ፲፱ -፲፮ -፲፱)

ብናሴ -ጨረቃ የጨረቃ ስም። እብላንና ኤራስን ተመልከት

ብንት [1]-(ዕብ ባት ዐረ ቢንት ሱር ባዲታ) ልጅ ወለት እንስት ቄብ ልጃገረድ

[2]-(ዕብ ኢሾን) ያይን ማሚቶ ጥቍሩ ብረቱ ብሌኑ እንደ መስታዮት የሰው መልክ የሚታይበት፤ ብርሃን የሚሣልበት። ዕቀበኒ ከመ ብንተ ይን። ብንተ አዕይንቲሁ ይሬኢ ጽልመተ ብንተ ዕይንቲሁ ሕል ታረምም ብንተ ዐይንኪ -(መዝ፲፮ -፱። ምሳ፳ - ስንክ -ታኅ፲፩ ስቈ፪ -፲፰)

ብዑል -(ላን ላት ልት) ከበ የበለጠገ የዘመነ የጌተየ ብዙ ገንዘብ ያለው ዕደው ብዑላን። አንስት ብዑላት ሀገር ብዕልት ልቦ ብዕል ዘይፈደፍድ እምነፍስ ብዕልት -(ሢራ፵፬ -፮። ኢሳ፵፪ -፬። ፴፫ - ፈላስ) በብዖል ፈንታ ባዕል በባዕል ፈንታ ብዑል ይላል ፍችው አንድ ነው -(ራእ፪ -፬። -፲፯)

ብኡስ -(ሳን ሳት እስት) የባሰ የከፋ የተጠላ ክፉ መጥፎ። ርሑቅ ግዱፍ በማለት ፈንታ ብኡስ ይላል አያሰኝም -(፪ነገ -፲፬ -፲፱)

ብዑድ -(ዳን ዳት ) የተለየ ልዩ ሌላ ዐይነት ሩቅ ጥልቅ ረቂቅ ተፈልጦ ማእከለ ሮን ወማእከለ ክርስቶስ ብዑድ ፈድፋደ ማሁ ብዑዳን ብዙኃን። ብዑድ ሥነ ሕይ። ብዑድ እምኅሊና -(አፈ -ተ፲፩ ቄር -እስት ቅዳ -ግሩ)

ብዒል ሎት -(ብዕለ ይብዕል አው በዐለ ይቤዕል ይብዐል። ዕብ ባዐል ዐረ በዐለ ሱር ብዓል) መክበር መበልጠግ መጌትየት ብዙ ገንዘብ ማግኘት መላቅ መብበለጥ በሀብት ማደግ። ሚስት ማግባት ባል መኾን ድይኒ ወብዒልኒ ምኀበ እግ ሠያጢ ወሰካሪ ይብዕል። ዘይብዕለከ። ምንት ይብዕላ ጥበብ ይብዕል ወሬዛ ድንግለ -(ሢራ፲፩ -፲፬ ፲፱ -፩። -፪። ጥበ፰ - ኢሳ፷፪ -) አካኼዱ በጥሕረና በጸዐለ መንገድ ስለ ኾነ በዐለ ይቤዕል ይቤዕል ይገኛል ኹለተኛም በብዕለ ፈንታ ተብዕለ ይላል፤ አያሰኝም እለ ይትበዐላ ደርገ -(ስንክ -ሐም፳፯)

ብኢስ ሶት -(ብእሰ ይብእስ ይብአስ። ዕብ ባአሽ፤ ገማ። ዐረ በኢሰ) መባስ መጽናት፤ መክፋት፤ ማገርሸት፤ መቈጣት እየባሰ መኼድ መጕዳት። መጠላት ማስጠየፍ፤ ማስቀየም፤ የደዌ የቍስል የጠባይ የግብር የክፉ ነገር። በሽታ ቢስ ማለት ዚህ የወጣ ነው ወእመሂ ርመምኩ ይብእሰኒ ሕማምየ ዘላዕለ ኃጥኣን ይብእስ ምስብዒተ ዝንቱ ኵሉ። ይብእሰከ ረጊፅ ውስተ ቀኖት በሊኅ ብእሶ ንጉሠ ፋርስ እበድ ዘይብእሶሙ -(ኢዮ፲፮ - ሢራ፵ -፰። ግብ፱ -፭። ፬ነገ -፲፯ -፬። ፩ጢ - -)

 -ማደግ መጐልመስ፤ አካለ መጠን ማድረስ፤ መግነን፤ ፍጹም ጐበዝ መኾን። መድፈር መጨከን መቀልጠፍ መፍጠን፤ ያርበኛ ተብዐን እይ የዚህ ጎር ነው

ብዒር ሮት -(በዐረ ይብዕር ይብዐር። ዕብ ባዐር) ርሶ ብላት፤ ማብላት ማቃጠል ከብትን እሳትን ወደ ርና ወደ ቋያ መስደድ መልቀቅ። ሞኝ አላዋቂ መኾን ከዚህ የተነሣ ከብት እንስሳ መባል ማረስ መቁፈር መማስ መመንቀር፤ መደደቅ መደንጐር ገብር ገበሬ መኾን።

ብዒድ ዶት -(በዐደ ይብዕድ ይብዐድ ዐረ በዒደ ራቀ) ማባድ ባዕድ ማድረግ መለየት መነጠል ማራቅ ማስገለል፤ መለወጥ መቀየር ሌላውን በሌላ ወይም ያነኑ አንዱን፤ እንደ በትረ ሙሴ ዘአመ በዐደ ምቅድሜሁ ለአቤሜሌክ መዪጥ ርእሶ ውበዒድ ምፍጥረቱ -(አርእስተ -መዝ -፴፫ መጽ -ምስ) አንዳንድ መጽሐፍ በበዐደ ፈንታ አብዐደ ይላል ያሰኝም ሰብአ ማነ ይሬስይዎ ወያብዕድዎ ምወልድ -(ቄር -ጰላ)

ብዔል -(ጽር ቤኤል። ዕብ ባዓል) ዝኒ ከማሁ፤ ስመ  ጣዖት ሞአባውያን የሚያመልኩት። ብዔል ፌጎ ብዔል ጣዖቱ፤ ፌጎር ሥርዐቱ። ፌጎርን ተመልከት -(ዘኍ፳፭ -፫። ዘዳ፬ -፫። መዝ -፻፭)

ብዔል ዜቡል -(ጽርእ ወዐረ ባዓል ዝቡል) የሰይጣን ያጋንንት አለቃ ብዔል ዓል ዜቡል መንገድ ቤት በተገናኝ መሪ አሳዳሪ ባለቤት ማለት ነው -(ማቴ፲፪ -፳፬ -፳፯) በዝብል ዘይቤ ሲፈቱት ግን የጕድፍ ጋኔን ልክስክስ ድፍ ሰራዊቱ ከሰማይ ተጠርጎ የወደቀ ድፋም ምላቃ የጕድፎች አለቃ ያሰኛል ምስጢሩ ከሐራውያ ይሰማማል ዘበለንና ዜቡልን ተመልከት

ብዕል -(ላት) በቁሙ፤ ብልጥግና ባለጠግነት፤ ክብር ድልብ ብዙ ገንዘብ። ብኩኅ ብዕልየ ብዕል ዓለማዊት። ብዕል ዘይትዐቀብ በኀበ ዘአጥረየ -(ኢዮ፴፩ -፳፭ - -፲፰ -፩። መክ፭ -፲፪)

 -ምላት ስፋት፤ ብዛት ብዙነት። ብዕለ ስብሐቲሁ ብዕለ ጥበቢሁ -(ሮሜ፱ -፳፫ ፲፩ -፴፫)

ብእሰት -መባስ መክፋት አባባስ አከፋፍ ብሶት ችግር።

ብእሲ -(ዕብ ኢሽ) ልማሳ ይለኛ ወጣት የ፳ የ፴ ዓመት ጐበዝ ምሉ ባል ተባት ወንድ ውነት ተፈሣሕ ብእሲ በውርዙትከ ወአመ ኮንኩ ብእሴ ነሣእኩ ብእሲተ ኮነ ብእሴ ወተስቅለ ብእሲ ምስለ ብእሲቱ ትወልድ ወልደ ብእሴ። አስመ ወለደት ብእሴ እብል በእንተ ብሉይ ብእሲ -(መክ፲፩ -፱። ቢ፩ -፱።ጸሎ -ሃይ ኤር፮ -፲፩ - ፳፬ -፮። ዮሐ፲፮ -፳፩ ኤፌ፬ -፳፬)

ብእሲ ብእሲ - ኹሉ አንዱም አንዱም በየራሱ -(ዘፀ፲፮ -፳፱ ሕዝ፲፬ ፬። ዘሌ፲፭ -)

ብእሲሁ - ኹሉ አንዱም አንዱም በየራሱ -(ዘፀ፲፮ -፳፱ ሕዝ፲፬ ፬። ዘሌ፲፭ -)

ብእሲታ -ይች ሴት፤ ያች ሴት፤ ሴቲቱ፤ ሴትዮይቱ ሴትነት። ምንት ብእሲታ -(ሉቃ፯ -፴፱)

ብእሲት -( ኢሻ ኢሽት) ንዦ ምሉ ሴት፤ ሚስት። ብእሲት ድንግል። ብእሲ ወብእሲት። ብእሲተ ብእሲ -(ዘሌ፳፩ -፲፫። ዘፀ፳፩ -፳፰ ዘዳ፭ -፲፯)

ብእሲቶ -የቅርብ ተጠሪ ንች ሴት እሜቶ ወይዘሮ -(ዮሐ፪ -፬። -፳፩ -፲፫ -፲፭) ብእሲና ብእሲት እንደ ወርቅና እንደ ሐራ ውስጠ ብዙዎች ስለ ኾኑ፤ ግልጠ ብዙነት የላቸውም ብእሲ ከዕደው ብእሲት አእንስት ይገባሉ።

ብእሴ ሐቅል -በረኸኛ ዐዳኝ፤ ወንበዴ፤ ሽፍታ ወያኔ -(ዘፍ፳፭ -፳፯)

ብእሴ ኅይል -ኀይለኛ ጕልበታም ባለአእምሮ -(፩ነገ - -፵፪)

ብእሴ ምድር -ራሽ ገበሬ ጃን ገበር የርሻ ባለቤት -(ዘፍ፵፱ -፲፭)

ብእሴ ሰላም -ፍቅረኛ ፍቅር ወዳድ አስታራቂ -(መዝ -፴፮) ብእሲ በስም በግብር በዘር በነባር እየተናበበ በዚህ ምሳል እንደ ስልቱ እንዳመጣው ይፈታል

ብእሴ ዐመፃ -መጠኛ ዋሾ ግፈኛ ሳዊ መሲሕ -(፪ተሰ - -)

ብእሴ እግዚ -ነቢይ ሐዋርያ ጻድቅ ቅዱስ -(፩ነገ - - -  ፩ጢሞ - -፲፩)

ብእሴ ደም -ደም አፍሳሽ ነፍስ ገዳይ ዐርበኛ የጦር -(መዝ -)

ብእሴ ፍትወት -መውደድ መወደድ ያለው ሥልጡን ስብቅል -(ዳን፲ -፲፩)

ብዕራዊ -የበሬ በሬማ፤ በሬያም ባለበሬ ዐራሽ ገበሬ ባሪያ ሎሌ ቅን አሽከር ተገዥ አገልጋይ ብእሲት ብዕራዊት ታስተፌሥሖ ለምታ -(ሢራ፳፮ -)

ብዕር ብዕራ ብዕራይ -(ዕብ ብዒር ከብት ሱር ብዒራ ዐረ በዒር ገመል አጋሰስ) በሬ፤ የቀንድ ከብት ተጠምዶ የሚያርስ የሚያሳርስ ሞኝ አላዋቂ እገሌ በሬ ነው እንዲሉ። ብዕር ላንድ ብቻ፤ ብዕራ ብዕራይ ላንድም ለብዙም ይኾናል እንደ ሐራና እንደ ባዕላይ ነው ድግ ወእመሂ ብዕራ ፅምደ ብዕራ ርዑተ ብዕራ ተያፍም ወብዕራ መጺኦ ዐቢይ ብዕራይ በልዖሙ ብዕራይ ብርት። ዘይቀሥፍ ብዕራዪሁ -(ዘፀ፳፪ -፲። ኢሳ፭ - -፲፰ ስንክ -ሠኔ፲፩ ዮሴፍ። ስንክ -መስ፳፯ ራ፴፰ -፳፭)

ብዕዛ -(ዛት። ትግሬ በዕዛ) ሳላ የፍየል ዐይነት የዱር የበረሓ እንስሳ እንደ ቦኸር እንዳጋዘን ያለ ቀንዳም፤ ቀንዱ ቀጫጭን ረዥም ቀጥ ያለ የተካ በትር የሚመስል። ቱልቱላ የሳላ ቀንድ እንደ እንቢልታ እንደ መለ በአፍ የሚነፋ፤ ወይም በሳላ ቀንድ አምሳል የተሠራ መለ ንዋየ ማሕሌት፤ የሚነፋ ኹሉ ባሉብሉዮች ግን ቃጭል ጸናጽል ነጋሪት ይሉታል ቀርንና ብዕዛ በመጻሕፍት  እንደሚገባቸው አልተፈቱም መላሾች ቀርንን በሮ ነጋሪት ብዕዛን እንቢልታ መለ ብለውታል፤ በበገናና በመስንቆ በሌላውም ፈንታ ብዕዛ ተጥፎ ይገኛል። በአቅርንት ወበብዕዛ ርጋኖን ወብዕዛ ቃለ ቃርን ወእንዚራ ወመሰንቆ ወብዕዛ ወማሕሌት ወምስሴሁ መዘምራን እለኒ በጸናጽል ወእለኒ ከበ ወእለኒ በብዕዛ ወበአቅርንት -(፪ዜና -፲፭ -፲፬ ስንክ -መስ፲፰። ዳን፫ -፭። ፪ዜና -፲፫ -)

ብዕድና -ባዕድነት፤ ልዩነት፤ ውላጤ ዘእንበለ ፋቄ ወብዕድና -(ቄር -እስት)

ብኵ -ብኩይበከየ

ብኩር -(ራን ራት ርት) የተበኰረ በኵር የኾነ የተባለ የቀረ የታጐለ።

ብኩይ -(ያን ያት ኪት) ያለቀሰ አልቃሽ ሐዘንተኛ።

ብካይ -(ያት) ልቅሶ ዋይታ ፍጅጅት፤ መራራ ኸት እንብ ጋራ በከየ ብካየ ቢየ ብካየ ያዜር። ብካይ ወላሕ። ቃለ ብካይ ወቃለ ዐውያት -(ኤር፴፰ -፫። ኢሳ፲፮ -፱። ፳፪ -፲፪ ፷፭ -፲፱)

()          ብክ ብኵ -(ዕብ ቦኬ) ስመ ሰብእ ዳዊት በካዪ ብኩይ አልቃሽ እንባማ ማለት ነው ባጎር ወልደ ብኵ -(ጥበ፩ መዝ፮ -) የባጎርን ፍች መልከት

ብውሕና -ጌትነት ሥሉጥነት። ልዮተ ብውሕናሁ -(ማር -ይሥ፪ -)

ብዉሕ [1]-(ሓን ሓት ውሕት) የሠለጠነ፤ ሥሉጥ የተገባ። ብእሲት ኢኮነ ብውሕተ ዕለ ርእሳ፤ ወከማሁ ብእሲኒ ኢኮነ ብዉሐ ወአኮሰ ዘኢኮነ ብዉሓነ ኮነኑ ብዉሐ ብሓዊ ይግበር -(፩ቆሮ - -፬። ተስ - -፱። ሮሜ፱ -፳፩)

[2]-(ይደሉ፤ መፍትውርቱዕ) ይገባል የተገባ፤ የሚገባ ግቡ፤ አገባብ። ይደሉ ሲኾን በቁሙ ውስጠ ሲኾን ውእቱ አለበት። ብዉሕ ይባእ ውስተ ቤተ መቅደስ ዘእንበለ ካህን ብዉሕ ለኤጲስቆጶ ከመ ፍታሕ። ብዉሕ ትንብብ ወትግበር ዘፈቀድከ ኮነሁ ብዉሐ ልዑል ይግበር ዘፈቀደ -(ዮሴፍ - - -፪። ቀሌ ኢዮ፳፪ -፲፪)

ብዙኅ -(ኃን ኃት ዝኅት) የበዛ ብዙ እጅግ ያሌ። ዕንቍ ዘብዙኅ ብዙኃን ምውሉደ ብጽ ብዙኃት ዋልድ ገር ብዝኅተ ሰብእ -(ዮዲ፲ -፳፩።  ኩፋ -፵፪። አስቴ፪ -፰። ሕዝ፴፬ -፲፮)

ብዙኀት -በዝቶ ብዙ ኹኖ ብዙ ጊዜ በብዙ። መጽአ ብዙኀ ወተመይጠ ኅዳጠ ትትአመኖ ብዙኀ ብዘኀ ተመንደበ ዙኀ ይትሜየን -(ዘረፋ። ሢራ፮ - ፴፩ -፲፩)

ብዙት -የተባዘተ፤ ብዝት፤ ባዘቶ፤ ፍልቅቅ። ፀምር ብዙት -(መሳ፮ -፲፯ ስንክ -ታኅ፲፮)

ብዝኀት -መብዛት፤ አበዛዝ ብዛት ብዙነት። ብዝኀተ ሰብአ -(ዮሴፍ)

ብዝኅ -(ኃት) ብዛት፤ ብዙነት ብዥ። ብዝኀ መዋዕል ብዝኀ ዓሣት በብዝኀ ዓመታት በብዝኀ ብረት -(ዘካ፰ - ዮሐ፳፩ -፮። ኢዮ፲፪ -፲፪)

ብዝር ክታን -ብዝር ክታን፤ የተልባ ፍሬ፤ እንቡጡ ቅንጣቱ።

ብዩን -(ናን ናት ይንት) የተለየ የታወቀ የተረዳግልጥ ልሕ ዝንቱ ብዩን -(ዮሴፍ)

ብዩጽ -(ጻን ጻት ይጽት) የተለየ ልዩ ምርጥ።

ብያኔ -(ያት) መለዮ፤ ልዩነት፤ በቁሙ ብይን ፍርድ አፈራረድ፤ ፈሊጥ ዕውቀት፤ ሥርዐት ማእምረ ብያኔ ብያኔ ልባዊ። ብያኔ ሮማዊ -(ታሪ -ነገ - -)

ብዱር -(ራን ራት ድርት) የተበደረ የተቀደመ የተወደደ፤ ምርጥ

ብዱት -የተፈታች ባዶበድወ

ብዳ -(ዐረ ቤዳ) ነጭ ንጣቱ ዕንቍላል መድ ወይም ያህያ ሆድ የሚመስል። ሕብረ ከብድ ባለው ብዳ ይላል ባለብሉዮች ግን ብጫ ይሉታል -(ዘፀ፴፮ -)

ብድብድ -ዛሕል ዝገት። ሞተ ግብት ቸነፈር መቅሠፍት ሰውነትን የሚያዝግ የሚያጠወልግ ፈጥኖ የሚገድል እንደ ነፍጥ ያለ በሽታ ባለወግ መልአክ ለመዐት ለመቅሠፍት የሚላክ አጥፊ ቀሣፊ። ክፉ ካኝ ንጉሥ እንደ ሮድስ እንደ ቴዎድሮስ ያለ -(ዘኍ፲፯ -፲፪ ፪ነገ -፳፬ -፲፭፲፯ ዕብ፲፩ -፳፰) ወአውሥእዎ ለውእቱ ብድብድ ጉሥ ጉእ ወመግእዝ ወነባቢ ብድብድ ስሙ -(መቃ -ገ፩ ምሳ፳፩ -፳፬)

ብድወት -መጥፋት መፈታት፤ ውድማነት ባዶነት ይርአይ ብድወታ ለኢየሩሳሌም -(ስንክ -ሚያ፫)

ብድው -(ዋን ዋት ዱት) የጠፋ የወደመ ባዶ ባድማ የኾነ የተፈታ ምድር ብዱት ገዳም ብዱት -(ዮሴፍ ስንክ -መስ፫)

ብጡሕ -(ሓን ሓት ጥሕት) የተበጣ ብጥ ሥንብጥ ትፍትፍ

ብጡል -(ላን ላት ጥልት) የበጠለ የጠፋ ጥፉ መጥፎ ብልሹ ንቱ። ስብሐት ብጡል ዝንቱ ብጡል ኦሪተ ይሁድ ብጡል። ዛቲ ተደምሮ ብጥልት ምሕገ ሰብሳብ ወእሰምያ ጢአተ -(ፊልክ -፳፱ ገድ -ተክ - -፵፪ -፩። አቡሻ - - -) ድልድል ቅምጥል ሥራ ፈት አውታታ፤ ወይም ዘመናይ ጌታ ብጡል ወሌ ብጡል እንዲል -(የጁዬ)

ብጥሐት -ሙብጣት፤ መበጣት፤ አበጣጥ ብጥነት ብጥታት። ብጥሐተ ገጽ -( - )

ብጥለት -መጥፋት፤ አጠፋፍ፤ ጥፋት፤ ከንቱነት ስመ በው ዘዝንቱ ዘመን ረሰይዎ ብጥለተ -( - -፲፫)

ብጥም ቡጥም -(ዐረ ቡጥም ሱር ቤጥማ) በቁሙ፤ የዛፍ ስም፤ ወርቤንቶስን እይ ዚህ ጋራ አንድ ነው። ይዘብሑ ታሕተ ባሉጥ ወቡጥም ወገውዝ ወለውዝ -(ሆሴ፬ -፲፫። አቡሻ -፵፯)

ብጹሐ መዋዕል -ቀኑ የደረሰ ድሜ የጠገበ ዕለተ ሞቴ የቀረበ አሮጌ -(፩ዜና -፳፱ -፳፰)

ብጹሕ -(ሓን ሓት ጽሕት) የደረሰ ያደገ የጐለመሰ  የመላ የተፈጸመ ፍጹም። ብጹሐ ምጣን። ብጽሕተ ምጣን። ብጹሓነ ምጣን ምዕሥራ ዓመት ወከሃ ብጹሓነ ሠላሳ ዓመት -(ኤፌ፬ -፲፫ ሲኖዶ ፩ዜና -፳፫ - -፳፬)

ብጹሕ ውስተ  ትሩፍ -ብጹሕ ውስተ ትሩፍ፤ ከፍጹምነት የደረሰ በትሩፋት የተፈጸመ ባሕታዊ።

ብፁዓዊ -የብፁዕ ወገነ ንጹሕ፤ ወጣኒ መንፈሳዊ ወይም ብፁዕ የተባለ ብፁዕነት ያለው ማእከላዊ ፍጹም ቅዱስ ብፁዓዊ ተክለ ሃይማኖት ሐዱ እምብፁዓውያን -(ገድ -ተክ። ፊልክ -)

ብፁዕ -(ዓን ዓት ዕት) ብፅዐት የገባ ባለብፅ የብፅ ልጅ የብፅ ገንዝብ። ኵሉ ዘብፁዕ ዘበፅዑ መሀይምናን -(ሃይ -አበ፫) በቁሙ የታመነ የተመሰገነሥራውና ልቡ የቀና የተከናወነ ክቡር ምስጉን ምሩቅ ቡሩክ ቅዱስ ጻድቅ ቸር ብእሴ እግዚአብሔር እንደ ኢዮብና እንደ አብርሃም እንደ ዳዊት  ያለ ብፁዕ ብእሲ ዘኢሖረ በምክረ ረሲዓን። ብፁዐ ረሰይከኒ። ትበሉ ብፁዐ ዘእንበለ ትርአይ ደኃሪቶ ብፅዕት ፍስ እን ትፈርሆ ለእግ ብፁዓም ዳያን በመንፈስ -(መዝ -፩። -ዕዝ፲፪ -፲፬ ሢራ፲፩ -፳፰ ፴፩ -፲፯ ማቴ፭ -፲፩) ስምነቱ ማእከላዊ ነው ንጹሕ በላይ ከቅዱስ  በታች ስለዚህ ለፈጣሪ ሳይቀር ለወጣኒና ለፍጹም ለኹሉ ይኾናል። ለብፁዕ እግዚአብሔር -(፩ጢሞ - -፲፩)

()          ብጻል -ልጥ ቅርፍት ቅራፊ ብጫቂ ብጭቅጫቂ፤ ላቂ ብጣሽ ቍራጭ። ረከብኩ ብጻላቲሃ ወአጽርቅቲሃ -(ኤር -፲፫ -)

ብፃው - (ዋት) እንቅልፍ እንጕልቻ ቅዠት ጨዎታ ቧልት አለውቀት ከደኖን ቀራንብቲከ በብፃወ ጣውእ ወእመኒ መጽአኒኢ ብፃው ለአፅርዖ ጸሎት እንቅልፍ (መጽ ምስ ርጋ ) ወለእመኒ አእመርዎሙ እከዮሙ ይብሉ በበፃው በርነ ጨዎታ (ምሳ፳፱ ፲፱)

ብጽሐት -(ታት) መድረስ፤ መምጣት አደራረስ። ብጽሐትከ ኀቤየ። ሶበ አእመረ ብጽሐቶሙ ምቤተ መቅደስ። ጊዜ ብጽሐተ ሐጋይ መጽሐፍ ጽሐት ወአስተፍሥሐኒ ብጽሐታ -(ገድ -ተክ ዮሴፍ - - -፮። ዮሴፍ)

 -ምርመራ ፍተሻ፤ የተጣፈን ጥር ቀመርን ጉበቶ ማየት ድርሱን ማግኘት፤ ማወቅ መረዳት -(አቡሻ -)

ብጽሕ -(ሓት) ድርሻ ፈንታ፤ ክፍል ዕድል።

ብፅዐት -(ታት) መሳል ብፁዕ መባል ስለት የስለት ገንዝብ፤ የብፅዐት ሥራ ኢታጐንዲ ውሂበ ብፅዐትከ ፍዲ ብፅዐተ ብፅዐተ ሕይወትየ መሥዋዕት ዘዘልፍ ወዘብፅዐት። ብፅዐት ቦሙ በእንተ ብፅዐታት። አንተ ውእቱ ዘትትዌከፍ ብፅዐታተ ወዓሥራተ -(ሢራ፲፰ -፳፪ናሖ፪ -፩። መዝ -፵፩። ዮዲ፬ -፲፬ ግብ፲፰ -፲፰ - -፲፰ ማር -ይሥ) ብፅዐትና ብልኅ ባማርኛ ይተባበራሉ፤ ስለት በመባል። -(ሙሾ፤ ልጆቿ በሰይፍ ያለቁባት) የቤተ ክሲያን ገንዘብ አትንኩ ስላችኹ ምነዋ ልጆቼ ስለት የበላችኹ።

ብፅዓን -(ናት) ዝኒ ከማሁ ክብር ምስጋና። ብፅዓን ወፍሥሓ ክሙ ቃላተ ብፅዓን። ብፅዓን ይደልዎ ገብር  ምእመን የኀጥእ ብፅዓነ ንተ ተብህለት ሕዙናን። ታወሥኦሙ ለኅሩያን በቃለ ብፅዓን -(ዮሴፍ። አፈ -ተ፯ - - -፲፩ ፊልክ -፸፱። ቅዳ -ያዕ)

ብፅዕ -(ዓት) ክብር ምስጋና ብፁዕ ማለት መባል የቡራኬ ቃል ጴጥሮስ ረከበ ብፀዐ እምኀበ መድኅን ወይቤሎ ብፁዕ ንተ ወሀበ እግዚ ለእሉኒ ብፅዐ በብሂሎቱ ብፁዓን መሓርያን -(ቀሌ። ፊልክ -፶፩)

ብፅዕና -ብፁዕነት፤ ክብር ምስጋና ቅድስና። ብፁዓን እሙንቱ ወዓዲ ነሂ ብፅዕና -(ገድ -ኪሮ) በብፅዐት ፈንታ ብፅዕና ብፅዕናት ይላል ስሕተት ነው። ብፅዕናት ወብኵርናት -(ቀሌ)

-ባር ንቀጽ። አለ፤ ኖረ፤ ነበረ ኾነ ላንድም ለብዙም ለወንድም ለሴትም ይከታል ዐርክ ኀላፊ። ጻድቃን ውሉደ ቤትከ ብእሲት እንተ ትሤኒ እምብእሲት ወቦ አንስትኒ እለ ጌሣ መቃብር ቦቱ ባለው በዝርዝርነት ፈታ ግን ላንድ ብቻ እንጂ ለብዙ አይኾንም። ይህም አለው አለለት አለበት እያለ መኼዱን ያሳያል። ቦቱ ተለይቶ በርሱ በት ይኾናል። ዘቦቱ ኵሉ ኮነ ኹሉ በርሱ የተፈጠረ፤ ወይም የተፈጠረበት። ኵሉ ዘየአምን ቦቱ፤ የሚያምንበት ኹሉ። በርሱ ቢል በት ቢል ስልቱ ንድ ነው ለክፉም ለበጎም ይኾናል።

ቦሁ ቦኑ -( ሁ፤ ) ነባር አንቀጽ የጥያቄ ቃል በተገናኝ አለን አለ ይኾን ያሰኛል። ቦሁ ኀበ ይሴወሩ ምኔየ ቦሁ ዘተርፈ ቤከ ቦኑ ረኣይ ዝየ -(ኤር፳፫ -፳፬። ዓሞ፮ -፲። ፩ነ - -፲፩) ኹለተኛም በትርፍ ማርኛ በውኑ እውን እያሰኘ ጥያቄን መደብ አድርጎ ምርመራን ወቀሣን ተግሣጽን ያሳያል። ትርፍ ማርኛ ማለት አንቀጽነቱን ይለቅ ቦሁ ዘሰአልኩክሙ፤ ቦኑ ዘዐመፅኩክሙ እያለ ይህን በመሰለ ገባ ውኑ የለመንኋችኹ የበደልኋችኹ አለን ያሰኛል ስለዚህ ነው። አንቀጹ ሌላ ኾን ግን ፍችው በውኑ ብቻ ነው፤ ስለዚህ በጥያቄ ኹሉ ይገባል፤ በውኑ ማለት ርሱው ራሱ ጥያቄ ውና። ቦኑ በኣተ ፈያት ውእቱ ቤትየ። ቦኑ፤ለባሕቲቶሙ ለአይሁድ እግዚ። ቦኑ አባእክሙ መሥዋዕተ ወቍርባነ። ዘአባእክሙ ቢል ግን አለን ያሰኛል ውኑ ሲጨመር ያምርለታል -(ኤር፯ -፲፩ ሮሜ፫ -፳፱። ግብ፯ -፵፪)

ቦቀ -(ይበውቅ ይቡቅ በዊቅ ዐረብ በወቀ) ነፋ መታ አስጮኸ ባፍ ትንፋሽ።

ቦኑ -( ) ውኑ አለን ቦሁን ተመልከት ፍችው ዚያ አለልኽ

ቦአ -ገባ፤በዊእ ቦአ

ቦዐ -(ዐረ ባዐ) ዘረጋ ጋተ ሰነዘረ

ቦአኔርጌስ -(ጽርእ። ዕብ ብኔይ -ርጎሽ) ደቂቀ ጐድጓድ -(ማር፫ -፲፯) |

ቦክ [1]-(ዕብ ቡኽ) በዊከ መባከን መቅበዝበዝ እንቡዝ መኾን፤ ተለል ተለል ማለት የመንገደኛ የድውይ። ባለብሉዮች ግን ስለ ሥጋ ይሉታል። መጽአከ ሕማም ወገሰሰከ ቦክ -(ኢዮ፬ -) ክዳም ገዚፍ በማለት ፈንታ ክዳነ ቦክ ይላል የተሳሳተ ነው። ዕብራይስጡ ግን ማክቤር ይላል ልብድ ለሐፍ የሌት ልብስ እንደ ቡልኮ ያለ ማለት ነው -(፬ነገ - -፲፭)

[2] -ቦክመባከንበዊክ

ቦዝ -ቸልታ አንቀጽ፤ ንባቡ ስያፍ ቃሉ ነፍ ነገር የማያስር ቀቲሎ ባሪኮ ቀዲሶ ይህን የመሰለ ካሥሩ ውታረ በገና ያንዱ ስም። ቦዝ ደንጉል እንዲሉ። ነጮችም ባውዛ የሚሉት የታላቅ መብራት ስም ከቦዝና ከቤዝ ይሰማማል



 

No comments:

Post a Comment

ማውጫ

ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ