~ገ~

                                 

-ሦስተኛ ፊደል በግእዝ አልፍ ቤት በአበገደ ስሙ ገምል ጥሩ ፫፤ አኃዝ ሲኾን ሠለስት ይባላል ዕብራውያን ግን ሦስትን መደብ አድርገው በራሱ ነቍጣ እየጨመሩ ሦስት እልፍ ይሉታል። ምስጢሩ ሠሉስንና የሠሉስን ፍጥረት መደብ አድርጎ ኛውን አካል መንፈስ ቅዱስን የመንፈስ ቅዱስን ሀብትነት ፍሬ ጸጋውን ያሳያል፤ ገመልን እይ -(ዘፍ፩ -፲፩ ፲፪)

ገሃህ ገሀህ -የጨረቃ ምላት ብርሃኗ ተወለደች ወይም በበቀለች ባ፲፭ኛ ቀን መልቶ ተካክሎ ውድማ መስሎ የሚታየው ከመ ወርኅ ምልእት በዕለተ ገሃህ። ወርኅ ተፈጥረ ምሉ ብርሃን ዕለተ ገሃሁ ሥኑ ወርኅ ሀህ በቀዳሚ ወርኅ ገሃሁ ወርኅ ዘአሜ ሀህ -(ሢራ፶ -፮። አቡሻ -፲፫ አርጋ -፮። ሕዝ፴፪ -፲፯ ደራሲ)

ገሓሢ -(ሢት ሥያን ያት ሐሥት) የሚገባ ገቢ መጪ፤የሚርቅ የሚያገል አግላይ ፈቅቅ ባይ መናኒ

ገሃነማዊ -የገሃነም ሥቃይ እሳት ጭፍራ ራዊት። ላህብ ገሃነማዊ -(ጥበ -ጠቢ)

ገሀነም ገሃነም -(ጽር ጌሄና። ዕብ ጌይሂኖም። ዐረ ጀሀነም) የቦታ ም፤ ከደብረ ጽዮን የተያያዘ የተራራው እግር፤ የቄድሮንና የግዮን ወንዝ ማየ ሊሖም የሚወርድበት የኢየሩሳሌም ቅርብ አጠገብ በስተደቡብ ያለው ጐድጓዳ ቈላ ሸለቆ ወንዛወንዝ መቀራቅርት፤ እስራኤል ልጆቻቸውን ለሞሎኽ ይሠዉበትና ይጦብሱበት ያቃጥሉበት የነበረ፤ የከተማው ውስጥ ለውስጥ ወደ ርሱ የሚጐርፍበት የጥንብና የጕድፍ መጣያ ርኩስ ቦታ፤ የውነተኛው ገሃነም ምሳሌ። ሄኖም የሚባል ያቀናው የወረሰው የሄኖም ወንዝ ወይም ሄኖም ልጆች ላንዱ የደረሰ ያንደኛው ልጁ ክፍል ማለት ነው። ጣፌጥን እይ ከዚህ ጋራ አንድ ነው -(ኢያ፲፭ -፰። ኤር፯ -፴፩ -፴፪። ፬ነገ -፲፮ -፫። ፳፫ -) በቁሙ ሲኦል መቃብር የእሳት ድጓድ ዘቅት መካነ ኃጥኣን ሞቱ በኋላ የሚኖሩበት የሥቃይ ቦታ፤ እሳቱና ትሉ የማይጠፋ የማያንቀላፋ -(ምሳ፩ -፲፪ ፲፭ -፲፩ መክ፱ -) እቶነ ሃነም። እሳተ ገሃነም  ሥቃያት ዘገሃነም ወሞትሰ ዳግም ገሃነም ዘእሳት -(ሱቱ -ዕዝ፮ -፩። ማቴ -፳፪ -ኢሳ፩ -፫። ራእ፳ -፲፬። ማር፱ -፵፫ ኢሳ፷፮ -፳፬)

ገሓይ ግሔ -(ሕያት ዕብ ሻፋን ዐረ ወብር ጽር ኪሮግሊዩ) ኮኮ አሽኮኮ እንደ ጥንቸል ያለ ቅጠል ቡቃያ የሚበላ ማለዳ ቀድ የሚጮኽ የሚያሽካካ። ፈሪ ድኩም ጎሓዊ ማለት ነው ርሥከሂ ጾላ ምጕያየ ግሔ ረኃብ። ወግሕያት ሕዝብ ዘኢኮኑ ጽኑዓነ ናጽል ወግሕያት -(ቅኔ። መዝ -፻፫ ምሳ፴ -፴፮። ሔኖ፺፮ -)

ገሃደ -ገልጦ ተገልጦ ግልጥ ኹኖ በግልጥ በገሃድ። ዘገሃደ ተነበይኩ። ገሃደ ይመጽእ። ዐርገ ጽሚተ ወአኮ ሃደ -(ዕር -ኢሳ፬ - መዝ -፵፱። ዮሐ፯ -)

ገሀድ ገሃድ -ቁሙ የልደት የጥምቀት ዋዜማ፤ እንዳርብና ረቡ የሚጦም። ሰላም እብል ጾመ ዕለት ዋሕድ ዘስሙ ገሀድ -(ስንክ -ጥር፲)

ገሃድ ገሃዲ -(ዲት ድያን ያት) በቁሙ የሚጋድ የሚገለጥ፤ ተገላች ተገላላጭ ግልጥ ኵሉ ዘገሃድ ርሃን ውእቱ ኮነኑ ገሃደ ይእዜ ኮነ ማነ ወብዙኀ ይጌሥጾሙ ከመ ገሃደ ይረስይዎ -(ኤፌ፭ -፲፫። ር። ማር፫ -፲፪)

ገሓፊ -(ፊት ፍያን ያት ሐፍት) የሚግፍ የሚጠርግ፤ ጋፊ ጋፋፊ ጠራጊ ሆዳም

ገሓፍት -(ዐረ ቁፈት። ሳል) ቅርጫት መሶብ እንቅብ አገልግል ቅንብቻ ፈዳ ግትቻ። ወታነብሮ ሓፍት -(ዘፍ -፳፱ -፫። ፳፫ -፴፪) 

ገህግሀ -(ዕብ ጋሃህ። ሱር ግሃእ ዐረ ጀህጅሀ) አራቀ ስገለለ ለየ ከላ ለከለ ኀጢአ እንተ ልባቲ ዘይገሀግሃ -(፪ጴጥ - -፲፬) ዘሩ ግሂህ ነው፤ ገህሀን እይ።

ገለሠ -ተቀመጠ ሸነጓገሊስ ገለሰ

ገለባት - ነጋዴ ቅፍለት ማኅበር ኹኖ አጋሰሱን ጭኖ እንደ ጐርፍ የሚኼድ የሚያረብድ

ገለብ [1]-መግለብ መቃጥን መንጠቆ፤ መግለቦ ዘረ መትር ያሣ ወጥመድ መያዣ መጋፈፊያ በመግለብት ወበመዋቅሕተ ኀጺ ተሐውር -( ኢሳ፫ -) ጀልባ ታን ፍልኳ ዓሣ ወጋሮች የሚቀመጡበት። አንዳንድ መጽሐፍ በገለብ ፈንታ ጌልያ መርከብ ይላል። ገለባ ንፋሽ እንጕላይ -(ዐማርኛ)

[2]-(ትግሬ) ጋዛ ፀጋም ግራ የሚያዝ የሚነገብ አላባሽ አግሬ

ገለዓድ -(ዕብ ጊልዓድ) ስመ ገር ተራራ፤ ከዮርዳኖስ ማዶ ያለ -(ዘኍ፴፪ -)

ገለድ -(ትግሬ) ኪዳን፤ ላም ርቅ ፍቅር ስምምነት ቅርበት ልጽቀት

ገለዶ -(ዐማርኛ) ታላቅ ላዎ ካራ የበጎች ጠጕ መሸለቻ፤ ቈርበት የሚቀፍ የሚቀድ፤ የሰፎችና የፋቆች መሣሪያ።

ገሊላ -(ዕብ ግሊላ፤ ጋሊል) ስመ ገር የምድረ እስራኤል ሜን፤ በዮርዳኖስና በጥብርያዶስ በዐቢይ ባሕር መካከል ያለ የይሳኮርና የዛብሎን ክፍል ታችኛው ይኛውም የአሕዛብ ክፍል ሳይቀር። ገለልተኛ ገጠር ዐልፎ ዐልፎ ሀገርና መንደር ያለበት ዐውድ ዘውር ማለት ነው -(ኢያ፳ -፯። ነገ - -፲፩) ናዝሬት ዘገሊላ ቃና ዘገሊላ ወገሊላ ዘአሕዛብ -(ሉቃ፩ -፳፮። ዮሐ፪ -፩። ማቴ፬ -፲፭)

ገሊል ሎት -(ገለ አው ገለለ ይገልል ይግልል ዕብ ጋላል) መምረጥ ማንጓለል፤ መለየት ማስገለል። ማንጋለል በዥርባ ማስተኛት ገልገለ የዚህ ዲቃላ ነው

ገሊስ ሶት -(ገለሰ ይገልስ ይግልስ ትግ ገልሰ ዕብ ጋላስ ዐረ ጀለሰ ተቀመጠ) መለበድ ልብድ መስፋት ርበት ማልበስ መደጐስ መደልደል ማመቻቸት፤ መሸብለል መጠቅለል፤ የኮርቻና የጭነት።

ገሊብ ቦት -(ገለበ ይገልብ ይግልብ ዐረ ጀለበ ሳበ) ጥመድ፤ መቃጥን መስደድ መረብ መንዛት፤ መሳብ መጐተት፤ መግለቦ መሥራት ያሣ ወጋሪ ንዘ ንገልብ -(ኪዳ) መግለብ መግለጥ የኀፍረት የቂጥ መሸሽ መሮጥ፤ መጋለብ ማምለጥ መዘራት መበተን መቅለል ንጓለል ፍሬ ቢስ መኾን፤ የገለባ።

ገሊዕ ዖት -(ገልዐ ይገል ይግላዕ ዕብ ጋሎ) መንቃት መሠንጠቅ መስበር መድቀቅ፤ መንከት መነካት መጐዳት፤ የሸክላ ያጥነት

ገሊው ዎት -(ገለወ ይገሉ ይግሉ ገለበ ገለደ) መጐለብ መለጐም፤ መሸፈን መጋረድ ማልበስ መለበጥ፤ መጐለብ የስፌት መለጐም የባላፍ ያታሞ የከበሮ መሸፈን ማልበስ ለኹሉ መለበጥ ከንጨት ከደንጊያ ለተሠራ ቤት ለሣጥን ይገልዎሙ ልቦሙ ከመ በሮ ዘገለውዎ ጎሞር ዘገለውዎ በቈጽለ ወርቅ -(፪ቆሮ - -፲፭። ድጓ መጽ -ምስ ዘፀ፲፮ -፴፫። ነገ - -፲፭)

ገሊጽ ጾት -(ገለጸ ይገልጽ ይግልጽ) መግለጥ መግፈፍ ማሳየት መንገር መተርጐም ማስረዳት

ገሊፍ ፎት -(ገለፈ ይገልፍ ይግልፍ ሱር ግላፍ። ዕብ ጋላፍ) መቅረጥ ማነጥ ማንጠጥ ጣዖት መሥራት በንጨት በደንጊያ በልብስ ላይ መሣል መመሰል መፈደል  መጠረዝ መጥለፍ እለ ይገልፍዎ ለዕ ይክል ሊፈ ምሳል ገለ ላዕሌ በቀልተ ወአክሊላተ። ይግልፍዎ ውስተ ኰኵ እለ ይገልፉ ወየኀርዉ ዐይነ ማኅተም። ልፍ ላዕሌሆሙ ስማተ ቀጠንት ያሰረግውዎሙ በሕብራት ዘገለፉ ቦሙ -(ኢሳ፵፭ - ዜና - -፲፬። - -፯። ኢዮ፲፱ -፳፬ ሢራ፴፰ -፳፯ ዘፀ፳፰ -፱። - -፳፫)

ገላሜዎስ -ሥሥት፤ከሜሌዎን

ገላዊ መግልው -የሚጐልብ የሚሸፍን፤ ጋራጅ ባጭ

ገላዲ መገልድ -(ዲት ዳን ዳት) የሚደጕስ ደጓሽ ርበት አልባሽ አንጣፊ።

ገላፊ -(ፊት ፍያን ያት ለፍት) የሚቀርጽ አንጣጭ ምስል አፍሳሽ።

ገልበበ -(ተቀ ዐረ ጀልበበ ገለወ) ሸፈነ ከደን አለበሰ አከናነበ ጋረደ ለበጠ መረገ ለሰነ ቀባ ገልበቡ ርእሶሙ ይገልብብ ፉሁ ይገለብብዎ ገጾ ሥብሕ ዘይገለብብ ከርሦ ዘይገለብቦ ለሰማይ ደመና ወገልበቡ ዘውስቴቱ ምዕፅ በነፍጥ ብዙኅ ገልበበታ ለንፍቅ ፒሳ -(ኤር፲፬ -፬። ዘሌ፲፫ -፵፭። ሉቃ፳፪ -፷፬። ዘፀ፳፱ -፳፪ -፻፵፮ ዮሴፍ ኩፋ -፵፯)

ገልባቢ መገልብብ -የሚሸፍን ዳኝ አልባሽ፤ ጋራጅ አከናናቢ።

ገልዓት አግልዕት -ገሎች ገላልት ሰሩ ውስተ ከሣዱ ሐብለ ወዲቤሁ ሰቀሉ ገልዓተ ዘአጽለምዎሙ በፍሕም ዘያስተጣግዕ አግልዕተ -(ስንክ -መጋ፳፯ ሢራ፳፪ -)

ገልእ -የሸክላ ስባሪገሊዕ ገልዐ

ገልዕ -(ዕብ ሔሬሽ) ገል የሸክላ ስባሪ እንክትካች የሳት መጫሪያ እሳት በገል ውሃ በቅል እንዲሉ ብሩር ዘይትወሀብ ምስለ ሕብል ገልዕ ውእቱ የብሰ ሥጋሁ ገልዕ። ትጽሐፍ ኅሊናሃ ውስተ -(ምሳ፳፯ -፳፫  ገድ -ተክ። ስንክ -ጥር፳፮ ኢዮ፪ -፰። መዝ፳፩ -፲፮)

ገልይ ዮት -(ገለየ አው ገልየ ይገሊ ይግለይ ዕብ ጋላህ ገለጠ) መቍረጥ መቈጥቈጥ መለየት መግለጥ መግፈፍ ማሳየት ራቍቱን ግንዱን መለመላውን መተው የዛፍ የሰው ይገልይዎ -(ዮሐ፲፭ -)

ገልድ -(ዕብ ጌሌድ። ዐረ ጊልድ ሱር ጌልዳ) ርበት ዠን ጥፍ ዳባ ሌጦ አንቀልባ የባሕር ዐረብ ብራና ቅርፍተ ዕፅ

(ጥግ)        ገልዶ ዶት -(ገለደ ይጌልድ ይገልድ ዕብ ጋላድ ገልድ ለበሰ) መደጕስ ርበት ማልበስ ማንጠፍ መክፈፍ ልጋን መኝታን በዠንዲ በነት ይም በሰርፍ በለሐፍ መሸፈን ማስጌጥ። በቀጠንት ገለድኩ ምስካብየ ወዘርቤታተ ነጸፍኩ -(ምሳ፯ -፲፮ ዲድ -)

ገልገለ -(ገሊል ገለ) ገለገለ ገላገለ ለየ ነጠለ አላቀቀ፤ የሰው ረገፈ ቀዳ ገለበጠ አጋባ ባዶ ደረገ፤ ቃ። ወገልገልዋ ሙዳየ ምጽዋት -(፪ዜና -፳፬ -፲፩)

ገልገላ ዕብ -(ጊልጋል) ስመ ገር መንኰራኵራት ማለት ነው እሊሁም በይሁዳ ክፍል ያሉ አህጉር ናቸው አንዲቱ የኢያሪሖ ቅርብ አጠገብ -(ኢያ፭ -፬። ነገ - -፲፮) ፪ኛዪቱ በኬብሮን ያለች -(ዘዳ፲፩ -፴። ኢያ፲፪ -፳፫)

ገልጋሊ -ገልጋይ ገላጋይ ዘርጋፊ ዘራፊ ወራሪ በርባሪ

()          ገልጎ ጎት -(ገለገ ይጌልግ ይገልግ ዕብ ጋላግ) ማጌጥ መሸለም መልበስ መፀረር መከናወን መበጃጀትና መዘጋጀት፤ ወደ ሸንጎ ወደ ገበያ ወደ ሰርግ ወደ ቤተ ክሲያን ለመኼድ።

ገልፈፈ -(ተቀ ) ገፈፈ ገለፈፈ የቈርበት የከንፈር።(ዐማርኛ)

ገመላት አግማል -(ላት) ገመሎች ግመሎች ቀጭኔዎች። ጸጕረ መል ሥአ ሠርተ አግማለ ምአግማለ እግዚኡ። አግማላቲሆሙ -(ማቴ፫ -፬። ዘፍ፳፬ -፲። መሳ፮ -)

ገመላዊ -ግመልማ፤ የግመል ይነት ግመል ሳቢ ጠባቂ የግመል እረኛ ባለግመል ቈሪል ገመላዊ -(ስንክ -ታኅ፳፱)

ገመል -ገምል -(ዕብ ጋማል ሱር ጋምላ ዐረ ጀመል) ቁሙ ግመል የቤት እንስ የጭነት የኮርቻ ብት በረሓ ቈላ የሚደፍር ውሃ ጥም የሚችል ንገተ ረዥም ነዊኀ ቅልጥም ካህያ ካጋሰስ ብልጦ የሚይዝ የሚሸከም ቀጭኔ የበዳ ግመል ነብርማ ዝንጕርጕር የበዳ አህያ የሚመስል፤ ዳኞች እንዳውሬ የሚገድሉት።

ገመመ -(ይጌምም ይገምም ገምሞ) ያዘ በጠ ላጨ ረጠ ረከመ የለጓሚና የላጭታ ጋማ ጋሜ  ማለት ዚህ ወጥቷል። ኹለተኛም ገሚም ገመ ይገምም ይግምም ብሎ ዲቃላውን ገምገመ ሲሉት ገመገም ዚህ ይወጣል ጌመንና ጉማን ተመልከት ፍችው ከዚህ ጋራ አንድ ነው

ገመስ -( አግሙስ) ምንዛሪ ታናናሽ ገንዘብ የተሸረፈ የተመነዘረ አላድ እስከ ሶልድ እስከ ቤሳና እስከ ድዋኔ ያለ ባለሐዲሶች ግን ንኬቶ ቀለበት ይሉታል ደኃሪተ ገመስ -(ሉቃ፲፪ -፶፱) ዳግመኛም ድርህማት ዲናራት ማለት ፈንታ አግሙስ ይላል። ዐሥሩ አግሙስ -(ሉቃ፲፭ -)

ገመር -( ገመራት አግማር) ቁሙ ታላቅ ዝንጀሮ ባለብዙ ጅር ጐምቱ ማግሌ ያገር ቀንድ መምህር አበ ማኅበር። -(ተረት) መምሩ ገመሩ ምስጢሩ ታላቅነት ነው።

ገመታ -ግምጋማሚ ግምት የጭገሬታ ለውጥ። በእንተ ተዓስቦ ቤት ወውሂበ ዋይ ምድር ዘከመ መታ -( - -መቅ)

ገማኒ -(ኒት ንያን ያት) የሚያገምን የሚያሳድፍ የሚያረክስ።

ገመድ -በቁሙ ሐብል። ሐቢልን ተመልከት

ገመገም -ገመገም፤ በቁሙ -(ማርኛ)

ገሙስ ጋሙስ -(ሱር ጋሙሻ) ጐሽ ቀንደ ሹል የበረሓ እንስሳ መልኩ የላም የበሬ ባዩ ያውሬ እንዳንበሳና እንደ ነብር ዐዳኙን የሚሻ የሚከተል በቀንዱና በግሩ የሚበቀል ወይሴሰይ ምሐሊበ ገሙስ እሉ እሙንቱ አልሕምት ጸሊማን ዘገዳም -(ስንክ -መስ፭) ዘገዳም ማለቱ ግብጦችና ህንዶች የሚያልቡትና የሚጠምዱት ጠጕ ሥሥ ቀንደ ገላላ ሻኛ የሌለው ገራም ጭምት የቤት ጐሽ አለና ከዚያ ለይ ነው

ገሚስ ሶት [1]-(ገመሰ ይገምስ ይግምስ ፈተተ) መግመስ መገማመስ መቍረስ መቈራረስ፤ መሽረፍ መሸራረፍ። መመንዘር፤ አንድ የነበረውን ብዙ ማድረግ ለብዙ መለወጥ መግመስ መቍረስ የንጀራ መሽረፍ የገነንዘብ፤ ለንጀራም ይኾናል መመነዘር ግን ለገንዘብ ብቻ ነው

[2]-ገሚስ፤ ዝኒ ማሁ ግማሽ ጼው መጠነ ገሚስ -( -)

ገሚር ሮት -(ገመረ ይገምር ይግምር ሱር ግማር ዕብ ጋማር) ማግመር መጨረስ መፈጸም፤ መቻል መያዝ መወሰን መድፈር ርሶ መናገር -(መጐምራት። መጐመር ማደግ መጋመር መዳበር የሴት) መጽሐፍ ግን በገመረ ፈንታ አግመረ ይላል አድራጊውን ባስደራጊ። ለእመ አግመረ ራህተ እን ይበልዕ ብሑእ ዘአግመሮ ሐሪጽ እለ ይፈቅዱ ያግምርዋ ለምድር ባሕቲቶሙ እግዚ ያገምር ወኢያገምሮ መካን። ታገምር ፍኖታ ዘእንበለ ሐቲ ኪደተ እግረ ብእሲ በከመ አግመረ ኢሳይያስ ወይቤ -(ዘፀ፳፪ -፬። ቅዳ -ዮሐ ኢሳ፭ -፰። ግንዘ ሱቱ -ዕዝ፭ -፯። ተረ -ቄር፲፮)

ገሚት ቶት -(ገመተ ይገምት ይግምት) መገመት መገምገም ይህን ያኽል ማለት

ገሚእ ኦት -(ገምአ ይገምእ ይግማእ ዕብ ጋሜእ ማገ ጠጣ አሸተተ) መግማት መበሽቀጥ ጽዩእ መኾን።

ገሚድ ዶት -(ገመደ ይገምድ ይግምድ አው ገምዶ ዶት፤ ገመደ ይጌምድ ይገምድ ዕብ ጋማድ ዐረ ጀመደ) መጕመድ መጐማመድ፤ መቍረጥ ማጨድ መጨርገድ መገዝገዝ ማረድ። መቍረስ መገምደል መግመድ መፍተል ማክረር ጊዜ ሚድ በጽሐ ዘእንበለ ይግምድዎ ይገምዱ ስካለ ስከ ማእዜኑ ትገምዲ መጥባሕት። ገመዱ መሌሊቶሙ ሥጋ ውስተ ጽህርት ይጌምድ ጋሁ በእብን -(ማሕ፪ -፲፪። ኢዮ፰ -፲፪። ኢሳ፲፰ -፭። ኤር፳፱ -፮። ማር፭ -) መላላቱና ጥበቁ ቱሱሕ ስለ ኾነ ነው የቱሱሕን ፍች ተመልክት

ገሚጽ ጾት -(ገመጸ ይገምጽ ይግምጽ አው ምጾ ጾት፤ ገመጸ ይጌምጽ ይገምጽ) መግመጥ መጋጥ መዘንተር መዘብተር ማማት መንቀፍ ሰላም ስምዖን እን ሐቌሁ አጽን በሐብለ በቀልት ይቡስ እንተ ይጌምጾ ወይበልዖ ወገሚጽኒ ምዕጸበ ስተሐቅሮ -(ስንክ -ነሐ፫ ማር -ይሥ፳፪ -)

 -ማጕበጥ፤ ማስጐንበስ፤ ማጥመም መቈልመም መቀለስ ማጽንን ማዘንበል ወዳንድ ወገን ማድላት መድፋት ራስን ወይም ሌላውን። ዘይጌምጽ ክሣዶ እምንእሶሙ ግምጽ ክሣዶሙ ወርቅ ገመጾሙ ልቦሙ ለነገሥት። ገሚጸ ፍትሕ ትግምጽ ፍትሐ ነዳይ -(መጽ -ምስ ራ፯ -፳፫ -፪። ዘፀ ፳፫ - ዲድ -) ትግሬ ግን ገመጸ ብሎ ደኸየ ድኻ ኾነ ይላል

ገማሲ -(ሲት ስያን ያት፤ መስት) የሚገምስ ገማሽ ራሽ ሰራ ሸራፊ መንዛሪ ራሽ

ገማዒ መገምዕ -(ዕት ዓን ዓት) የሚቈርጥ ሸላች ላጭታ ገያሪ ሸክላ

ገማዲ -(ዲት ድያን ያት) የሚጐምድ ቍራጭ ዐጫ ገማጅ።

ገማዲም -ስመ ነገድ ስመ ትውልድ ያፌታውያን የጎሜር ራጮች -(ሕዝ፳፯ -፲፩)

ገምል - ፊደል ሣልስ ገ፤ በአበገደ ረቦች ጂም ይሉታል

ገምኖ ኖት -(ገመነ ይጌምን ይገምን) ማግመን ማሳረር ጥበስ ማሳደፍ ማኵለፍለፍ ማርከስ ማስነወር መለወጥ መቀየር የቃል የነገር። ኀፀብኩ ገርየ ፎኑ ጌምኖን እለ ገመኑ ልባሲሆሙ ገመነ ይሁዳ መቅደስየ እለ ይጌምኑ ስመ ቅዱሰ፤ እስመ ገመንዋ ለዲና ኅቶሙ። ኢይገምን ቃሎ -(ማሕ፭ -፫። ራእ፫ -፬። ሚል፪ -፲፩ ኩፋ -፴። ዘኍ፴ -) አንዳንድ መጣፍ በገመነ ፈንታ ግመነ አገመነ ይላል፤ ያሰኝም። አገመኑ መሥዋዕተ ያጌምንዎ ሥጋሆሙ -(አዋል። ፪ጴጥ - - ይሁ - ራእ፳፩ -፰። - ዘኍ፭ -፲፱ -፳። አመረን አእመረ እንደሚል፤ ይህም እንደዚያ ነው

ገምዖ ዖት -(ገምዐ ይጌምዕ ይገምዕ) መቍረጥ መሸለት መላጨት የጠጕር ምዒ ርእሰኪ። ወይገምዖ ጽሕሞሂ -(ሚክ፩ -፲፮ ኢሳ፯ -) ማለዘብ መፋቅ  መላግ ማስተካከል ልጩ ራስ ማስመሰል የርጥብ ሸክላ የምርግ የልስን ትግሬ ግን ገምዐ ብሎ መከረ ይላል ምስጢሩ ዚያው ማለዘብ ይገባል

ገሞራ -(ጽር ጎሞራ። ዕብ ዐሞራ) ስመ ሀገር አካቶ ፈጽሞ እሳተ መዐት ከዘነመባቸው ካምስቱ አህጉረ ሰዶ  ኣንዲቱቴ -(ዘፍ፲፫ -) ዘይገብሩ ግብረ ሞራ -( - -፵፰)

ገሞራዊ -የገሞራን ሥራ የሚሠራ ወንድ ኹኖ ወደ ወንድ የሚኼድ በሴት ፈንታ ወንድ የሚፈልግ ከወንድ የሚዛወግ አድራጊ ወንድ ወይም ተደራጊ ወንዳገረድ፤ ወንድነቱን ክዶ ማይገባ ለወንዶች እንደ የሚኾን  መቀመጫውን የሚደቅን። ገሞራውያን -( - -፵፰)

ገሠሠ --ዳሰሰ፣-ገሲስ ገሰ ገሰሰ

ገሲስ ሶት -(ገሰ፤ ገሰሰ ይገስስ ይግስስ። ዕብ ጋሻሽ ሱር ጋሽ ግሻ ዐረ ጀሰ) መግሰስ መዳሰስ መዳበስ በእጅ መንካት ማባበስ መያዝ መጨበጥ። ወዘገሰሳሁ ደዊነ ዘኢይከውኖሙ ገሲስ በአደዊሆሙ ትግስሱ መሲሓንየ ትግስስ ወኢትልክፍ -(ዮሐ፩ -፩። ዮዲ፲፩ -፲፫ መዝ -፻፲፫ ቆላ፪ -፳፩)

ገሳሲ -(ሲት ስያን ያት) -(334) የገሰሰ የሚገስ ገሳሽ፤ ዳሳሽ። ማቴዎስ ገሳሴ ስልከ ገሳሲት -(አዋል። አርጋ -)

ገሣጺ -(ጺት ጽያን ያት) ቁሙ የሚገሥጽ ቀጭ ተቈጭ መካር መምር ገሣጼ ሕዝብ ብዳን -(ስንክ -ኅዳ፲፫)

ገሥገሠ -(ጌሠ) ቁሙ፤ ቸኰለ አረበደ ፈጠነ።

ገሥጾ ጾት -(ገሠጸ ይጌሥጽ ይገሥጽ። ዕብ ያሳር) መገሠጽ፤ መቅጣት መቈጣት፤ አጥብቆ መላልሶ መምከር ማስተማር፤ እንደ ንጊያ መውቀር፤ በነገር ባለንጋ መግረፍ ማሰንበር ያባት የመምር የወዳጅ ገሥጾሰ ገሠጸኒ እግ ወለሞትሰ መጠወኒ ብከ ውሉድ ሥጾሙ ወመሀሮሙ ንጉሥ ጠቢብ ይጌሥጽ ሕዛቢሁ ገሥጾ ለዐርክከ በእንተ ሥጾቱ ለአብ ገሠጽኮ ዮናስ በቀስታመ ባሕር -(መዝ -፻፲፯ -፳፫ ፲፰ -፲፫ ፲፱ -፲፫ ፵፪ - ቅኔ)

ገረማ -በቁሙ፤ ናር ጌንጭ፤ የገብስ ዐረም -(ዐማርኛ)

ገረሠ -(ዐረ ጀረሰ ከካ። ዕብ ጋራስ፤ ተክካ) ጐረሠ ቃመ፤ አላመጠ ረጠመ ለቀ አላመ አለዘበ። ገረሸ -አገረሸ የደዌ። ባለቅኔዎች ግን ሠራ ይሉታል። ገረሠሠ ተገረሠሠ ማለት ዚህ ወጥቷል

ገረዘ -(ዕብ ጋራዝ) በቁሙ ቈረጠ ገረዘዘ ገዘረን እይ  ከዚህ ጋራ ነው ነከሰ ነሰከ ቀሐመና ቀምሐ እንደ ኾኑ እነዚህም እንደነዚያ ናቸው።

ገረፋ ጐረፋ -የፍርድ ቅጣት፤ ግርፋት እስራት። ፍዳ መርገም፤ ፍትወት የአዳም ኀጢአት እንደ ጐርፍ ከላይ ወደ ታች ካባት ወደ ልጅ የሚወርድ ባልሐነ ምጐረፋነ ወእምቀዳሚት በሳነ -(ቄር)

ገሪህ ሆት -(ገርሀ ይገርህ ይግራህ ገበረ ረየፀ ዕብ ጋሬህ አፍርሀ አርዐደ) ማረስ መነገድ፤ ማግራት መገራት፤ ገር ማድረግ፤ ማለስለስ ማለዘብ የመሬት የከብት።

ገሪማ -የሰው ገባሬ ተኣምር ግሩም፤ ተስዐቱ ቅዱሳን አንዱ ይሥሐቅ። ገሪማ የግብር ስም ነው። ገሪማ ረምከኒ -(ድጓ)

ገሪም ሞት -(ገረመ ይጌርም ይግርም። ዕብ ጋራም ሰበረ ጐረመመ) መግረም መድነቅ፤ መፈራት ግሩም መኾን፤ ማስገረም ማስደነቅ ማስፈረት፤ ሌላውን፤ የመልክና የክብር የታላቅነት ወይም የክፋት ረሞሙ ዘኢኮነ ሩመ። ወይጌርም ምነገሥት ምድር። ትጌርሞ ወታደነግፆ ፈሄ እግዚአብሔር አል ዘይጌርም። መንግሥት እንተ ትጌርም እምኵሉ መንግሥት -(መዝ -፲፫ ፸፭። ሢራ፬ -፲፯ ፴፩ -፲፰ ሱቱ -ዕዝ፲፪ -፲፯)

ገሪር ሮት -(ገረ ገረረ ይግርር ይግርር። ገነየ) መገዛት መታዘዝ፤ ዜጋ ገባር መኾን። ለሊሆሙ ገረሩ ፈቀዱ ይግርሩ ሎቱ ይግርር ኤጲስቆጶስ ዘኢየሩሳሌም ካልኡ ምኤጲስቆጶሳት። ይገርር ሕገ እግዚ -(ኢያ፲ -፩። ዮሴፍ - -፬። ሮሜ፰ -) ገርገረን እይ፤ የዚህ ዲቃላ ነው

ገሪዛን -(ጽር ጋሪዚን። ዕብ ግሪዚም) የተራራ ቍርጥ የኾኑ የቡራኬ ቃሎች የሚነገሩበት ተራራ ጌባልን እይ የዚህ ወንድም ነው -(ዘዳ፳፯ -፲፪)

ገሪድ -(ገረደ ይገርድ ይግርድ ዕብ ጋራድ) ማግረድ ማምረት ግርድ ቂንድ ማውጣት  ፍሬን ከገለባ መለየት መፈልፈል ማሸት መጋረድ መሸፈን። ገረድ ግሪዶ መኾን። ርደደን እይ የዚህ ዲቃላ ነው። ጋሬዳ ማለት ዚህ ወጥቷል

ገሪፍ -ወጥመድ ዘረ መትር፤ መረብ መግለቦ ያሣ መያዣ፤ መጋፈፊያ -(ማቴ፲፫ -፵፯) ኀሠሡ ግበር ሎሙ ገሪፈ። መሥገርተ ሪፍ እን ታስተጋብእ ዘመደ ሎን ዓሣት -(ፊልክ -፻፳፭ አርጋ -) ዓምና ያለፈው ዓመት።

ገሪፍ ፎት -(ገረፈ ይገርፍ ይግርፍ ዕብ ጋራፍ ሳበ) መግረፍ መሸንቈጥ፤ በጅራፍ ባለንጋ መቅጣት። መግለቦ መሥራት፤ የተሠራውን መውገር መጣል ባሕር ማግባት ዓሣው ሲመላ መሳብ መጐተት ወደ የብስ ማውጣት

ገራሂ -(ሂት ህያን ያት ህት) ዐራሽ ፋሪ ነጋዴ ዐጣሪ ፈረስ በቅሎ ገሪ

ገራህታት ገራውህ -ዕርሾች ቅብቅቦች። ጥረየ ባግዐ ወአልሕምተ ወገራውሀ ዙኀ። ውስተ ኵሉ ገራውህ ሀሎ አብራም መንገለ ገራውህ። እመ ውስተ ካልእ ብሔር ራውህ -(ዘፍ፳፮ -፲፬ ኩፋ -፲፩ ማቴ፲፪ - ሲኖዶ)

ገራህት ገርዋህ -(ዐረ ቀራሕ ቂርዋሕ) ዕርሻ ቅብቅብ የለዘበ የለሰለሰ ዘር ለመቀበል የደረሰ ርሻ የሚመስል የበረሓ መሬት ሣርና ቅጠል ዛፍ የሌለበት አሸዋ ድቡሽት። ሠናየ ዘርዐ ዘራዕከ ውስተ ገራህትከ -(ማቴ፲፫ -፳፯)

ገራሪ -(ሪት ርያን ያት) የሚገዛ ተገዥ፤ ታዛዥ። አማንያን ቃለ እግዚ ወገራርያን ነገረ አኀ -(ገድ -ኪሮ)

ገርሃት ገራህው -ጣቆች የንግድ ቆች ሸቀጦች። መጽሐፍ ግን ገራህው በማለት ፈንታ ገራውህ ይላል፤ ባለሐዲሶችም ፍችውን ዕርሻ ይሉታል፤ ንባቡም ፍችውም ተሳስቷል። ዘይሣየጥ ሎሙ ገራውሂሆሙ -(ራእ፲፰ -፲፩) ገራውህ ያለውን ዚያው ባ፲፪ና ባ፲፫ ዘርዝሮ ተርትሮ የንግድ ዕቃነቱን ይናገራል።

ገርህ -ገር የዋህ ገራም ጭምት ልሙጽ ልዝብ ስላሳ ጣምና ሸካራ ያይዶለ የመሳል ዐይነት ካህን ዘያዐርግ ርባነ ይግበሮ ገርሀ አላ ይኩን ኵለንታሁ ምስቁለ በማኅተም -( -) መዳ ጣቃ የንግድ ሸቀጥ የሚሼጥና የሚለወጥ አስረው አክተው በሣጥን መልተው ካገር ወዳገር የሚወስዱት ገርህ ማለት ሥራው ያለቀለት ዝግጁ መኾኑን ያሳያል -(ሕዝ፳፯ -፳፬)

ገርሣ -ልዝብ ለስላሳ ልሻ የጠጕር ይነት እንደ ጭድ እንደ ገለባ ጭቃ የሚስማማ ርሻ ርሦ፤ ግርሻ -(ዐማርኛ)

ገርሣኒ -ያርብሓዊ ረዐይታዊ ይለኛ ጣሽ ጠምላሽ። ጺናዊ ማሕረጻዊ ማለት ነው፤ ጐራሽነትንም ያሳያል -(ገድ -አዳ) ለሽጕጥና ለነፍጥም ይሰማማል ጐራሽ ጐራሽ እንዲሉ

ገርሥ -(ሣት) የመዝጊያ ብረት ሳንቃውን መቃን የሚያዛውግ፤ የሚያቈራኝና ንድ የሚያደርግ፤ ወንዴና ብረት፤ ወንዴው በመቃን ላይ ሴቴው በመዝጊያ ተቸንክሮ ርስ በርሱ የሚሳካና የሚጓረሥ ወይም በሳንቃው ላይ እንደ ሳንቃ ኹኖ የሚለበጥና የሚጠረቅ። ወካዕበ ስተዳለወ ብርተ ብዙኀ ዘአልቦ መድሎት ገርሣተ ዋኅው፤ ወለባዕድኒ ብር -(፩ዜ -፳፪ -) ባለብሉዮች ግን ንሰለት ይሉታል

ገርዋህ -(ትግሬ) አጋዘን ቡኸር ገራገር ማለት ነው

ገርዜን -(ገንዜን ገኒዝ ገነዘ) ቀጭን ሸማ ጥሩ በፍታ ሻሽ ሐዲስ ልብሰ ክታን። አምጽኡ ልብሰ ገርዜን ለግንዘተ ሥጋሁ በሰንዱነ ርዜን ተገንዘ ወተቀብረ። ዘተጠብለለ በልብሰ ገርዜን ምሥዋዕ ይኩን መንጦላዕት ዘገርዜን ጹሕ ዘአልቦ ነውር ክድንኒ ገርዜነ ጸጋ ዘኢአነምዎ ቢባን በኪን -(ቅዳ አፈ ተረ -ቄር፲፮ አርጋ ኪዳ። ደራሲ)

ገርገረ -(ገሪር ገረ ገረረ። ዕብ ጋራር) ጐተተ ተሳበ ተጐተተ የጋሪ በቁሙ ገረገረ አቆመ፤ የይሎ የንጨት። ወገሸ አገረገረ ግር ግር አለ የከብት ግርግር ፍግርግር ወጋግራ ግርግራ ገረገራ ማለት ዚህ ወጥቷል

ገበለ -(ዕብ ጋቤል) ለወሰ አቦካ ላቈጠ የዶቄት የጭቃ።

ገበታ [1]-( ገባትው) በቁሙ የንጨት ለገን ወጭት ማቡኪያ ማሻ መለወሻ ወይም ማሣሻ ዝርግ ፍጣፋ ሉሕ ሰደቃ ዋልታም ይኾናል ወዲበ ገባትው በዘይገብሩ ናእተ -(፩ዜና -፳፫ -፳፱)

[2]-ገበታ -(ዕብ ጋብታ። ጽር ጋባታ) የቦታ ስም ፍታና ሜዳነት ያለው -(ዮሐ፲፱ -፲፫)

ገበታ ሐዋርያ -(ዐማርኛ) የመጽሐፍ ስም፤ ገበታዋሪያ ባቱ የሐዋርያት መልእክታ ያዕቆብ እስከ ይሁዳ ያሉት። ጽሐፋን በታ ያሰኘው ዕንጨቱ ነው ፍችውም ማእድ ማእደ ትምህርት ዘሠርዕዎ ሐዋርያት እንደ ማለት ነው

ገበነ -(ዕብ ጋቤን) አረጋ ዐየበ ዐይብ ደረገ፤ ወተቱን።

ገበዝ -ዳር ዳርቻ ጠረፍ። ተቀበሎ ዲበ በዘ ተከዚ -(ዘፀ፯ ፲፭)

 -ብርቱ ባቂ ዘበኛ በረኛ። እምነ ጽዮን ገበዘ አኵስም ሰዴድዎ ምሀገር እለ ገበዘ አኵስም ዕጣና ለገበዝ። ቦአ ውስተ ቤተ ክርስቲያን ዘገበዘ አኵስም ገበዝ የጽዮን ቅጥል -(ሥር -አኵ -ገ፹፱  መዋሥ። ስንክ -ግን፲፩)

 -የሹመት ስም የቤተ ክሲያን ሹም አስተንታኝ የሰሞነኞች አለቃ። ምስጢሩ ያው ባቂነት ነው። ቀይሰ ገበዝ። ኢይትለአክ ካህናት ወኢይኩን ካህናት ወኢይቀድስ ከመ በዝ -(ሥር -አኵ ቄድር -ገ፹፰) ,

 -መሐንድዝ ሊቀ ነደቅት ገበዝ አንባ እንዲሉ

ገበያዊ -መንገደኛ ነጋዴ ገበያተኛ።

ገበይ -(ትግሬ) መንገድ ጐዳና፤ ገበያ። ዘሩና ሥሩ ጉባኤ ው።

ገበጣ -በቁሙ፤ የጠጠር ዎታ ልቅሞሽ ቅልሞሽ፤ ግብጦች ወይም ጠጠር ጣዮች ያወጡት -(ተረት) ገበጣ ላዋቂ ወሬ ለጠያቂ ኢይትላሀዩ ብረ ሰንጠረዥ ወገበጣ -( - -፴፪ -)

ገበጥባጥ -የሆድ ትል ወስፋት ሹጥ ሥራይ ዘከመ ዝንቱ ወገበጥባጥ -(ኩፋ -፳፫)

ገቢስ ሶት -(ገበሰ ይገብስ ይግብስ ዕብ ጋባሽ፤ መላ። አው ገብስሶ፤ ሶት፤ ገብሰሰ ይገበስስ ይገብስስ) ማጋበስ መሰብሰብ የሣር የንጨት የኵረት፤ መምላት ማስተካከክል መምረግ መለሰን መቅባት መለቅለቅ የግድግዳ የግንብ። መምላት ውስጡን በኵረት መለሰን አፍኣውን በጭቃ፤ መለቅለቅ፤ በኖራ በበረቅ። ገየረን እይ።

ገቢር ሮት -(ገብረ ይገብር ግበር ዕብ ጋባር ኀየለ ጸንዐ) መሥራት ማድረግ መፍጠር ያልነበረ ነገር ማስገኘት የነበረውን ማዘጋጀት፤ ፍጥረትን ከፍጥረት ምሮ ሌላ ህላዌ ማቆም፤ እንደ ሥጋና እንደ ሸክላ እንደ ቤት እንደ ምንጣፍ። በሚሠሩት ሥራ ማየል መበርታት መሠልጠን ሃሊ መኾን። ስዱሰ ዕለተ ትገብር ብረ ገቤረ ግበር በከመ ዘዝኩ። ዘገብረ ሰማየ ወምድረ። ወገብሮ እግዚ ለሰብእ መሬተ እምድር ገብረ ወይነ እምፍሬ -(ዘሌ፳፫ - ዮዲ፪ -፲፫ -፻፳፫ ፍ፪ -፯። ኩፋ -) ገብረ ሥራ ኹሉ እየገባ እንደ ሥራው ስልት ይፈታል። ይግበሩ ውስተ ማሕቶት ቅብዐ ይደዩ በር እዴከ ዛቲ ጻሕል አንብር ያሰኛል -(ስንክ -ጥቅ፳። ቅዳ)

ገቢእ ኦት -(ገብአ ይገብእ ይግባእ ቦአ መጽአ። ገብአ ትግ ኮነ ይከውን) መግባት መጥለቅ መዝለቅ ወደ ውስጥ። መመለስ ወደ ኋላ መዞር መታጠፍ ተመልሶ መምጣት ቢኦትከ ውስተ ሥጋ ይትመየጥ ለገቢእ። ገብአ ቤቶ ገብእ ውስተ ምድር። ብኡ እምፍኖት እኩይ -(ዕር -ኢሳ፰ -፳፯ መክ፭ -፲፬ ጦቢ፰ -፲፩። ኢዮ፩ -፳፩ ኤር፵፪ -፲፭)

 -መኾን መያዝ መስጠት ገብኡ ታሐተ እደ ትሑት። ገብኡ ዘኢተወልዱ ደኃርት ይገብኡ ቅድመ ኮኑ ይከውኑ ባእነ ውስተ እደ ጸላእትነ ይግባእ ውስተ እደ ብእ -(ሢራ፲፩ -፵፬ -፱። ማር፲ -፴፩። ሱቱ ዕዝ፲ -፴፮። ሉቃ፳፬ -)

ገቢዝ ዞት -(ገበዘ ይገብዝ ይግብዝ) መለካት መወሰን፤ ዙሪያውን መቍረጥ መከለል የመሬት የሕንጻ። መጐበዝ መገበዝ ጐበዝ ግብዝ መኾን። መጋበዝ -(ዐማርኛ)

ገባሪ -(ሪት ርያን ያት፤ በርት) የሚሠራ ሠሪ አድራጊ ፈጣሪ ፈጻሚ። ሐዱ ገባሪ በማለት ፈንታ ሐዱ ግብር ይላል የጣፊ  ስሕተት ነው -(ሃይ -አበ -ጎር ብን) ብር ምስለ ገባሪሁ ጥበብ ባሪተ ኵሉ። ባርያነ ብርት በርተ ዐመፃ -(ጥበ፲፬ - -፭። ፲፭ -፱። መዝ -) ገብረ በመላላቱ የቀተለ ርዌ ሺኾን በመጥበቁ ቀደሰን ይመስላል መምሰሉም ይህ ነው

ገባራዊ -ዝኒ ከማሁ ገበሬ የነገር የሥራ -(፪ጢሞ - -፲፭ ክብ -ነገ። ስንክ -ኅዳ፲)

ገባር -(ራት። ዕብ ጊቦር ብርቱ) በቁሙ ገበሬ ሠራተኛ፤ በግድ የሚሠራ ልበቱን ገንዘቡን ለሹም የሚያፈስ  ሹማምት እንደ ወደዱ የሚያደርጉት ባለርስት ባሪያ። -(ግጥም፤ ቡልጌ ያበቡት ባለጌ ጤፍ ሲወቃ) የየጀርሳ ዝኆን የከረመ እንደኾን ስንኳን ገባር ጢሰኛም አይኾን መጽሐፍ ግን በገባራት ፈንታ ገባር ይላል፤ አያሰኝም ወገባሩ ኅዳጥ ይወስክ ባረ ናሁ ዐስቦሙ ገባር ወሢመ ዲቤሆሙ ሊቃነ ባር ይሣቅይዎሙ በግብር ዳእተ ገባር -(ማቴ፱ -፴፯። ዕ፭ -፬። ዘፀ፩ -፲፩። -) ገባረ ሪፍ ገባራት። ምጽአ ባራተ ያንኅሉ ረፍተ -(ታም -ማር ስንክ -ነሐ፩ አዋል)

ገባኢ -(ኢት እያን ያት እት) ቅጽልና ጥሬ የሚገባ ገቢ ተመላሽ፤ ተመላላሽ። ገበሬ ዐራሽ የለት ምንደኛ ሙያተኛ ራሚ ፋሪ አሽከር ወታደር አገልጋይ ሎሌ ገባኢ ይጻሙ በተገብሮታ ለምድር ገባኢ ዘይሌፎ ዐስቦ ይትዓሰብ ገባእተ ገባኢሁ ለኤፍሬም -(ጥበ፲፯ -፲፮ ኢዮ፯ -፪። ማቴ፳ -፩። ዮዲ፮ -)

ገብላ -(ላት) ገን ከግንድ ከደንጊያ የሚሠራ ማቡኪያ ማላቈጫ የከብቶች ውሃ ማጠጫ እንደ ገበታ የተጠረበ የተፈለፈለ። ዘየአምር ወኢይገብር ይመስል ብላ ዘምሉእ ማየ ዘእምኔሁ ይሰትዩ ብዙኃን ወያነጽሕ ብዙኃነ እምርስሐቲሆሙ። ገብላተ እብን ዘያሰትዩ ባቲ ፍራሰ -(ፊልክ -፻፱ ስንክ -መስ፩ ዘፍ፴ -፴፰ -፵፩። ዘፀ፪ -፲፮)

ገብሳሲ -(ሲት ስያን ያት ሰስት) የሚለስን ለሳኝ፤ ቀቢ ለቅላቂ።

ገብስ -በቁሙ ገም የብር እኽል ነጭ ነጫነጭ ማለት ነው። ገብስማ እንዲሉ።

ገብር -( አግብርት) ባሪያ ገዥ ገልጋይ የተማረከ ወይም የተገዛ ግዝ ውላጅ ገብር እግዚኡ ቦኑ ውእቱ ገብር ያዕቆብ ልደ ቤት ሥአ ርኣያ ገብር ከመ ኪያነ ይቤዙ እግዚእ ኮነ ብረ። አግብርትየ ወአእማትየ አግብርተ ጢአት -(ኢሳ፳፬ -፪። ኤር፪ -፲፬ ፊልጵ፪ -፯። ድጓ ግብ፪ -፲፰ ሮሜ፮ -፲፯)

()          ገብሮ ሮት -(ገበረ ይጌብር ይገብር) (ገበረ ይጌብር ይገብር) -(ጥገ) መገበር ማረስ መቈፈር ገበሬ መኾን መነገድ ንግድ ማድረግ። -(ጥበ)  መገበር ግብር መስጠት በግድ መሥራት፤ ባሪያ ገባር ዜጋ መኾን። መጽሐፍ ግን በገብረና በገበረ ፈንታ ተገበረ ይላል ያሰኝም። ተገበሩ ጽድቀአለ ይትጌበሩ ሜላተ ዘይትጌበራ ምድር ዘይትጌበር ራህቶ ሐመር እንተ ትትጌበር እምርሑቅ ተገበሩ እን ስከ አአ ንትጌበር ወንረብሕ -(ዕብ፲፩ -፴፫። ኢሳ፲፱ -፱። ምሳ -፲፩ ፳፰ -፲፱ ፳፱ -፴፪። ሉቃ፲፱ -፲፫ -፲፭። ያዕ፬ -፲፫)

ገብቦ ቦት -(ገበበ ይጌብብ ይገብብ ዕብ ጋባብ) መሰብሰ ማግባት መክተት። መቈፈር መቅበር። ማጓበብ መንጓበብ፤ ጕባ ጐባባ መኾን እንደ ቀስት። ጕቦ መስጠት መቀበል

ገብገብ ገብገቦ -አዳራሽ ቀላ በረንዳ። ሸንጎ ደባባይ ዐውደ ምቅታል ወወፅአ ውስተ ብገብ። አዘዘ ይሰድዋ ብገቦ ወይምትርዋ ክሣዳ -(ዮዲ፲ -፳፪ ስንክ -ኅ፮)

ገብጥ -የሆድ በሽታ ብስና ጓታ እህታ የሚቈርጥ የሚጐራብጥ የሚያስቀምጥ። ቅንጣዌ ወገብጥ። ያበዝኆ ገብጥ ሥሥዕት -(ሢራ፴፬ - ፴፯ -)

ገቦ [1]-ጐንገቢእ ገብአ።

 [2]-ገቦ -( ገበዋት ሱር ጋባእ ዐረ ጀንብ ጃኒብ) ጐን ጐድን ወገብ ወገን ማእዝን ቅርብ አጠገብ። ግንቦት ማለት ከዚ ወጥቷል፤ ክረምት ማለት ነው፤ ከጻዴ ጋራ ይሰማማል ትሰክብ በገቦከ ዘፀጋም። ገብር እኩይ ሥትሮ ገበዋቲሁ ይትዐጸፍ ርትዐ ውስተ ቦሁ ወልድከ ዘወፅአ ምገበዋቲከ። በገቦ መስዕ ወእምገበዋቲሁ ውእቱ መንበር ዝማድ እለ በዋት። ገዳም ዘገቦ ይታይም ኖመት በገቦሁ -(ሕዝ፬ -፬። ራ፵፪ -፭። ኢሳ፲፩ -፭። ነገ - -፲፮ መዝ -፵፯። ራእ፬ -፮። - -፳፬ - ዮዲ፬ -፮። ስንክ -ኔ፴)

ገቦታ -የሰው ስም። ምስለ ቦታ ወታራ -(አስቴ፩ -፲፪)

ገቲት ቶት -(ገተ ገተተ ይገትት ይግትት) መጐተት ማንገላታት እንዳለወገን ማድረግ። ገትገተ ብሎ ገተገተ ገትጋታ ማለት ማርኛው ዚህ ወጥቷል።

()          ገት [1]-(ትግሬ) ብዕል ሀብት፤ ጌትነት።

 [2]-() ገት ብዕል ሀብትገዪት ጌተ

ገነ -(ይገንን ይግንን ገኒን ዕብ ጋናን) ገነነ ገናና ኾነ ታበየ ተንጠራራ። ተከለ ጋረደ መከተ ጠረ ቀጠረ መገን ዚህ ወጥቷል ጋሻ ማለት ነው ገነገነና ጐነጐነም የዚህ ዘር ናቸው ግስነቱ ሐውልትና ገቢር እንደ ኾነ አስተውል።

ገነበ -(ዕብ ጋናብ፤ ሰረቀ) ገነባ ግንብ ሠራ፤ ወይም አፈረሰ ፈረ ሰረሰረ፤ ለመስረቅ። መገንባት የሸክላንና የጡብንም ሥራ ያሳያል ገንቦ ገንቦኛ እንዲሉ።

ገነት -(ታት ጋን ሱር ጋንታ ዐረ ጀነት) የተክል ብዙ ዛፍና ንጨት ቅመም የሚበቅልበት፤ ምንጭ ያለው ውሃ የሚገባው፤ የታጠረ የተቀጠረ ገነት ዕጹት ገነተ ቅማሕ ወቦ ህየ ገነት ጸደ ሐምል ወውስተ ውአቱ ገነ ዐቃቤ ገነት ገበርኩ አዕጻደ ሐምል ወገነታተ ወተከልኩ ውስቴቶሙ ዕፀወ ዘይፈርዩ -(ማሕ፬ - ዳን ፯። ዮሐ፲፰ -፩። ፲፱ -፵፩። -፲፭። መክ፪ - -)

 -ዓለመ ጻድቃን፤ አዳምና ሔዋን የነበሩበት፤ እግዜር ያበጀው ያዘጋጀው ረፍትና የሕይወት የተድላ የደስታ ቦታ ስለ ልናው ማይ የሚባል ልዑል ሀገር ልዑል ማኅደር -(ዘፍ፪ - -፱። -፳፫ -፳፬። ፲፫ -፲። ፪ቆሮ -፲፪ - -) ገነትሰ በእንተ ልዕልናሁ እምድር ይሰመይ ሰማየ ወሐዋርያኒ ሰመያ ለገነት ሰማየ ሣልሲተ። ቀዳሚታሰ ይእቲ ምጽናዓት ንተ ይቤ በእንቲኣሃ እግ በውስተ ሪት በልሳነ ሙሴ ነቢይ፤ በቀዳሚ ብረ እግ ሰማየ ወምድረ ወካልእታኒ ይእቲ ጠፈር ዘፈለጣ እግዚአብሔር ማእከለ ማያት ወሣልሲት ይእቲ ገነ በከመ መያ ጳውሎስ ሐዋርያ ወነፍሳቲሆሙ ለጻድቃን ይከውና ውስተ ገነ እስከ ይመጽእ እግዚእ ፍዳ ወአሜሃ ይከውን ሎሙ ተሳትፎ ምስለ ክርስቶስ ወያጌጹ በእንተ ውእቱ ቃለእግዚእነ ለፈያታዊ ዘየማን ትሄሉ ምስሌየ ውስተ ነት -(ፊልክ - ቃ፳፫ -፵፫)

 -መጽሐፍ የመጽሐፍ ስም፤ ዜና አበው ገድለ መነኮሳት። ስመ ጸሓፌ ገነት ይቤ መጽሐፈ ገነ ዘጸሐፎ ጰላድዮስ -(ፊልክ -፲፮ና -፴፱) በገነት መልካምና ክፉ የሚያሳውቅ ዕፀ አእምሮ እንዳለበት፤ በዚህም ጽድቅን ከኀጢአት ሐሰትና ምትሀት የሚያስለይ፤ ያምላክንና የመልአክን መንገድ ከሰይጣናት መንገድ ይቶ የሚያሳይ የሚያስረዳ የገነትን ተድላ የሚያወራ እንደ ማየ ሕይወት የጠራ ዕውቀትና ትምርት ስላለበት በምሳሌ ገነት ብለውታል ብርሃን ማለት ነው። አበዊነ ይሰምይዎ ለብርሃነ አእምሮ እግዚአብሔር ገነተ ልቡ ባሕታዊ ገነተ ድላ ውእቱ -(አረጋ -ድ፲፮ ፵፮)

ገነጰ -(ዐረ ከነበ) በሰበ አከበ፤ አከ ተተ

ገነፈ -(ይገንፍ ይግንፍ ገለፈ) ነፈ ሣለ መሰለ፤ ቀረጸ ጠበ አጠራ ወይም ለማጥጠብ ባመድ በረመጥ ጐነፈ ቀቀለ የልብስ የሸክላ ነፋ አገነፋ አማሰለ ዝሓን በሙቅ ውሃ ዘፈቀ ነከረ

ገኒሕ ሖት -(ገንሐ ይገንሕ ይግናሕ ዕብ ጋናሕ) መገንታት መጮኽ መቈጣት ድምፅን ማግነን ቃልን ማበርታት፤ መታበይ መኵራት ይለ ቃል ማውጣት። ሠጾ እግዚ ዳዊት በቃለ ነቢይ ንዘ ይገንሕ። ወትገንሖሙ ለኃጥ በቃለ ስክየት -(መጽ -ምስ ቅዳ -ያዕ) ጐሀነን ተመልከት፤ የዚህ መንቲያ ነው

ገኒን -(ዐረ ጀኒን) ጭንጋፍ የተናቀ ወራዳ ታናሽ ርካሽ። ኢትሢጣ በሤጠ ገኒ -( - -፲፰)

ገኒዝ ዞት -(ገነዘ ይገንዝ ይግንዝ። ዕብ ጋናዝ ቀበረ ወረ) መገነዝ መከፈን መጠቅለል መለፈፍ ማልበስ ማጐናጠፍ ማሰር መቋጠር መክተት የሬሳ የገንዘብ -(ማቴ፳፯ -፶፱ ዮሐ፲፱ -) ገነዞ ሴት ወአንበሮ ውስተ ታቦት። ምስለ ፈዋት ገነዘ ወቀበረ ድኖ። ትግንዝዎ እስመ ሕያው ውእቱ። ሶበ ሞተት ብእሲት በወሊድ  ይኅፅብዋ ወይግዝዋ በካልእ ልብስ። -(ግጥም) አጥበው ገንዘው ሲሰጡት ምን ይብላ መሬት -(ቀሌ። ስንክ -ነሐ፩ ባሮክ - -፳፪)

ገናሒ ግኑሕ -የሚቈጣ ጡ፤ ተሳዳቢ።

ገናዊ -(ዊት ውያን ያት ነውት) የተጀነነ የሚጀነና ጋኔን ዛራም ጋኔናም ካህነ ጣዖት ነቢየ ሐሰት። ገናዌ ማልክት ገነውቱ ቤል ገነው ለዳጎን። ወገብረ ገነውተ ማልክት -(ቈስጠ -፳፯ ዳን፲፫ -፰። ነገ - -፭። ነገ -፲፪ -)

ገናዚ -(ዚት ዝያን ያት) የሚገንዝ ገናዥ፤ አማዋች ቀባሪ ከታች።

ገናዪ -(ዪት ይያን ያት ነይት) የሚገዛ ተገዥ ጋጅ አመስጋኝ

()          ገናፍ ገናፊ -(ጽር ግናፊስ። ዕብ ኮቤስ) ልብስ ጣቢ ዐጺደ ገናፊ -(፬ነገ -፲፰ ፲፯)

ገንሕ አው ገንዕ -(ዓት አግንዕት) ጋን፤ ገናና ታላቅ የሸክላ ዕቃ የጠላ የጠጅ ጥመቂያ የልብስ ማጨቂያ። የጋን ሸማ እንዲሉ ገንዐ ወልጕነ -(ገድ -ተክ)

ገንበረ -ገነበረ አገነበረ ባዕድ ኾነ።

ገንታ -ቀን መለከት ቱልቱላ ንትቶ የሚጮኽ። ዐዊዶሙ ምስለ ገንታ ወግርጣጥ በከበሮ ወጸናጽል -(ታሪ -አኵ)

ገንዕ -ጋንገኒሕ ገንሐ ገንሕ ዐና ሐኀ እንዲወራረሱ አስተውል።

ገንዎ ዎት -(ገነወ ይጌኑ ይገኑ ዐረ ጀነ) መጀነን ጋኔን መሳብ ለጋኔን ለጣዖት መገዛት ማገልገል፤ ካህነ ጣዖት መኾን መባል። ገነየንና ገኒንን እይ፤ የዚህ ናቸው

ገንዘብ -(ሱር ግኑዝባ) በቁሙ፤ መድፍን የተቀበረ ወርቅ ወይም በሣጥን የሚደበቅ -(ዲድ -) ከዘገበ መጥቶ በገንዘ ላይ ተደርቧል

ገንዜ -ዝኒ ማሁ፤ ልብሰ መግነዝ ዜንን እይ ስለ ተዋረሱ ገረዘ ወስዶታል

ገንዜን -ዝኒ ማሁ፤ ልብሰ መግነዝ ዜንን እይ ስለ ተዋረሱ ገረዘ ወስዶታል

ገንይ ዮት -(ገነየ ይገኒ ይግኒ አው ገንየ ይገኒ ይግነይ። ዐረ ጀነአ። ሱር ግናእ። ዕብ ካናዕ) መገዛት ማጐንበስ መስገድ መዋረድ መታዘዝ ማገልገል መጸለይ ማመስገን መየበብ ምስጋና ማቅረብ መለማመጥ ማቈላመጥ። ምስጢሩ ነው፤ መገዛትና የመገዛት ሥራ ወለጽድቀ እግዚአብሔርሰ ስእኑ ገንየ። ግነዮ ወስገዱ። አፎ ሠመርክሙ ትግነዩ ለአቢባል። ኵሉ ልሳን ይገኒ እግዚ። እገኒ ለከ እግዚኦ በኵሉ ልብየ ወነዳይሰ ሊሁ ይትገፋዕ ወለሉሁ ይገኒ -(ሮሜ፲ -፫። ዳን፫ -፭። ዮሴፍ ኢሳ፵፭ -፳፫ መዝ -፱። ራ፲፫ -) በገነየ ፈንታ ተጋነየ ይላል፤ በጐንደየ ፈንታ ተጐናደየ እንዲል። ትጋነያ ብእሲትየ እን ይትጋነይ ተጋነይ ሶበ ትኤብስ ተጋነየ ገጸ እግ ተጋነዩ ወሰገዱ ቅድሜሆሙ። ስኢል ወተጋንዮ -(ኢዮ፲፱ -፲፯ አስቴ፯ -፰። ሢራ፲፰ -፳፩ ፬ነገ -፲፫ -፬። ቀሌ ፩ጢ - -)

 -መገኘት መምጣት መፈጠር መወለድ -(ዐማርኛ)

ገንደበ -(ትግሬ) አረጀ ገነጀበ ገንጀባ ኾነ

ገንዶር [1]-ጕንደ እግር፤ ማእሰረ እግር፤ የግር ግንድ የንጨት ዛንጅር። ወስከምት የቀንበር ይነት መንቈር ባላ እንዛዝላ የወይፈን መቅጫ አዘዘ ይደዩ ውስተ ክሣዶሙ ጋጋተ ወገንራተ ውስተ ገሪሆሙ ወይሰድዎሙ ውስተ ቤተ ሞቅሕ ክብድ ገንዶራቲሁ -(ስንክ -ታኅ፲፪ ሢራ፴ -፴፰)

[2]-ግንደ  ርቍር ንዝዛ፤ በዚያው በግንዱ ውስጥ ማር የሚሠራ ወይም የጢንዝዛ ወገን ሌላ ጥቍር ደረቅ ራሳም ሸካራ

ገንጰለ -(ተቀ ) ለወጠ ገለበጠ ገለባበጠ -(ገነበለ አገነበለ ገንባሌ ለበሰ) እንዘ ይገነጵሉ ጽድቀ ውስተ ዘኢመፍትው ፈድፋደ ይዔምፁ በዝንቱ ገንጲሎሙ ጽድቀ በሐሰቶሙ። ወገንጰለ መናብርቲሆሙ -(ቄር -ጳላ ገድ -ተክ)

ገንጳሊ መገንጵል -የሚለውጥ የሚገለብጥ ለዋጭ ገልባጭ።

ገንፈለ -(ገለፈ) አቦካ ለወሰ ጡብ ሠራ ተኰሰ። ወይገነፍሉ -(ታሪ -አኵ) በቁሙ ገነፈለ ወደ ላይ አለ ፈላ ፈሰሰ የወጥ የመጠጥ -(ዐማርኛ)

ገንፎ -(ዐማርኛ) በቁሙ፤ ገዐት በውሃ የበሰለ ዱቄት የጕንፋን መድኀኒት -(ተረት) ለጕንፋን ምሱ ገንፎ በትኩሱ።

ገአረ -ጋረ ጣረ  ጮኸግዒር ገዐረ

ገዐር ገዓር -ገዓር፤ ጩኸት ጭንቅ ጣር ጋር መራራ ቃል የሐዘን የደዌ የመከራ ሜት ገዓ ምስኪናን። ብካየ ገዓሮሙ። ገዓሮሙ ለሙቁሓን ወይብጻሕ ቅድሜከ ዐርየ -(ኢዮ፴፬ -፳፰ ኤር፫ -፳፩ መዝ -፸፰ -፻፩)

ገአት -ገንፎግዒት ገዐተ።

ገዐት -ገንፎ መንካኮ፤ አጥሚት እንቀት፤ ያራስ የሕፃን ያሮጌ የበሽተኛ ምግብ። -(ተረት) ብኖር ዓመት ብበላ ገዐት አስተዳሉ ሎሙ ዳጠ ገዐተ ስመ ድዉያን ሙንቱ -(ፊልክ -፸፱)

ገዐዘ ግዕዘ -ነቀፈ ጠረ አጋዘ፤ግኢዝ ገአዘ ግእዘ ግእዝ።

ገዓሪ ግዑር -(ራን ራት  ዕርት) የጋረ የጣረ ጋረኛ ጣረኛ። ግዑራን -(ቄር -)

ገኣዚ -(ዚት ዝያን ያት አዝት) የሚነቅፍ ነቃፊ ወቃሽ ከሳሽ፤ ፈራጅ -(ያዕ -፲፩)

ገዓዝ ጋዕዝ -ጓዝ መንገደኛ ቤተ ሰብ። ተቃወመከ በፍኖት ወአምተረከ ጋዕዘከ እለ ጻመዉ በድኅሬከ ተንሥኡ ምስለ ገዓዞሙ -(ዘዳ፳፭ -፲፰ ዘኍ፲ -፲፪)

ገዊሕ ሖት -(ጎሐ ይገውሕ ይጉሕ ዕብ ጊያሕ) መጎሕ ሙውገግ መፍገግ ወገግ ፈገግ ማለት የንጋት ምልክት ማሳየት፤ ሐመድ ያህያ ሆድ መምሰል የሰማይ ሶበ ይገውሕ። እንዘ ይገውሕ ጽባሕ ኮከበ ጽባሕ ዘይሠርቅ ሶበ ይገውሕ። ወይገውሕ ሶቤሃ ብርሃንከ -(ኢያ፮ -፲፭፪ነገ -፲፯ -፳፪ ኢሳ፲፬ -፲፪። ፶፰ -)

ገዊል ሎት -(ገወለ ይገውል ይጉል ዐረ ጃል ጋል) ማጠር መቅጠር ዘለሳ መጣል መካብ መክበብ ዙሪያውን መዝጋት የበረት ያታክልት ገዘዘንና ጸቈነን ተመልከት።

ገዊር ሮት -(ጎረ ይገውር ይጉር ዕብ ጋር) መቅረብ መጠጋት ቅርብ አጠገብ ጥገኛ መኾን፤ በቤት በቦታ። ጕር ጐሬ ማለት ዚህ ጥቷል

ገውሣን -(ዐረ ገውሻን) የሰልፍ ልብስ ጌጥ ሽልማት ድርዕ ጥሩር የመሰለው ኹሉ ወኮነ ዕሌሁ ገውሣን ዘወርቅ ዘንኩር በሪሁ -(ዮሴፍ)

ገውዛ -(ዐረ እልጀውዛ) ኮከ ኮከብ ካ፲፪ መናዝል አንዱ። ዕጥፍ ጥንድ መንታ ኹለት ማለት ነው መልኩ በሥዕል ሲያዩት ባልና ሚስት ወንድና ሴት ይመስሳል። ኮከብነቱም የግንቦት ነው ከፀሓይ ጋራ ፴፩ ዕለት ኬክሮስ ይመግባል -(አቡሻ -)

ገውዝ -(ዕብ ኤጎዝ ሱር ጋውዛ ዐረ ጀውዝ) በቁሙ የታወቀ የተክል ዛፍ ስም፤ የፍሬው ጥንት ደረቅ ጠንካራ ውስጡ የሚበላ መንታነት ያለው ዘይት የሚኾን ሌላውም የገውዝ ዐይነት ኹሉ ገውዝ ወለውዝ ተከልከ ገውዘ ይበቍልኑ ይን -(ሆሴ፬ -፲፫ መቃ -ገ፭)

ገዚም ሞት -(ገዘመ ይገዝም ይግዝም ዕብ ጋዛም ሱር ግዛም ዐረ ጀዘመ) መግዘም መቍረጥ መጐንደብ መመንደብ መመልመል መጨፍጨፍ ድል መንሣት ማሸነፍ። ጐደበን እይ የዚህ ነው ግዝሙ ዕፀዊሃ ይገዝም በጕድብ መሠንየ ርዝከ ዘማ ሕይወትየ -(ኤር፮ -፮። ፳፪ -፯። ኢዮ፲፱ -)

ገዚረት -(ዐረ ጀዚረት) ደሴት የየብስ ራጭ፤ ባሕር ያጠረው የከበበው መሬት ገር አፈ ወርቅ ዘሞተ በስደት በውስተ ገዚረት -(መጽ -ምስ)

ገዚር ሮት -(ገዘረ ይገዝር ይግዝር ሱር ግዛር ዕብ  ጋዛር ናማል። ዐረ ጀዘረ ኀተነ) መግዘር መግረዝ የብልትን ሸንኰፍ ርጦ መጣል፤ ወይም በጭራሽ መስለብ -(ዘፍ፲፯ - -፲፩ -፳፫ ሉቃ፩ -፶፱። -፳፩) ዘገዘረ ወልዶ በእንተ ደዌ ዝሩ እከ ብክሙ -( - -፴፫ -፭። ኤር፬ -፬። ዘዳ፲ -፲፮)

ገዚእ ኦት -(ገዝአ ይገዝእ ይግዛእ ዐረ ጀዘአ ሰጠ ዐደለ) መግዛት መዋጀት መጌትየት ጌታ መኾን በገንዘብ በዜጋ መሠልጠን። መቍረስ መክፈል መስጠት ማደል፤ ማሳለፍ ማገልገል በጌትነት ወይም ባሽከርነት ማብላት መቀለብ መከባከብ ለማሳደግና ለማሥባት የሕፃን የከብት መጽሐፍ ግን በገዝአ ፈንታ አመግዝአ ይላል ይእተ አሚ ያመገዝእ ሰብእ ጐልተ ወክልኤተ ባግዐ -(ኢሳ፯ -፳፩) ግዕዘን እይ የዚህ ጎር ነው

ገዚዝ ዞት -(ገዘ፤ ገዘዘ ይገዝዝ ይግዝዝ። ዕብ ጋዛዝ ጊዛህ) መግዝዝ፤ መሸለት መቍረጥ መቈጥቈጥ ማጨድ መጨርገድ የጠጕር የፀምር የሣር የቅጠል። የተቈረጠውን መጀጐል ማጠር መቅጠር መጋረድ መከለል የቡቃያ የተክል ገድገደን ተመልከት። መጽሐፍ ግን በገዘዘ ፈንታ አግዘዘ ይላል አያሰኝም አግዘዝኩ ሎቱ በክንፍክሙ ዐውድየ አግዝዙ -(ኢሳ፭ - ስንክ -ኅዳ፳፬)

()          ገዚፍ -(ፋን ፋት ዛፍ) የገዘፈ ወፍራም ደጓሳ ደንዳና ልሕ ሥጋዊ ገዚፈ ባል ለምንት ውሰብከ ብእሲተ እስተ ወአንተኒ ብእሲ ገዚፍ ወዐቢይ ገዚፍ ምድ ልብስ ገዚፍ ምእስት ገዚፋን። አብትር ዘኀጺን ገዚፋት ምክር ዚፍ -(ፈላስ -ገ፶፫ ፹፩ ንክ -ጳግ፩ - -፳፫ -፮። ገድ -ተክ ማር -ይሥ፳፪ -)

ገዚፍ ፎት -(ገዝፈ ይገዝፍ ይግዘፍ) መግዘፍ መወፈር መደንደን መዳጐስ መሥባት፤ ወፍራም ደንደሳም መኾን አጽባትየ ይገዝፍ ይጸን ምሐቌ አቡየ። ናሁ ገዝፋ ልባቢክሙ ወኮና አእባን ከመ ይግዝፍ ልቡ ወኢይጽልም አእምሮቱ -(፪ዜና - -፲። ዮሴፍ - -)

ገዛሚ -(ሚት ምያን ያት ዘምት) የሚገዝም የሚቈርጥ ራጭ።

ገዛሪ -(ሪት ርያን ያት፤ ዘርት) ቁሙ የሚገዝር ገራዥ ባለወግ ትቤሎ ማርያም ዮሴፍ ምጽእ ገዛሬ ጠቢበ -(ስንክ -ጥር፮)

ገዛእ ገዛኢ -ገዛእ ገዛኢ -(ኢት እያን ያት እት) የሚገዛ ገዥ ጌታ ባለቤት። የሚሰጥ የሚናኝ ቀጅ አሳላፊ ዳይ፤ የድግስ አገልጋይ ደቀቀ ዛእየ በወይነ ማሕሌት እንተ ይቀድሕ ገዛኢ ደቀ ጽርሕ ወገዛእት። ቦአት ይእቲ ወክልኤ ገዛእቲሃ። ወገዛእትሰ እለ ድሕዎ -(ኢዮ፲፱ -፲፯ ስንክ -ታኅ፳፱  ኢሳ፴፱ -፯። ዳን፩ -፵፮። ዮሐ፪ -)

ገዛዚ መግዝዝ -የሚቈርጥ የሚጀጕል፤ ጀጐል ሠሪ

ገዝም -(ማት) በቁሙ ቃዳ ተለላ ፈፋ እመም መዛሪያ ትልም በዘርና ባረም ባጨዳ ጊዜ ሠራተኞች ከዳር እስከ ዳር የሚያወጡት ፍል

ገዝአ -ገዘገዘገዝዐ።

ገዝዐ -(ዕብ ጋዛ ዐረ ጀዘዐ) ረከረ ገዘገዘ፤ ቈረጠ ገረዘዘ የመጋዝ ዘዘ መኰንን ይቀንውዎ ወይሥትሩ ሥጋሁ ወይዝሐቁ ምእስቲሁ ወይግዝዕዎ በመጋዝዕ እደዊሁ ወእገሪሁ -(ስንክ -ጥቅ፳፭)

ገዪም ሞት (ጌመ ይገይም ይጊም። ዐረ ዓመ) መጎም መዳመን ደመና መልበስ በጉም መታፈን መሸፈን መጮኽ ማስገምገም ማስተጋባት የሰማይና የተራራ። ገመገም ማለት የዚህ ዘር ነው ጐሀነን እይ

ገዪሥ ሦት -(ጌሠ ይገይሥ ይጊሥ ጋየስ ሰበሰበ) -(ጥሰ) መሰብሰብ መከተት መሰለፍ ጦር ለመንገድ መዘጋጀት ከዚህ በኋላ መዝመት መገሥገሥ፤ ማልዶ መኼድ ነግህ አስቀድሞ ጎሕ ሲቀድ ወይም ዶሮ ሲጮኽ መነሣት። ገዩሠክሙ በጽባሕ አሌለ ገዪ በሌሊት ትገይሥ መንፈስየ ቤከ ነቂሀነ እምንዋም ንጊሣ ቤተ ክርስቲያን -(ዘፀ፲፱ -፲፮ ሉቃ፳፬ -፩። ኢሳ፳፮ -፱። ድጓ) ገሥገሠን እይ የዚህ ድርብ ነው

ገዪድ ዶት -(ጌደ ይገይድ ይጊድ ዐረ ጀይድ ጃደ በረታ) መፍጠን መሮጥ መፈርጠጥ መበርታት።

ገያሢ -ገያሢ -(ሢት ሥያን ያት) የሚገሠግሥ ገሥጋሽ ማላጅ ማለዳ ኻያጅ። -(ተረት) ገበ ላርፋጅ ቤተ ክሲያን ለማልጅ።

ገያሪ መገየር -(ርት ራን ራት) አቅራቢ አስጠጊ፤ ይሁዲ ድራጊ ኖራ አውጭ ሸያጭ ለሳኝ ቀቢ ለቅላቂ። መገይራን ወለወቀርት እብን -(፬ነገ -፲፪ -፲፪)

ገይሮ ሮት -(ገየረ ይጌይር ይገይር ዕብ ጋየር) በፍቅር በትምርት መሳብ ማቅረብ ማስጠጋት ሕዛብን ከጣዖ ማፍለስ ኦሪት ማሳመን መግዘር ይሁዲ ማድረግ

 - ማውጣት በኖራ ጭቃ መምረግ መለሰን መቅባት መለቅለቅ ገበሰሰን እይ እለ የርዋ ለአረፍት ረፍት ንተ ገየሩ -(ሕዝ፲፫ -፲፭ ኢሳ፲፮ -፲፩)

ገይብ [1]-(ዐረ ጀይብ) ጀብ ኪስ የጀይብን ፍች ተመልከት

[2]-(ዕብ ጋቢያ ዐረ ጣስ) ኮራ ታላቅ ጽዋ ረዥም እግራም እንደ ጐሽ ዋንጫ በስተላይ ሰፊ ለቃቃ በስተታች ጠባብ ሸልቋቋ ውሃ አንጥፈው ያበባ ችቦ የሚያኖሩበት፤ ወይን ቀድተው የሚጠጡበት። ገይበ ብሩር ዘቦቱ ይሰቲ እግዚእየ። ገይበ ወርቅ ምቅዳሐ ስብሐት -(ዘፍ፵፬ - - አርጋ) ባለብሉዮች ግን አንኮላ ክና ቦሬ ሽልም ባያ ካቦ ይሉታል

(ጥይ)        ገይድ -(ዳን) ቅጽል። ብርቱ ጮሌ ፈጣ ፈርጣጭ። ፈረስ ገይድ ርክ ወገይዳን እንተ ወይጠል -(ሢራ፴፮ -፮። ፩ዜና -፲፪ -)

ገደላ -(ላት) ውዳቂ ሬሳ ጥንብ፤ ገደል ገብ -(ዘፀ፳፩ -፴፬፴፮) ሀሎ ገደላ ህየ ይትጋብኡ አንስርት -(ማቴ፳፬ -፳፰ ሉቃ፲፯ -፴፯)

ገደል -(ዕብ  ጋዶል፤ ዐቢይ) ቁሙ ጸድፍ። -(ተረት) ዛፍና ወፍ፤ ገደልና አፋፍ። በሬ ሆይ በሬ ሆይ ሩን አየኽና ገደሉን ሳታይ

ገዲል ሎት -(ገደለ ይገድል ይግድል ቀተለ ዕብ ጋዳል ዐብየ) መግደል ማቍሰል፤ ማረድ መቅተል ማነቅ ገደል መጣል። ፈነወ ሐጾ ወነደፎ ዔሳው እኍሁ ወገደሎ ወገደሎ ዳቤላ ጠሊ -(ኩፉ -፴፰። ዳን፰ -) በጠብሐ ፈንታ ገደለ ይላል ወገደለ ንጉሥ እምጥሪተ ዚኣሁ ወመላእክትኒ ገደሉ ሕዝብ እገድላ ዛቲ ርሆ ተዝካረ ቡየ -(፪ዜና -፴፭ -፯። ገድ -ተክ -ታም)

ገዲም ሞት -(ገደመ ይገድም ይግድም። ዕብ ጋዳም ገዘመ) መጋደም፤ መተኛት። -(ጥደ) መገደም መደበር መከለል ዳሩ እሳት ማኽሉ ገነት ይኹን ማለት። መነየነ ተመልከት የዚህ ጎር ነው

ገዲው ዎት -(ገደወ ይገዱ ይግዱ) መስጦት ማቅረብ ማስረከብ። መጋዳት መከልከል

ገዲድ ዶት -(ገደ ገደደ ይገድድ ይግድድ ዕብ ጋዳድ። ዐረ ጀደ) -(ጥገ) መገደድ በግድ መያዝ ማስገደድ ግድ ማለት የዳኛ የባለዳ። መወንበድ መሸፈት መጨከን የሰራዊት መባስ መታደስ፤ ማገርሸት የደዌ የክፋት መግደድ ማግደድ መወላገድ ጥመም መጣመም የመልክ የጠባይ ኹሉም የክፉ ነው።

ገዲፍ ፎት -(ገደፈ ይገድፍ ይግድፍ ዐረ ጀደፈ ጋዴፍ ሰደበ አረከሰ) መግደፍ፤ መጣል መተው፤ መርሳት፤ ማጥፋት፤ የጣፊ የተማሪ ለጧሚም ይኾናል ገዳፍ ዘኢያገድፍ እንዲሉ። መወርወር ማሽቀንጠር፤ ጥሎ መኼድ የጕድፍ የሸክም የመሰለው ኹሉ ደፈቶ ሕፃን ታሕተ ዕፅ ንግድፎ ውስተ ይግድፉ ውሉዶሙ ውስተ ፈለግ ግድፋ ውስተ ምድር ስተዋፅጽ ወገደፉ ውስተ ባሕር ንዋዮሙ -(ዘፍ፳፩ -፲፭ ፴፯ - ኩፋ -፵፯። ዘፀ፬ -፫። ዮና፩ -)

ገዳሊ -(ሊት ልያን ያት) የሚገድል ገዳይ ራጅ፤ ገደል ዳጅ።

ገዳሚ -(ሚት ምያን ያት) የሚጋደም ተጋዳሚ ጋድም። ገዳሚ ደባሪ፤ ገዳም ሠሪ።

ገዳማዊ -የገዳም በረኸኛ ዐዳኝ መነኵሴ ባሕታዊ

ገዳም -(ማት ዕብ ሚቅላጥ) ቁሙ ምኔት ደብር የመነኮሳት ሰፈር ታላቅ ቤተ ክሲያን በደለኛ ሸሽቶ የሚጠጋበት ደውሎ የሚማጠንበት ደብረ ምስካይ -(ኢያ፳ -) ዱር ወማ በረሓ ምድረ በዳ ከሀገር መንደር የራቀ የአራዊት ክፍል ውስተ ገዳም ዐቢይ።አራዊተ ገዳም ገዳም ውእቱ ብሔር ገዳማት ወአድባራት ቦአ ውስተ ውሳጤ ገዳማተ ድው -(ዮዲ፩ -፭። ፍ፪ - ማቴ፲፬ -፲፭ ስንክ -ጥር፳፪ የካ፲፭)

ገዳፊ -(ፊት ፍያን ያት) ቁሙ የሚገድፍ የሚጥልመናኒ ገዳፍያነ ዓለም -(ፊልክ -)

(ላት)         ገድል -ቁሙ፤ ትግል ፈተና ውጊያ ሰልፍ ድልና አክሊል እስኪገኝ ድረስ የሚደክሙት ድካም የሚሠመሩት ሥራ የሚቀበሉት መከራ ገድለ መዊእ ድል ጽኑዕ ነበ በዝንቱ ድል ሠለስተ ዓመተ እለ ጋደሉ ሠናየ ድለ ወሞቱ እንተ ክርስቶስ። ዕሴተ ገድላቲሆሙ ወድካማቲሆሙ ሰማዕታት ገድላቲሆሙ ተጽሕፈ ለነ ትመሀር ሃይማኖቶሙ ድላቲሆሙ ቅዱሳን -(ጥበ፬ -፪። -፲፪። ገድ -ተክ ዲድ -፳፭ - - -፪። መዋሥ አፈ -ድ፳፰)

 -መንፈሳዊ  ዜና ወግ ሪክ የቅዱሳንን መከራና ጸጋ ተጋድሏቸውን የሚናገር መጽሐፍ ገድለ አዳም ገድለ አብርሃም ገድለ ሐዋርያት የመሰለው ኹሉ

ገድገደ -(ገዲድ ገደ ገዘ) ቁሙ ገደገደ አቆመ አጸና ተከለ የይሎ የድንኳን።

ገድገድ -ግድግዳ ቅጥር የድንኳን ካስማ አውታር፤ የሸማ ጥር በዐውደ ገድገደ ቤቱ በዐጸደ ድገዱኒ ለደብተራ -(መቃ -ገ፩ ፲፰) አንገደገደ ተንገደገደ፤ ገድጋዳ ማለት ዚህ ወጥቷል።

ገግጾ ጾት -(ገገጸ ይጌግጽ ይገግጽ) መገገጽ ተግ ማለት መቆም መገታት፤ ማፈግፈግ ማሸግሸግ ወደ ኋላ ማለት ፍሮ ፈርቶ ደንግጦ። ይጌግጽ እመዋቲ ይጌግጽ እምገጾሙ ኢይጌግጽ እምጸብእ ወቀትል ገገጹ እምንጻሬ ምት እንዘ ይጌግጹ። ሰላም ለአዕይንቲከ እለ ገገጻ እምርእይ -(ኢዮ፴፪ -፴፩። ፴፬ -፲፱። ዮሴፍ አፈ -ድ፬ ሄርማ ደራሲ) ገጽን ተመልከት የዚህ ዘር ነው

ገጸወ -(ይጌጹ ይገጹ። ተቀ ) ታየ ተገለጠ ጐላ ተረዳ ፊት ለፊት ኾነ ተነጻጸረ መጽሐፍ ግን በገጸወ ፈንታ ተገጸወ ይላል፤ አያሰኝም ዛቲ ጢአት ትትጌጾ ብዙኅ ጾታ ገጻት እን ይትጌጾ በትእምርተ መስቀል -( - - -፩። መጽ -ምስ)

ገጽ -(ጻት ገገጸ። ሱር ሐዛእ። ዕብ ሓዛህ ሙል) በቁሙ፤ ፊት ግንባር ይንና አፍንጫ አፍ ያሉበት ካንገት በላይ እስከ ራስ ጠጕ ወደ ታችም እስከግር ጥፍር በስተፊት ያለው ክፍል። ፊት ለፊት የሚታይ፤ በፊት አንጻር ያለ ይን የሚያርፍበት ማዩም ምድሩም ማናቸውም ኹሉ ይከድኑ ገጾሙ ሰዐረ ንብዐ ምኵሉ ገጽ ደነኒ ፍረት ገጽየ ከመ ስሕቶ በገጽየ ገጸ ሰማያት ተአምሩ። አስተፍሥሕ ምድር -(ኢሳ፮ -፪። ፳፭ -፰። መዝ -፵፫። ዮዲ፲፫ -፲፮ ማቴ፲፮ -፫። ቅዳ)

 -ድፍረት ቀረቤታ ልነት ግልጥ ገሃድ። ገጽ ብነ እግዚ ከመ ንርክብ ገጸ ወሀበኒ እግዚ ገጸ ወሞገሰዘእንበል ፍረት ትቤሎ በገጽ -(፩ዮሐ - -፳፩ -፳፰ ጦቢ፩ -፲፫ ምሳ፯ -፲፯)

 -አካል ቁመና ቁመት። መድኀኔ ጽየ አሐደ ገጸ ነአምኖ እግዚእነ የሱስ ክርስቶስ። ክልኤቱ ገጻት በበ ካሎሙ -(መዝ -፵፩። ቄር - አፈ -ድ፫)

 -ወገን ማእዝን፤ መንገድ ስልት ተራ ምክንያት የመጽሐፍ አንቀጽ ክፍል ምዕራፍ እምአርባዕቱ ገጹአርባዕቱ ገጸ ምድር ርገ እን ካልእ ገጽ ወሖረ እን ካልእ ንንግር በበ ገጹ በምንትኒ ገጽ ዘኮነ በብዙኅ ገጸ መካን -(ሕዝ -፵፯። አዋል ዮሐ፲ -፩። ገድ -ተክ። ዕብ፱ -፭። - - -፭። አፈ -ድ፲) ገጽ በነገር ኹሉ እየተናበበ ሳይናበብም ወድቆ በሚስማማው ይፈታል ደቂቅ አገባብ ገገጸን ተመልከት

ገፊር ሮት -(ገፈረ ይገፍር ይግፍር) መገፈር መቸፈር ማጋፈር ማጐፈር፤ ገፈራ አጋፋሪ ጐፈሬ ማለት ከዚህ ወጥቷል።

ገፊት ቶት -(ገፈተ ይገፍት ይግፍት) መገፈት ማጋፈት ገፋች አጋፋች ገፈታም መኾን

ገፊዕ ዖት -(ገፍዐ ይገፍዕ ይግፋዕ ዐረ ጀፋ ተቈጣ ሰደበ) መግፋት መገፍተር ለመጣል ለማራቅ። ግፍ መሥራት መጭቈን ማጣበቅ ማስጠበብ ማስጨነቅ መበደል መቀማት መንጠቅ መመንጠቅ በኀይል መውሰድ ፍዕዎ ውእቱ ቤት ወኢወድቀ ለሊሁ ይገፍዕ ወለሊሁ ይትመዐዕ ግፍዕ ዘገፋዕክሙ ወእመሂ ዘገፋዕክዎ ፈድዮ ትርብዕተ ሙሴ ጸሊም ፍዓ ለመንግሥት ሰማያት -(ማቴ፯ -፳፭ ራ፲፫ -፫። ሔኖ፺፰ -፰። ሉቃ፲፱ -፰። ስን -ኔ፳፬) ገፍትዐን ተመልከት የዚህ ሯጽ ነው ሯጹም ነው

ገፊፍ ፎት -(ገፈ ይገፍፍ ይግፍፍ) መግፈፍ መገልፈፍ መጋፈፍ -(ዐማርኛ) ኹለተኛም ገፍገፈ አንገፍገፈ ብሎ  ገፈገፈ ንገፈገፈ ተንገፈገፈ ማለት ከዚህ የወጣ ነው

ገፋዒ -(ዒት ያን ያት ) የሚገፋ ግፍ የሚሠራ ገፊ ግፈኛ በዳይ ቀማኛ ብእሲ ገፋዒ አነ ውእቱ ገፋዒ። መኳንንት ገፋዕያን። ኖሎት ገፋዕያነ መርዔቶሙ ኖሎት ፋዕተ ባግዖሙ -(ምሳ፳፱ -፳፯ ፩ዜና -፳፩ -፲፯ ጥበ፮ - ቀሌ ዕር -ኢሳ፫ -፳፬)

ገፍታዒ -(ዒት ዕያን ያት) የሚጥል የሚገለብጥ ገልባጭ ገላባጭ ገለባባጭ ፍታዔ መናብርተ ኀያላን -(መቃ -ገ፲፯)

ገፍትዐ -ገፈተረ፤ ጣለ አራቀ ገለበጠ ደፋ የውስጡን በላይ የላዩን በታች አደረገ አፈረሰ ለወጠ ቀየረ፤ ሌላ አደረገ አጠመመ ቈለመመ። ትገፈትዕዎ ሕዝብ ምግብሩ -(አራቀ) እገፈትዕ መናብርተ ነገሥት ወእገፈትዕ ሠረገላተ ወመስተጽዕናነ ፍትዖሙ ለአድባር መሠረቶሙ ፍታዕኩ ዋዮ ፍኣ ጣለ -(ሐጌ፪ -፳፪ ኢዮ፳፰ -፱። ሐ፲፫ -) አንተኑ ዘትገፈትዖሙ ለእስራኤል ፍትወት ፍትዐ ልበከ እለ ትገፈትዕዋ ርትዕ ይገፍትዕ ፍትሐ ምስኪን ለወጠ -(፫ነገ -፲፰ -፲፯ ዳን፩ -፶፮። ሚክ፫ -፱። ኢሳ፴፪ -)

ጉማ [1]-ታላቅ ኸት ህና ተመማ የብዙ ዜማ ብርኤል ዘራማ ዕራጌ ስብሐት ጉማ ጉማ ቃሎሙ ሐዋዝ ወጥዑም ይመል ቤተ በየ ጉማ ቃሎሙ -(ደራሲ ራ፵፯ -፱። -፲፰) በቁሙ የነፍስ ዋጋ ያውም የቀንድ ከብ የገዳይ ወገን ቀንበር ተሸክሞ እግዚኦ እያለ ለሟች ወገን የሚሰጠው ካሳ መገመ ግምጋሚ ማለት ጉማ የወጣ ቃል ነው ርኅራኄና ለውጥ ያሳያል።

 [2]-ድምፅ ዜማ፤የነፍስ ዋጋ፤ገዪም ጌመ።

ጉማዕ -(ዓት) በቁሙ ጉማ ሙዳ የሥጋ ራጭ ታናሽ ክፍል፤ ለብቻው ጉም ያለ

ጉምጉማ -(ትግ ሐባ) ርኩም አፈ ረዥም ክንፈ ውዥምዥም ድምጡ እንደ በሮ የሚተም እንደ ነጋሪት የሚጐሰም እንደ ማይ የሚያስገመገም

ጉር ጎር -(ዕብራ) ያንበሳ ግልገል የዥብ የተኵላ የውሻ ቡችላ የናቱን ጡት አጥብቆ የሚመጥ የሚመጠምጥ

ጉቡእ እስትጉቡአ -(ኣን ኣት ብእት) የተያዘ የተሰበሰበ ብስብ ክምቹ። ቅምም ጥርቅም። ጉቡእ በእድ። ኵሉ እስራኤል ምስሌሁ ጉቡኣን እለ ጉቡኣን ውስተ የሩሳሴም -(ምሳ፲፩ -፬። ፩ዜና - -፰። ፲፪ -) እስትጉቡእ ዝንቱ መጽሐፍ እመጻሕፍት ምላካውያት ወቀኖናት ወእምዝ ትለወ በዝንቱ ተግሣጽ እስትጉቡእ። ወዝንቱ ውእቱ ዘእስትጉቡእ ለኵሉ -( - -መቅ። አፈ -ድ፴፫ ተ፴፬) በእስትጉቡእ ፈንታ ምስትጉቡእ ይላል ስሕተት ነው ምስትጉቡኣት አእላፍ እምነ መላእክት -(አፈ -ድ፴፪)

ጉባኤ -(እያት) መሰብስብ -(ጥሰ) መሰብሰብ አሰባሰብ ስብሰባ እከባ ንድነት መስብሰቢያ -(ጥሰ) መሰብስቢያ፤ መሰባሰቢያ መገናኛ ጊዜ ቦታ ገበያ ሸንጎ አደባባይ ገዳም ቤተ ክሲያን የትምርትና የሰርግ  የልቅሶ ቤት የመሰለው ኹሉ ወይም በቁሙ የተሰበሰበው ማኅበር እንግልጋ፤ ገበያተኛ የሰው መንጋ በጉባኤከ ጉባኤ ቀኖናት በመካነ ጉባእያት ዘከመ መራሕበት ወምሥያጣት -(ዘፀ፳፫ ፲፮ - - - - -) ተጋበኡ ዕሌሆሙ እምሮም ጉባኤ ብዙኅ። ጉባኤ ፀርየ ዝሩ ባኤ ሐራ። ጉባኤ ኤጲስዎጶሳት። ጸሐፈ መጽሐፈ ጉባኤ። ቤተ ክርስቲያን እንተ ዕለ ኵሉ ጉባኤ ዘሐዋርያት ብዙ ሰው -(ዮሴፍ። ስንነክ -ነሐ፲፪ አርጋ ቀኖ -ኒቅ ቅዳ)

ጉባኤ ቃና -የቅኔ ስም መዠመሪያ ቅኔ ባለ፪ ቤት። የስሙ ንባብና ምስጢር ወንጌል መጥቷል -(ዮሐ፪ -፲፩)

ጉንባሕ -(ዐረ ጁንቡሕ ወፍራም ረዥም) ንባ እያለ የሚመጮኽ ላቅ አሞራ ርኩም፤ ወይም የርኩም ዐይነት ሌላ ጉንባሕ። አበ ጉንባሕ ጉንባሕ፤ የጩኸት ባለቤት -(ፈላስ -ገ፲፯ ዘዳ፲፬ -፲፰)።ትግሮች ግን አባ ጉንባሕ ማለት ጐንባሳ ማለት ነው ይላሉ አብ አባ ካልተጨመረ ጉንባሕ ብቻ ርኩምነቱን አያሳይም ማእከላይ ስም ነው። ስምነቱም ገነበና ነብሐ ኹለቱ ሥር የወጣ ነው ነብሐን እይ

ጉጋ ጕጋ -ጕጕት፤ የጕጕት ይነት ሞራ ባለብሉዮች ንጫ ይሉታል -(መዝ -፻፩ ሌ፲፩ -፲፯ ዘዳ፲፬ -፲፯) ቆቃሕ በማለት ፈንታ ጉጋ ይላል ሕተት -(፩ነገ -፳፮ -)

ጕሀን ጉሃን -ስዋሬ ውር ድብቅ ስወራ ድበቃ ርቆሽ ወሀብዎ በዓላተ በጕሃን ወመሥዋዕተ በምስጢር -(ጥበ፲፬ -፲፭)

ጕሑቍ -(ቋን ቋት ሕቍት) የጐበጠ ጐባጣ፤ ቀላሳ ተርካሳ

ሒል ሎት -(ጕሕለ አው ጐሐለ ይጕሕል ይጕሐልዐረ ጀሐለ ጋሓል ጋለ ጋመ) ማፍረስ መጣስ ማቃጠል መተኰስ የሕግ የቅጥር የቤት መስረቅ መቀማት፤ መውረር መዝረፍ

ጕሒቍ ቆት -(ጕሕቈ ይጕሕቍ ይጕሐቍ ዐረ ጀኃ) መጕበጥ መጐንበስ መጽነን እንደ ደጋን መኾን፤ በደዌ በርግና -(ሉቃ፲፫ -፲፩) መካን ዘጕሕቈ ወምተ ማሕፀና ዕቤራይት ዘጕሕቈት ምአብዙኆ ውሉድ -(አፈ -ድ፳፭ መጽ -ምስ)

ሂን ኖት -(ጕህነ አው ጐሀነ ይጕህን ይጕሀን) መሰወር መደበቅ። መጮኽ ማዜም ማጕረምረም። ገንሐንና ገነየን ተመልከት የዚህ ጎር ናቸው። መጓን ማጓን ወደ ላይ -(ዐማርኛ)

ጕሕላዌ -ሕሉት መታለል ማታለል አታላይነት። ሽንገላ ልብለባ፤ ክዳት ተንኰል ሰይጣናዊ ባህል። ልማደ ራዊት ሕላዌ ወገብረ ዮአብ ዘንተ ሕሉተክዒወ ደመ ሰብ በጕሕሉት። ወጕሕሉት ቃለ ፉሆሙ። ሕሉት ወጽልሑት -(ቅኔ። ፪ነገ -፲፬ - ቀሌ ኤር፱ -፰። ማር፯ -፳፪)

ጕሕልው  -(ዋን ዋት ሉት) የተታለለ የተሸነገለ፤ ሽንግል ድልል፤ ሌሎች ያታለሉት የሸነገሉት።

ጕሕቈት መጕበጥ አጐባበጥ ጐባጥነት ብጠት

ጕህና -ጕህና በቁሙ ዐቢይ ዜማ ስልት ያለው ጩኸት ጉማ ተመማ ወፍራም ድምጥ ዝማሬ ዘበልሳን ወጣዕመ ቃል ዘበጕህና ወሕንጸቱሂ ይእቲ ዘታቀርበነ ግዚ በአእኵቶ ማሕሌቱ ውስቴታ በዘይደምፅ ህና ቤነ -(አረጋ -ድ፯ ዮሴፍ)

ህን -(ናት) ኅቡእ ነገር ረቂቅ ምስጢር በትምርትና በብቃት የሚገኝ። ጳውሎስ ዘበኵሉ ጠቢብ መጋቤ ህናቱ ለክርስቶ -(ቄር -) ኅቡኣቲሁ ምስጢራቲሁ ማለት ነው አንዳንድ መጽሐፍ ህነት ይላል አያሰኝም።

ጕሉሕ ጕልሕ -ቁሙ የጐላ የተገለጠ ግልጥ፤ ፈጽሞ የሚታይ የሚሰማ።

ጕላ አው ጕሌ -( ጐላል ዐረ ወዕብ ጉሎት። ጽር ጉላት) አፍላል፤ መንቀል የሸክላ ቅል ልላት የመንቀል ዐይነት ወገብረ ልኤተ ዕማደ  ወመልልቴሆሙ ጕላ -(፪ዜና - -፲፪) አንዳንድ መጣፍ ጎላት ብሎ በሳብዕ ይጥፋል።

ጕልሓዊ -(ትግ ልሓይ ዕብ ጋሉሕ) ልጩ፤ ንጩ፤ራሱን ጽሕሙን ፍረቱን የላጨ የነጨ መላጣ ቡሓ ጐዳ ራሰ በዳ -(ተረት) የሴት ላጪ የወንድ ነጪ

ጕልማ -(ዐማርኛ) ቁሙ አባት ለልጁ ጌታ ላሽከ የሚሰጠው መሬት ግዛት። -(ግጥም ተጠማኝ። ወይም ተጋዥ) አይኾንም እንጂ ኾነማ መጋዞ ይሻላል ልማ

ጕልበት -በቁሙ፤ ብርክ ኀይል ብርታት ጥንካሬ -(ግጥም ደጃዝማቾች ዋጉ ትቢተኛው ድል ስለ ኾነ) አላዋቂ ሰፊ ሱሪ አሳጥሮበት የደጃች እገሌ ልበቱ ታየበት።

ጕልት -(ታት) ጕልቻ። በቁሙ ዲስ ርስት ሰው በፈቃዱ ለዘመድ ለባዕድ ወይም ለገዳም የሚያወርሰው፤ ገንዘብ ጥሪት መሬት። ንሕነ ጐለትነ ልተ ገበዘ አኵስም ብፅዓታት ወጕልታት -(ክብ -ነገ። - -፲፰)

 -የማይፈልስ ቀለም ገቢር ተገብሮ የሚከት የማይለወጥ ስብዑ ዮም ትማልም አፉሁ እዴሁ የመሰለው ኹሉ።

ጕሎ - ዕፅ ፍሬው ዘይት የሚኾን ቅባታም ሐኪሞች ለሆድ መፈወሻ በዞች ለምጣድ ማሠሻ ፋቆች ለቈርበት ማራሻ ለማለስለሻ የሚሹት ንጨቱ ግብዝ ውስጠ ክፍት። -(ተረት) የጕሎ ዘንግ የባሪያ ደግ

ጕመሮ ገመሮ -የቈላ ዕንጨት ረጋም እሾኻም የቀንጠፋ ወንድም ወንዴና ሴቴ ያለው።

ጕማሪ ጐማሪ -በቁሙ፤ የባሕር አውሬ ምር ተጐማሪ -( -)

ጕሥዐት -ማግሣት፤ መናገር፤ አገሣሥ ነጋገር፤ ግሣት ትፋት ቅርሻት፤ ልብ ወለድ ፈጠራ ነገር ከመ ሥዐተ ልቦሙ ይትናገሩ። ሥዐተ ኅሊና ሰይጣናዊ ፈላስፋ ተቶስሐ ልቦሙ በሃይማኖት ወኢበርሁ በብርሃነ ዚኣሃ አላ ይትአመኑ በጕሥዐተ ቦሙ ይሜህሩ ፈጠራ ዘእምጕሥዐተ ልቦሙ -(ዕር -ኢሳ፫ -፳፩ ቄር -ገ፫ -ድ፳፪ መጽ -ምስ)

ጕርን -(ዕብ ጎሬን። ዐረ ጁርን) ምክያድ፤ ዐውድማ የበሬ የገበሬ ሸንጎ አዝመራ መከር ታጭዶ ተሰብስቦ የሚወቃበት የሚበራይበት ተመሽኖ -(ንሽቶ) የሚመረትበት ጕርነ ኦርና። ርና የሰው ስም -(፩ዜና -፳፩ -፲፭ -፲፰ -፳፩ ፪ዜና - -)

ጕርዑይ -(ያን ያት ዒት) የታነቀ የተሰረነቀ ታን የሞተ

ጕርዒት -ዕንቂት ዕንቂያ፤ ጕረሮ አያያዝ አስተናንቅ፤ የማነቅና የመቃነቅ ሥራ

ጕርዔ -( ጐራዒት ዕብ ጋሮን) ዐንገት ማንቍርት ረሮ የሆድ ደጃፍ ውስጠ ፍት መዋጫ መሰልቀጫ ማግቢያ ማውጫ መጮኺያ፤ የዜማ የንባብ የምግብ ጣዕም የሚታወቅበት መተረ ርዔ ጥዑም ለጕርዔየ።ጕርዔ ይፈልጦ ለኵሉ ጣዕመ ክል። ጕርዔየ ይነብብ። ትክሉ ቢበ በጕርዔክሙ መቃብር ክሡት ጐራዒቶሙ -(ስንክ -ጥቅ፮ መዝ -፻፲፰ -፳፮ -፳፬ ኢዮ፮ -፴። ሌ። ሮሜ፫ -፲፫)

ጕርዔያዊ - ቀባጣሪ ሆዳም ኹሉን ውጨው የሚል

()          ጊኑይ -ገናዊ ጋኔናም፤ ኔን ያደረበት እብድ -(፩ነገ -፳፩ -፲፬) ገነወን እይ

ጕኑድ -(ዳን ዳት ንድ) የጐነደ ንድ የኾነ የደነደነ። ብዳን ወጕኑዳነ ልብ -(መጽ -ምስ)

ጕንደ ማኅፈድ -የግንብ ምድ ልፎ ዐልፎ የቆመ፤ ወይም ወገቡ መካከሉ -(ሄርማ)

ጕንደ ማእሰር -እግር ግንድ -(ግብ፲፮ -፳፬)

ጕንደ ዳዊት -ወገን የትውልድ ሥር -(አርጋ -)

ጕንዱየ -ይቶ ሰንብቶ ዝግሞ ዝግ ብሎ መጽአ ጕንዱየ ሖረ ጕንዱየ

ጕንዱይ -(ያን ያት ዲት) የቈየ ዘገየ የሰነበተ የኖረ ያለ ዳተኛ ዝግተኛ። ንዱይ ነቢብ ጕንዱይ መዐት ጕንዱየ መዐት ንዱያነ ልብ -(ያዕ፩ -፲፱ ነሐ፱ -፲፯ ሉቃ፳፬ -፳፭) ብዙ እጅግ ዐያሌ። ሕየው ጕንዱየ ዓመተ ምጕንዱይ ዕለት። በጕንዱይ መዋዕል እምድኅረ ንዱይ መዋዕል -(ኢዮ፳፱ -፲፰ ሮሜ፲፭ -፳፫ ኢሳ፴ -፳፯ ኤር፲፫ -)

ጕንዳን -ቁሙ ዝግተኛ፤ ታናሽ ጥቍር ንኳሽ ተናካሽ ተቈናጣጭ

ጕንድ -(ዳት አጕናድ) ቁሙ ግንድ በሥርውና በዐጽቅ መካከል ያለ ሥሩም ይቀር ወፍራም ደንዳና የኖረ የቈየ፤ የዘገየ ዕንጨት። ሥርዎ ወጕንዶ ጕንደ ወይን ጕንደ ዕፀው ወለለ ሐቲ ንድ በበ ሠላሳ ወአሐዱ ልፍ ዕጹቂሃ ጕንዳት። አጕናደ በቀልት -(ዮሐ፲፭ -፬። ማቴ፫ -፲። ቀሌ ሔኖ፹፫ -፬። ስንክ -ሚያ፳፫)

 -ሥር መብቀበያ፤ ወገብ አጠገብ ወይና ደጋ ዘዘ ያውቅዩ ልሳና አምጕንዱ እምጕንደ ደብር ሰርዎ ጕን ደብር -(ስንክ -መስ፭ ጥቅ፲፰ ዮዲ፯ -፲፪። -፲፫)

ጕንዶ -(ዐማርኛ) ታላቅ የማር መስፈሪያ ፲፮ ነጥር የሚይዝ ጕንዶ ማር እሰጥ እንዲሉ

ጕንፋ -(ትግሬ) በቁሙ ንፋን ገር በሽታ፤ ክርፋትና ከትንፋገን ክፋ ሽታ የሚመጣ

ጕዕ -( ዓት ቆዕ) ጓሚያ ቃሪያ እንጭጭ ያልበሰለ ድብድብ የጥጥ ያበባ እንቡጥ

ጕዕቱይ -(ያን ያት ቲት) የተሞኘ የተታለለ ፍጻሜው ከንቱ የኾነ ዕቱይ ወለድከ ዕራቀከ ወትቀውም በከሃ ዕራቀከ -(ግንዘ)

ጕዕትያ -(ጽር ጎዒቲያ) ሟርት ጥንቈላ የጥንቈላ ሥራ ጋኔን ጥራት ምትሀት ማሳየት ማታለል መሸንገል ማሞኘት፤ ከንቱ ነገር ትግል ትግያ ንንቅ፤ ጣር ድካም ልፋት የጕልበት ሥራ በከ ሰርሐ በሥራያቲሁ ወበብዝኀ ዕትያሁ ስብሐቶሙ ኮነ ስብሐተ ዝንቱ ዓለም በጕዕትያ እለ ይገብሩ -(ቀሌ) ወእምድኅረ ብዙኅ ዕትያ በሀፍ በጕዕትያ ወጻማ በፈቃደ እግ ተውህበ ኵሉ መንግሥተ ዓለም ዘርዐ ሴም፤ ወግብርናት ለዘርዐ ካም ወጕዕትያ ዘርዐ ያፌት -(ፊልክ -፲፬ መቃ -ገ፲፩። -ነገ፸፫)

ጕዛ -(ዕብ ጋዝ፤ ጋስ) ነጣቂ ወፍ አሞራ፤ ጭላት የጭላት ይነት -(ዘሌ፲፭ -፲፮ ዘዳ፲፬ -፲፯) በንስር ፈንታ ጕዛ ይላል ስሕተት ነው ከመ ክን -(ዘፀ፲፱ -)

ጕየት -መሸሽ መኰብለል ሽሽት ብለላ ስደት፤ ሩጫ ፍርጠጣ። ይጼዕሉ የቶ እል የአምሩ ትስብእቶ ነጽር ጕየተ ሕፃን አጕየዮ ለዲያብሎስ -(ተረ -ቄር፲)

ጕዩይ -(ያን ያት ይይት) የሸሸ ራቀ የኰበለለ። ተረክቡ ጕዩያነ ምሥርዐተ መላእክት -(አዋል)

ጕያ [1]- ዝኒ ማሁ ሽሽ ስደት ብለላ -(ማቴ፳፬ -፳። ኢሳ፶፪ -፲፪) ይከውን ዐቢ ምንዳቤ ወጕያ ወክዕወተ በሰንበት ይኩን ያክሙ ያከ ምቤት ልሔም ደብረ ስቋም -(ኪዳ። ድጓ። አዋል)

[2]-ጕያ፤ ቁሙ የጭንና የጭን መካከል ሕፃን መሸሻ መደበቂያ። የናት እንዲሉ።

ጕዱዕ -(ዓን ዓት ድዕት) የተጐዳ የተነካ ንክ፤ ባራ ሻዋ ኰሳሳ።

ጕድለት -በቁሙ መጕደል አጐዳደል ጐደሎነት። በጕድለት ፈንታ ጐደሎ ይላል፤ አያሰኝም አቡነ ምሉ ዘአልቦ ደሎ -(ገድ )

ጕድባ -ቁሙ የታረደ የተቈረጠ ዕርድ ምሽግ ማንኵት ፈፋ፤ ውሃ የበላው መሬት።

ጕድብ -(ባት። ዕብ ጋርዜን ቃርዱም ዐረ ፋስ) ምግዛም፤ ገዠሞ የብረት መሣሪያ፤ መጥረቢያ ምሣር። ኹለት አፍ ብረት ምሣርና ማ፤ የሚቈርጥና የሚቈፍር እጀታው አንድ ምላሱ ጥንድ በኹለት ወገን የሚሠራ -(ዘዳ፲፱ -፭። መሳ፱ -፲፰ ፩ነገ -፲፫ - ኢሳ፲ -፲፭ መዝ ፸፫። ሉቃ፫ -፱። ሕዝ፱ -) ከመ ምሣር ዘይሤጽር ወከመ ድብ ዘይሰብር -(ዲድ -፲። አዋል)

ጕድዐት -መጕዳት መጐዳት አጐዳድ አነካክ ዳት ንኪት ብራት

ጕድፍ -(ፋት) በቁሙ፤ ጥራጊ ውዳቂ ዝብል ተጠርጎ የሚጣል ከመ ኵሉ ይኩስትር ቤቶ መሬተ ድፈ ይገር ውስተ መቃብሪሁ። ወኮነ ወግረ ዐቢየ ድፍ -(ስንክ -መስ፲፯ መጋ፲)

ጕጉእ -(ኣን ኣት እት) የጓጓ የቸኰለ ችኵልፈጣን ቀልጣፋ ትጉ አፍ ጕጉእ ሰማዕት ጉእ። ጉእ በከናፍሪሁ። እመ ርኢከ ብእሴ ጕጉአ በቃል -(ምሳ -፲፬። ፲፪ -፲፱ ፲፫ -፫። ፳፱ -)

ጕጕኣ -ችኰላ ጥድፊያ ቅልጠፋ ትጋት ጥረት ድንጋፄ ፈነዎሙ በብዙኅ ጕጕኣ። ኀለ በጕጕኣ ጕጕኣ ቢረክሙ። ቃል ወሁከት ወነጐድጓድ ወድልቅልቅ ወጕጕኣ ዕለ ምድር -(ጥበ፲፱ - መዝ -፸፯ ጴጥ - -፭። አስቴ፩ -፲፪ ሔኖ፴፱ -)

ጕጓኤ -መጓጓት፤ ጕጕት። መቸኰል አቸኳኰል ችኰላ ችኵልነት -(ዮሴፍ) በጕጓኤ ፈንታ ጕጕአ ይላል አያሰኝም። አምብዝኀ ጕጕአ -(ስንክ -ጥር፲፮)

ጕጠት -(ታት) (ታት) በቁሙ፤ መቈንጠጫ ጥብቆ ጣብቆ መያዣ፤ እንደ መቀስ ጣት ያለው ፍሕም ዘነሥአ በጕጠት። መጠዋ በጕጠተ ሳት ምሥጋሁ ወደሙ ለክርስቶስ ወደዩ ፍሓመ አሳት ዲበ ደዊሁ ወአኀዝዎ በጕጠት ብዙኀ ዜ። ወጕጠታቲሃ -(ኢሳ፮ -፮። ንክ -ነሐ፲፭ ታኅ፳፬ ዘኍ፬ -)

 -ሹካ ሜንጦ መኈሥሥ የሥጋ ማውጫ የወጣውን እየወጉ ማንሻ፤ እንደ መንሽ - -ጣት ያለው። ጕጠት  ዘሠላስ ተማት ጠታተ ሥጋ -(ፊልክ -፭። ፩ዜና -፳፰ -፲፯ ፪ዜና - -፲፩)

ጕጽፋር -(ራት) ዕከክ ፎከት፤ ደረመን ፈረሳቤት፤ የጥፍር ንኪት

ጊሜ [1]-(ዐረ ዐይም ሱር ዓይማ) ጉም ብዙ ደመና ምድር ወርዶ ተራራ ረብታ የሚሸፍን ወዠድ ለወዠድ የሚጐተት የቀን ጨለማ ከመ ደንክዋ ምድር ወረሰየ ደመና ልብሳ ወበጊሜ ብለላ ወከደነ ርእሰ ደብር በጊሜ ጠብለላ። -(ሢራ፵፬ -፫። ኢዮ፴፰ -፱። ውዳ -ማር፫)

 -ብትነ በረዶ ውርጭ ጠል ካፊያ በረድ ወጊሜ ይዘርዎ ለጊ መድ ውስተ ፀምር።ወፈውሰ ኵሉ ፍጡነ -(ዳን -፵፱ መዝ -፻፵፯ ዘዳ፴፪ - ሢራ፵፫ -፳፪)

 [2]-ጉምገዪም ጌመ።

ጊሠት -መገሥገሥ፤ አገሣገሥ ገሥጋሽነት ግሥገሣ ማለዳ

ጊር -(ዕብራ ዐረ ጀይር) ዲስ ትኩስ ኖራ ውሃ ያልነካው እሳቱ ያልጠፋ ያልበረደ

ጊዛን -የዕቃ ቤትጋዛ

ጊዜ [1]-( ጊዝያት) በቁሙ የተለየ የተወሰነ ሰዓት ዕለት ወርኅ ዓመት ዘመን ዕድሜ ሰው እስኪሞት እስኪሻር የሚኖርበት፤ የሚያርፍበት የሚሠራበት ሌትና መዓልት፤ ፳፬ -ሰዓት። -(ሙሾ ያጤ ዘመን ስለ በዛ) እስኪ ቀደም ብለኽ ጥቂት እኽል ቅመስ፤ ያልቅ የለሞይ ያንተ ጊዜ  እስኪደርስ ለኵሉ። በጊዜ ምጊዝያት ዝያቲሆሙ ለአውራኅ፤ በኵሉ -(መክ፫ -፱። ዮሴፍ። ኩፋ -፳፱)

[2]-ዐቢይና ደቂቅ አገባብ ቅጽል ይኾናል፤ አመና ሶበ ዓትና ዕለት በሚገቡበት እየገባ ጊዜነቱን ሳይለቅ ይፈታል። ዐቢይ ሲኾን በኀላፊ ሖረ ቅጽል ሲኾን በትንቢት ይመጽእ ደቂቅ  ኾን በጥሬ ቀትል እያለ ይገባል፤ አመንና ሶበን ተመልከት።

ጊደር -(ዐማርኛ) በቁሙ ያልሸረፈችና ያልተጠቃች ዕጐልት

ጊጉይ -(ያን ያት ጊት) የሳተ ስሑት ላዋቂ፤ በደለኛ ኃጥእ። ብእሲ አብድ ወጊጉይ ጉይ ውእቱ። ምስለ ጉያን ተኈለቈ -(ሢራ ፲፮ -፳፫ ፲፱ - ቅዳ -ዮሐ)

ጊጳ -(ጽር ጊፓ ትግ ጋብ) የጥንብ አሞራ -(ዘሌ፲፩ -፲፬ ዘዳ፲፬ ፲፪)

-እን -ሲጨመርበት -(እንጋ -እንጃ) ደቂቅ አገባብ ይኾናል

ጋህረተ -ተጋሀጊር ሀገረ፤ ሀግረተ

ጋሕር -(ትግ ገሕር። ዕብ ጊሖር ፍጹም ቀይ) ፍሕም ፍም የእሳት ምርት የበሰለ ንጨት፤ ብስል በርበሬ የሚመስል።

ጋሕፍ -(ትግ ጋሕፎ) የባሕር ዔሊ ደንጊያ ልብሱ

ጋሌ -(ጽር ጋሊ። ሔሌድ) ፋሮ ፋደት መጠማጥ የዱር ድመት ሸላ ሙጭሙጭላ የሚያድን የሚበላ መሬት የሚፍር የሚቈፍር ታናሽ ክፉ አውሬ ዐይነቱና ስሙ ብዙ ነው፤ ባለብሉዮች ግን አፍ ያለው እባብ ይሉታል -(ዘሌ፲፩ -)

ጋልሙት -(ዕብ ጋልሙድ) ዛዛኝ ሴሰ አውሬ የድመት የሙጭሙጭላ ዐይነት በቁሙ ጋለሞታ ባለመሸታ።

()          ጋማ [1]-(ጽርእ ወቅብጥ) ስመ ፊደል ልስ ገ። አልፋ ወቤጣ ወጋማ -(ሥር ጳኵ)

[2]-(ዐማርኛ) በቁሙ የፈረስ የበቅሎ ያህያ ጠጕ ያንገት የማዥራት ጭራ የጋማ ብት እንዲሉ ያንበሳ ጐፈር አንፋሮ በራስ የሚታሰር። ጋሜ የሰው ራስ ወጕር ማኽሉ ተላጭቶ በዙሪያው የሚቀር ብሮ በቀል ጐፈር

ጋሜ -የደጋን ዕንጨት ጥታ ዘለግታ ያለው ለብለቦ ሲያርቁት እንደ ቅን አሽክር የሚታዘዝ -(ግጥም ሽበታም ወይዘሮ የ፰ ዓመት ልጅ) ራሴ ጥጥ ኹኖ ፈታይ ስለምን ልቤ ተነደፈ በጋሜ ደጋን

ጋሜል -(ዕብ ጊሜልዝኒ ማሁ ስመ ፊደል ፍችው ፍጹም ዐሰ ሴት ፍዳ ጋሜል ስዮ ለገብርከ -(መዝ -፻፲፰ -፲፯)

ጋስ አው ጋሶ -ዝንጕርጕር ነጭና ጥቍር ጕሬዝማ የበዳ ህያ ይነት ሽልምልም ወይም ቡሕማ ጋስ ወጸዐዳ ወይወልዳ ሎን ባግዕ ጋሶ ወኵሎ ዘቦ ትእምርት ወኰስኵስ -(ኩፋ -፳፰)

ጋርሣ -(ገዐት ገርህ) የላመ የጣመ ምግብ፤ ገንፎ መንካኮ፤ ወይም ወፍራም ትኩስ ለስላሳ ዳቦ ባለመጣፎች ግን አንባዘ ዓሣ ይሉታል ውስተ መካነ አኀው ድዉያን አልቦ ዘይበልዕ ጋርሣ ወኢዘይሰቲ ወይነ ዘእንበለ ዘይደዊ ጸብኀ ጋርሣ -(ሥር -ጳኵ ሃይ -አበ)

ጋርዜን -(ዕብ) መግረዣ መቍረጫ የብረት መሣሪያ ምላጭ መጥረቢያ ማጤ ምሣር

()          ጋብ -(ዕብራ) ረዥም ቤት ገነት የደርብ ደርብ ዕንቍላል ግንብ። ወያንኅሉ ጋቤኪ -(ሕዝ፲፮ -፴፱)

ጋብኦ ኦት -(ጋብአ ይጋብእ ይጋብእ። ዐረ ጀባእ፤ ተቀበለ ሱር ግባእ) መሰብሰብ ማከብ ማጋበስ ማግበስበስ ማከማቸት፤ መልቀም ማጠራቀም መክተት ማጠፍ መኰርተም፤ የሕዋስ መጽሐፍ ግን በጋብአ ፈንታ አስተጋብአ ይላል በሳተፈና በባረየ ፈንታ ስተሳተፈ አስተባረየ እንዲል። መራዕየከ ስተጋብአ ስተጋብአ ዋየ ብዙኀ ያስተጋበእ ሥርናዮ ውስተ መዝገቡ። ያስተጋብኡ ክነፊሆሙ። ታስተጋብእ እዴከ -(ኩፋ -፴፭።ስንክ -ሠኔ፲፫ ማቴ፫ -፲፪ ሕዝ፩ -፳፬ ምሳ፮ -)

ጋኔናይ -ዝኒ ማሁ ዘጋኔን። እንስሳ ጋኔናዊ ብድ የሚወገሽ ተዋጊ ደንባሪ ጋግርታም ወይም አበ ደደብ -( - -፴፫ -)

ጋኔን -( አጋንንት ዐረ ጂን ጃን ዕብ ሼድ) ቁሙ፤ መንፈስ ርኩስ፤ ዲያብሎስ የዲያብሎስ ጭፍራ ክፉ ካኝ ዕቡይ፤ የሚያሳብድ ባሕር ገደል የሚሰድ ምድር የሚፈጭ የሚያንቈጨቍጭ እሳት የሚጥል የሚያንከባልል፤ የሚያስፈጥጥና የሚያስገጥጥ፤ የሚያንቅ የሚያስጨንቅ፤ እንደንጨት የሚያደርቅ። ምስጢሩ ትቢትና ካኝነት ነው፤ ባለመጣፎች ግን ሩቅ ውዱቅ ጥንብ ሻጋታ ይሉታል -(ማር፱ -፲፯ -፲፰ -፳፪ -፲፫) ጋኔን ኩይ ጋኔነ ቀትር ጋኔን ርኩስ በመልኮሙ ጋንንት ያወፅ ጋንንት -(ጦቢ፫ -፰። መዝ -፺። ራእ፲፰ - ማቴ፱ -፴፬)

ጋን -(ትግሬ) ታላቅ አሞራ ጋን የሚያኽል ልዑለ ቃል -(ራእ፮ -፮። -፲፫)

ጋዕት -ጋት ጥርኝ መጋቻ መለኪያ። ጋት ንድ ይኾናል።

ጋእዝ -(ዛት) ጠብ ክርክር ሙግት ንዝንዝ ድብ ውዝግብ ጭቅጭቅ። ለደም ቀድሞ ወጋእዝጋእዞሙ ስራሕ ለዘይሰምዖ ገረ ጋእዝ ሰይጣን ብአ ፍልጠተ ወጋእዘ ውስተ ቤተ ክርስቲያን መቲረ ጋእዛት -(ሢራ -፳፪ -፳፬ ፳፯ ፲፭ ፩ጢሞ - -፬። ዲድ -፴፪ - -) በቁሙ ጋዝ ንባ ሽታውና ጢሱ እንደ ክፉ ነገር የሚያስቀይም፤ ነፍጥን እይ።

ጋዛ [1]-ጊዛን -(ጽር ጋዛ ጋዚስ ዕብ ኦጻር ዐረ ኀዛኢን) የቃ ቤት ግምጃ ቤት ጐተራ የብዕል የገንዝብ መክተቻ ማድለቢያ መሰብሰቢያ ቤተ መዛግብት። ቤት ዘጋዛ ምቤተ መንግሥትየ ዘጋዛ ለኵሉ ጋዛ ዋየ ቤተ ጊዛን -(ዕዝ፭ -፲፯ - -፳፩ ኢሳ፴፱ -)

[2]-ጋዛ -(ጽር ጋዛ ዕብ ዐዛ) ሀገር የይሁዳ ክፍል ካምስቱ አህጉረ ኢሎፍሊ አንዲቱ የፍልስጥዔም ደቡብ እንደ ዘጌ እንደ ቈራ በባሕር ረፍ ያለች -(ኢያ፲፭ -፵፯ ግብ፰ -፳፮)

ጋይሥ -( አጋይሥ) ዝኒ ማሁ እንግዳ መንገደኛ ዐድሮ ኻያጅ ገሥጋሽ -(ትግሬ)

ጋይሶ -(ጽርእ ኪዶን) ጦር ገር የሚወረወር ዐጭር መጠነኛ። ባለብሉዮች ግን ላማርኛ ስለ ቀረበ ጋሻ ይሉታል ልዕል ዴከ በጋይሶ -(ኢያ፰ -፲፰) ቢዶንን እይ።

ጋይጽ ጌጽ - ሽልማት፤ ልብስ መሣሪያ

ጋይጾ ጾት -(ጋየጸ ይጋይጽ ግእዘ) መንቀፍ መስደብ መገደር መናቅ ማጥቃት ማስጨንቅ ማስቸገር። ማጌጥ መጌጥ፤ መልበስ መሸለም መፀረር ማማር ዚህ የተነሣ መኵራት መታበይ መጽሐፍ ግን በጋየጸ ፈንታ ተጋየጸ ይላል አያሰኝም። እጸልእ ጸላኢከ ወእትጋየጽ ይትጋየጸከ ይትጋየጾ ጎረ ቤቱ -(ዘፀ፳፫ -፳፪ ኢዮ፳ -፳፮) ይቴ ሀለዉ እለ ይትጋየጹ በሥን ወበላሕይ ርቱ ንትዐበይ ወንትጋየጽ በምንትኒ ምግብር -(ግንዘ። አፈ -ተ፪)

ጋዳ [1]-ጋድበቁሙገዲው ገደወ

 [2]-ጋዳ፤ -(ዳት) እጅ መንሻ በረከት መተያያ በፈቃድ የሚሰጥ ገሥተ ሳባ ወዐረብ ጋዳ ያመጽኡ ጸባሕት ወጋዳ ስትዓ ወጋዳ የሀበነ ሰላመ ጋዳ -(መዝ -፸፩። ማቴ፲፯ -፳፭ ሔኖ፶፫ -፩። ድጓ)

ጋድ -ጋድ፤ የሰው ስም ገድ ብዕል በረከት ማለት ነው -(ዘፍ፴ -፲፩)

ጋግ ጋጋ -( ጋጋት ዕብ ጋግ ጠፈር መዋቅር ባጥ) መንቈር ቀንበር ዛንጅር፤ የቅጣትና ያገዛዝ መሣሪያ -(ዘዳ፳፰ -፵፰። ፫ነገ -፲፪ - - - ሢራ፮ -፳፬ ፳፱ ዕን፪ -) ግድፊ ጋጋ እምክሣድኪ አንትሙ እሱራን በሰናስል ወበጋጋ ወበመዋቅሕት ያከብዱ ለነ ጋጋተ ውስተ ክሣውዲነ ዘኢንክል ጸዊሮቶ ወደዩ ርባዕተ ጋጋተ ሐደ ውስተ ክሣዱ ወአሐደ ውስተ ገቦሁ ወአሐደ ውስተ ሐቌ ወአሐደ ውስተ አብራኪሁ(ኢሳ፶፪ ዮሴፍ ቀሌ ስንክ -የካ፲፫)

 -ያንገት ጌጥ ሽልማት ልሻን ማርዳ ድሪ ጋጋ ዘወርቅ -(ስንክ -ጥር፲፮)

-(ጽር ምድር ሀገር ርስት ባለጌ ሐፄጌ እተጌ እንዲሉ። ሐፀየን እይ

ጌልጌል ጌልጌላ -(ዕብ ጋልጌል ጋልጋል) ዝኒ ማሁ መንኰራኵሮች የሠረገላ እግሮች ተሽከርካሮች ተንከባላዮች -(ሕዝ፲ - -፲፫) ባለቅኔዎች ግን ማይ ይሉታል። ደመና ሰማይ ብርህት እንተ ይብልዋ ጌልጌላ -(ደራሲ)

ጌሰ -ገሠገሠገዪሥ ጌሠ።

ጌሠም -(ዕብ ጌሸም ብርቱ ዝናም) ነገ ጧት ማለዳ ርሞ ላመት እስከ ጌሠም ሠመ ጌሠመ ንመውት። አነ ወአንት ጌሠም ትተክዙ ጌሠም እስመ ጌሠምሰ ትኄ ርእሳ -(፩ነገ - -፲፩። ዘፀ፱ -፲፰ ሢራ፲ -፲። ፴፰ -፳፪ ማቴ፮ -፴፬) ጌሠም እንደ ዮምና እንደ ትማልም ልት ነው አይፈልስም መጽሐፍ ግን ጌሠመ ይላል አያሰኝም።

ጌሰም -ነገ ነገታገይሥ ጌሠ ጌሠም።

ጌሴራሴም -(ዕብ ጌእ ሐራሽም) ያናጦችና የጠራቦች የጠቢቦች ቦታ፤ በተራሮች ማኽል ያለ ቈላ፤ ሸለቆ ወንዛወንዝ -(፩ዜና - -፲፬)

ጌራ [1]-( ጌራት) ቦርቦርቲ የራስ ጋሻ ከወፍራም ርበት የሚሠራ ላዩ ብረት ውስጡ ርበት በጦርነት ጊዜ የሚለበስ -(፩ተስ - -፰። ኤፌ፮ -፲፯።ራእ፱ - -፲፯) ጌራ መድኀኒት ጌራተ ኀጺን -(ኢሳ፶፱ -፲፯። ስንክ -ም፲፭) የራስ ጌጥ ሽልማት ራስ ወርቅ ሜትራ ዘውድ አክሊል ፌት ቆብ ባርኔጣ፤ የመሰለው ኹሉ ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ ተቀጸለ ጌራ ዐቢየ ዲበ ርእሱ ሕጺጾ ጌራ ህነት ቅዱስ ወገብሩ ዲበ ርእሱ ጌራ ንጉሥ ወውስተ እዴሁ በትረ ወርቅ ወያአትቱ ጌራቲሆሙ ምርሶሙ -(ደራሲ ዮሴፍ። ሕዝ፳፮ -፲፮)

 [2]-(ዕብ ጌራህ) የገንዘብ ስም ታናሽ ግርሽ የሰቅል ኻያኛ የአቦሊ እኩያ ወሰቅል ዕሥራ ጌራ -(ሕዝ፵፭ -፲፪)

 [3]-ራስ ገየረ

ጌርዮስ -(ጽር ኪርዮስ) እግዚእ እግዚአብሔር -(ቅዳ)

ጌርጌል -መንኰራኵርጌልጌል።

ጌባል -(ጽርእ ዕብ ዔባል) የተራራ ስም የገሪዛን ወንድም ቅርብ አጠገብ፤ የርግማን ቃሎች የሚነገሩበት ከገሪዛን በስተሰሜን ያለ ፀጋማይ ተራራ። ኹለቱም በኤፍሬም ዕፃ  ውስጥ ናቸው -(ዘዳ፲፩ -፳፱። ፳፯ -፲፫)

ጌተ -(ይገይት ይጊት ገዪት ገዝአ) ጌተየ፤ ጌታ ኾነ ተባለ።

ጌቴሴማን -(334) -(ጽር፤ ጌትሲማኒ። ዕብ ጋት ሽማኔይ) የቦታ ም፤ የደብረ ዘይት እግር፤ የዐጸደ ሐምል ቅርብ ጠገብ ግበ ዘይት ምክያደ ዘይት ማለት ነው -(ማቴ፳፮ -፴፮)

ጌት - ሀገር፤ የኢሎፍሊ ክፍል። ፈለሰት ታቦተ አግዚአብሔር ውስተ ጌት -(፩ነገ - -) ሴት ጌትያዊ -(፪ነገ ፲፰ -)

ጌና [1]-ገና ልደትገኒን ገነ

[2]-(ጽር) ገና የልደት ዋዜማ፤ ድራር ገሃድ ወይም ልደት፤ በዓለ ልደት። የሴቶች ገና የወንዶች ገና እንዲሉ እንተ በኵሉ ክብርት ጌና ዘይእቲ ልደቱ በሥጋ -(ተረ -ቄር፳፭ ስንክ -ታኅ፳፰ -፳፱) ጌነሆይ ማለት ከዚህ ወጥቷል፤ ይኸውም ሊታወቅ ጽርኡ ብእሲቶ ሲል ጊኒ ፋም እመ ቤቴ ሲል ጌኒ ይላል

ጌዴር -(ዕብ ጋዴር) ጥር ቅጥር ግንብ መካበቢያ -(ሕዝ፵፪ -)

ጌዶር -(ጽር ጌዱር። ዕብ ግዱድ) ወራሪ ዘራፊ ፋኖ  ወያኔ የሽፍታ ራዊት የወንበዴ ጭፍራ። ገዲድን እይ።እዴግኖሙኑ እሉ ጌዶር -(፩ነገ - -)

ጌጋዪ -(ዪት ይያን ያት) የሚስት የሚሳሳት ተሳሳች አጥፊ ዳይ።

(ያት)         ጌጋይ -ስሕተት በደል ወንጀል ኀጢአት ፋት ዐስበ ጌጋይ። ምንት ጌጋይነ ይመውቱ በው በጌጋየ  ውሉዶሙ። መጽሐፈ ጌጋዩ በጌጋየ ልቦሙ -(ይሁ -፲፩። ኤር -፲፮ ነገ -፲፬ -፮። ማር ፲፭ -፳፮ ኤር፳፫ -፲፯)

ጌግዮ ዮት -(ጌገየ ይጌጊ። ጎገወ) መሳት መሳሳት፤ መንገድ መውጣት በስሕተት መበደል፤ ኀጢአት መሥራት። የጊ እጌጊ ስመ እንተ ፍኖተ ደብር መጻእኩ። ይጌግዩ ሥርዐተ ዘዓመታት ጌገዩ በስካር። አበሱ ወጌገዩ -(ራእ - ኩፋ -፮። ሢራ፵፰ -)

ግሑሥ -(ሣን ሣት ሕሥት) የገባ የመጣ። የራቀ ያገለለ የተለየ ልዩ ፍጹም ባሕታዊ ከረኸኛ። ትንሣኤ ዘግሑሥ ምሐሰት ልደት ቀዳማዊ ዘግሑሥ እምአዝማን ዐላውያን እለ ርሑቃን ወግሑሣን ምኔከ ይኩን ግሑ ምቤተ ክርስቲያን ነበረ ሑሠ በውላጤ ገዳም -( - -፳፪። ማር -ይሥ፲፫ ዳን፫ -፰። ቀሌ ስንክ -ኔ፳፬)

ግሁድ -(ዳን ዳት ) የተጋደ፤ የተገለጠ ግልጥ የታየ የጐላ የተረዳ ልሕ ኵሉ ክሡ ቅድሜከ ወግሁድ ምግባርየ ዘዐመፃ ሁድ ቅድሜየ ለኵሉ። ዕዉቅ ወግሁድ . . .) ወበእንተ ግህ ኮነት ወላዲተ ምላክ ይእቲ -(ሔኖ፱ -፭። ግንዘ ቄር ውዳ -ማር፭)

ግሑፍ -(ፋን ፋት ሕፍት) የተጋፈ የተጠረገ የታፈሠ

ግሂህ ሆት -(ገህሀ ይግህህ ይግሀህ) መብራት ማብራት መጽደል መምላት መተካከል ምሉእ ፍጹም መሆን መድመቅ ገሃ ብሕካ በረቅ መምሰል፤ የወርኅ።

ግሒሥ ሦት -(ግሕሠ ገሐሠ ይግሕሥ ይግሐሥ። የጌሠ ጎር) መግባት ማረፍ ማደር መጠጋት፤ መምጣት መቅረብ -(ዘፍ፲፰ -፭። ፲፱ - -፫። መሳ፬ -፲፰) ወይቤሎ ሐሥ ወንበር ዝየ ትናገር ወግሕሠ ወነበረ -(ሩት፬ -)

 -ከቦ ወደ መፍለስ፤ መንገድ መውጣት መጐዳኘት ማግለል መራቅ ገለል ፈቀቅ ማለት ለማደር ለመስፈር የመንገደኛ -(መሳ፲፰ -፲፭ ፲፱ -፲፭) ስመ ጐንደየ ሒሠ ህየ ወግሕሠ ህየ ይብላዕ እከለ -(፬ነገ - -) ዳግመኛም በግሕሠ ፈንታ ተግሕሠ ይላል አያሰኝም -(ሚል፪ -፰። ዘፍ፴፰ -፲፪ ዘኍ፲፪ -፲፭) ተገሐሥ እምነ ዐመፃ ወትትገሐሥ ምኔከ ለሊሃ ተግሕሡ ማያት ምዲበ ገጻ ምድር ውስተ ሐዱ መካን ይትገሐሥ መንፈስ ቅዱስ ምብዙኃን -(ሢራ፯ - ኩፋ - ኢሳ፫ -፳፮) አንቀጹን ተግሕሠ ካለ ዘንድ ጥሬውን ደግሞ ትግሕሥት ይላል። ትሜንን ትግሕሥቶሙ ምፍኖት ርቱ -(አፈ ድ፪ና -) አንዳንድ መጽሐፍ ግን  ተግሕሦቶሙ ይላል

ግሂድ ዶት -(ግህደ አው ገሀደ ይግህድ ይግሀድ። ዐረ፤ ጀሀደ ጀሀረ) -(ጥጋ) መጋድ መገለጥ መታየት ግልጥ ገሃድ መኾን መታወቅ መረዳት። መጽሐፍ ግን በገሀደ ፈንታ ተግህደ ይላል፤ አያሰኝም። ተግህደ ሃይማኖተ ክርስቶስ ደትገሀድ ተኣምሪከ ሜሃ ለእ ጸንዐት ዛቲ ወተግህደት ዘተግህዱ በወፂእ እምትእዛዛት -(መጽ -ምስ ስንክ -ሐም፴ - - -፲፩ - -፲፰)

ግሒፍ ፎት -(ገሐፈ ይግሕፍ ይግሐፍ። ዐረ ጀሐፈ) መጋፍ መጥረግ ማፈሥ መውስድ፤ ማንሣት ማስገለል መጋፈፍ ማጋፈፍ፤ አብዝቶ መብላት መጠጣት አለማትረፍ ቢተርፍም በልብስ መታቀፍ በኰፋዳ መክተት መወተፍ ጸበል ዘይግሕፎ ነፋስ -(ጥበ፭ -፲፭ መዝ -)

ግሕሠት -መግባት መራቅ አራራቅ ርቀት ሽሽት ደት። ምማቴ ወግሕሠት -(ምሳ፳ -)

ግሕይ ዮት -(ገሐየ ይግሒ ይግሐይ ትግ ገሔ) መፍራት መጨነቅ። መማለድ ማለዳ መነሣት። ጎሐን እይ  የዚህ ጎር ነው

ግህደት -መገለጥ አገላለጥ ግልጥነት ገሃድነት። አብኦ በግህደት ውስተ መንግሥተ ሰማያት ሜሃ ይቀውም ጻድቅ በብዙኅ ህደት -(ግንዘ። ጥበ፭ -)

ግህድና -ዝኒ ከማሁ ገሃድነት፤ መገለጥ። ረከብነ ሕነሂ ቦቱ ህድና ኖት እግ ብነ ህድና ውስተ በዊአ ቅዱሳን -(ቄር -ጰላ)

ግሕፈት -መጥረግ መጠረግ አጠራረግ ጠረጋ።

ግሉል -(ላን ላት ልልት) የተለየ የተገለለ የተንጓለለ የተንጋለለ።

ግሉይ -(ያን ያት ሊት። ጋሉይ) የተገለጠ ግልጥ፤ ርጥ።

ግሉድ -(ዳን ዳት ልድ) ተገለደ የለበሰ የተደጐሰ የተነጠፈ የተጌጠ ደጓሳ ወፍራም።

ግሉጽ -(ጻን ጻት ልጽት) የተገለጠ ግልጥ

ግሉፍ -(ፋን ፋት ልፍት) የተቀረጸ የተጣፈ የተሣለ። -(ግልፍተኛ ) እብነ ባሕርይ ሉፍ ግሉ ውስተ ጽሌ ቦሙ ጽላት ጽሑፍ ወግሉፍ። ወግሉፋን ኪሩቤል ወፀበራት -(ጥበ፲፰ -፳፬ ኤር፲፯ -፩። ንክ -ነሐ፳ ሕዝ፵፩ -፲፰)

ግላ [1]-ጨለማገሊው ገለወ።

 [2]-መሸፈኛ፤ ጥቍር መጋረጃ፤ ጨለማ። ቀላዔ ግላ። ምሳለ ግላ። ጽልመተ ግላ። ስመ ውእቱ ግላ ነበረ ውስተ ሕግ ብሉይ -(ጥበ -ጠቢ ስንክ -ሐም፭ አርጋ -፪። ቆሮ - -፲፭ -፲፮)

ግላል -እንጕላይ ንፋሽ ሐሠር ምራጭ እንግሊላ የኋሊት።

ግላስ -በቁሙ የኮርቻ ልብስ ምንጣፉ ምቹው መቀመጫው -(ዐማርኛ)

ግላውቃ -ግላውቃ -(ጽር ግላፍካ) ያሞራ ጕጕ የቀን ውር የሌት ይነ ብር ባለብሉዮች ግን ጫት አሞራ ይሉታል -(ዘሌ፲፩ -፬። ዘዳ፲፬ -፲፭)

ግልቡብ -ግልቡብ -(ባን ባት ብብት) የተሸፈነ የተከናነበ፤ ሽፍን ሽፍንፍን ልቡብ ርእሱ እን ግልቡባን ገጾሙ። ብእሲ ዘግልቡብ ንግልቡባት -(፪ነገ -፲፭ - ሔኖ፲፫ -፱። ቆሮ -፲፩ -፬። ዲድ -)

ግልባብ -ግልባብ -(ባባት ብያት) መሸፈኛ መጋረጃ ልብስ ክዳን ክንብንብ ሠርመዲ ሻል የሐር የሻሽ መንዲል ጥላ ቀጸላ። ክሥቲ ልባበኪ ሥኡ ግልባብየ ሠተ ልባበ ለብሰት ልባቤ። ቀራንብት ሥዩማት ማንቱ ህየንተ ምስዋር ወግልባቤ ምሐሩረ መርቄ ወእምቍረ ምንዳቤ ክናፊክሙ ይኩናነ ልባቤ ግልባቡ -(ኢሳ፵፯ - ማሕ፭ -፯። ስንክ -ሠኔ፩ ኩፈ -፵፩። ደራሲ። ንክ -ኅዳ፲፫ መስ፳፩)

ግልወት -መሸፈን -(ጥሸ) መሸፈን አሸፈፈን ፈና ልበጣ መሸፈኛ ፋን፤ መጋረጃ ልባጥ ሰሌዳ ግልወታ በወርቅ ፂዋዌ ወፈየ ርምያስ ዋየ በሪሃ ለደብተራ ለሥጠተ ኩኵሕ፤ወተመጢዋ ኮነቶ ልወተ ኀጺን -(አዋል። መጽ -ምስ)

ግልው -(ዋን ዋት ሉት) የተሸፈነ ሽፍን ልብ ልጕም ልብጥ።

ግልየት -መግለጥ መገለጥ አገላለጥ ገለጣ ረጣ። የመጽሐፍ ገጽ ሉሕ ፊት ለፊት ተገልጦ የሚታየው የሚነበበው። በተለየ ግን ግልየት የሚባል፤ ወንዙን ጥራዙን ማጠፊያውን ወሰን አድርጎ በጥፈትና ጥፋት ማኽል ወዲያ ማዶና ወዲህ ማዶ ያለው ባዶ ስፍራ ነው

ግልያ -ዝኒ ከማሁ ገጽ፤ ግልየት፤ ሢራክ ሰንጠረዥ ሐሳበ እግርሰ ውስተ ልያሁ ስፍረ ሰዓት -(አዋል)

ግልፈት -መቅረጽ መቀረጽ አቀራረጽ ቅርጽ ፍልፍል ያበጠ የሰመጠ ግልፈተ ዐይነ ማኅተም ወግልፈት ዕሌሃ ልባስ እለ ልቦሙ ልፈት -(ዘፀ፳፰ -፳፩ ዜና - - አፈ -ተ፳፰)

ግልፎ -( ግልፍ() ዋት) ቅርጽ ጥ፤ የተቀረጸ ጣዖት የሰው ምስል። አርእስተ ዕማድ ዘግልፎ። ኵሉ ግልፎሃ ወአቅንእዎ በግልፎሆሙ ግልፍዋተ ትግበሩ። ልፍዋትተ ጣዖት -(፫ነገ - -፳፯። ሚክ፩ -፯። መዝ -፸፯። ኩፋ - አርጋ -) ግንፋልን እይ

ግሙስ -(ሳን ሳት ምስት) የተገመሰ የተቈረሰ ግምስ ርስ

ግሙራ -(ደቂቅ አገባብ) ጭራሽ ካቶ ፈጽሞ ካንዱ ዘን መቼም መች ለእግዚአብሔርሰ ልቦ ዘርእዮ ሙራ ሙራ ያስተርአየ ዘከመ ኢትምሐሉ ሙራ -(ዮሐ፩ -፲፰ ማቴ፱ -፴፫። -፴፬) ሲወድቅበት ለዘወትር ለዘላለም ያሰኛል ምስጢሩ ዚያው ይገባል። ቦኑ ለግሙራ ረምም ንከ አሐተ መሥዋዕተ ገብረ ንተ ለግሙራ ይርአይ ለግሙራ ትረስዐኒ ግሙራ -(ኢሳ፵፪ -፲፬ ዕብ፲ -፲፬። መዝ - ፲፪)

ግሙር -(ራን ራት ምርት) የተጨረሰ የተካተተ የተቻለ  የተወስነ ውሱን። የጐመራ ጐምር የተጐመረ ምር፤ የጋመረ የዳበረ።

ግሙን -(ናን ናት ምንት) የገመነ ያደፈ የረከሰ ርኩስ። ግሙን ርባኖሙ ኃጥኣን ልሳን ሙን ሙናነ መንፈስ ኵሉ ፍናዊሆሙ ግሙናን ምድር ምንት -(ሢራ፴፩ -፳፪ ፶፩ -፭። ዲድ -፳፩ ቅዳ -ሕር ኩፋ -፳፪ ዕዝ - -) ሐረርም ዘማይንቱ ግምንት ግሙና ይላል

ግሙእ -(ኣን ኣት ምእት) የገማ ግም በሽቃጣ። -(ተረት) ግም ለግም ቢተቃቀፍ አይነቃቀፍ

ግሙዕ -የተላጨ ልጩ ሽልት ልዝብ ፍሑቅ

ግሙድ -(ዳን ዳት ምድ) የተቈረጠ ርጥ ምድ ጐማዳ። ቶማስ ዘአባላቲሁ ሙድ ያዕቆብ ሙድ -(ስንክ -ነሐ፳፬ ኅዳ፳፯)

ግማስ -(ሳት) ግማሽ እኩሌታ መንፈቅ -(ተረት) ግማሹን ተላጭታ ግማሹን -ተቀብታ። አሐ ኅብስተ ማሰ ኅብስት -(አዋል)

ግማኔ ግምነት -ዝኒ ከማሁ ምኵሉ ማኔ ጢአት። ግማኔ ፍስ -(ኩፋ -፳። ጥበ፲፬ -፳፮) ማረር መግመን ማሳረር ማግመን አገማመን ገመና ዐራራነት ጥቍረት  ነውረ ኅብስት ለእ ንቅዐት ውስተ ኅብስት ምነት ታዕርግዎ -(ቄድር -ገ፹፱)

ግማን -(ናት) እድፍ ርስሐት ትክቶ ዝሙት ኀጢአት ገመና ነውር የሚያሳፍር። ምድር ርኵስት ይእቲ በግማኖሙ ለአሕዛበ ምድር -(ዕዝ፱ -፲፩)

ግማዔ -መላጨት -(ጥላ) መላጨት አለጫጭ ረጣ ሽለታ

ግምአት -መግማት፤ አገማም ግማት ሽታ

ግምኤ -ማሰሮገምዖ ገምዐ፤ ግምዔ

ግምዔ (ዕያት ገማዕይ ) ምንቸት ማሰሮ ይነት ጭንቍላ ታናሽ ሸክላ ልጩ ራስ ጭንቅላት የምትመስል የዘይት (ተረት) ጋኖች ለቁና ምንቸቶች ጋን ኾኑ ምዔ ሕኵት ምዔ ቅብዕ ኵሉ ምዕያቲሃ ዘቅብዕ ሥኣ ቅብዐ በገማዕይሆን (ዘኍ፭ ፲፯። ዮዲ ፭። ዘኍ፬ ማቴ፳፭ ፡፬)

ግምደት ግማዴ -መቍረጥ መቈረጥ፤ አቈራረጥ ረጣ ጨዳ ጐማድነት

ግምድ ግማድ -(ዳት) ቍራጭ፤ ጐመድ ማጅ፤ ራጅ ዕራፊ ቅናሽ ሙዳ ጉማ -(ግጥም) ኢየሩሳሌምን ይመኛል ሰው ኹሉ፤ ግሸን አይዶለም ወይ ግማደ መስቀሉ ግማድ ዘተርፈ ምዕፅ ምደ ደርግሐ ልብስ በግማደ ልብሱ ማደ ሥጋ ማዳት ዘኵሉ ባል ማዳተ ብድ -(ጥበ፲፫ -፲፫ ማር፪ -፳፩ ፊልክ -፲። ፪፻፵፫ ሕዝ፳፬ -፬። ኢዮ፲፮ -፮። ቅኔ)

ግሰት -(ጥዳ) መዳሰስ አደሳሰስ ዳሰሳ ዳበሳኢልኩፋን በግሰተ ጻብዕ። በግሰተ ናፍሪሁ ዳንኤል -(መጽ -ምስ)

ግሱስ -(ሳን ሳት ስስት) የተያዘ የተዳሰሰ የተደመሰሰ

ግሡጽ -(ጻን ጻት ሥጽት) የተገሠ የተማረ የተመከረ ምሁር ምኩር የተሠራ የተቀጣ፤ የተገራ ሥሉጥ፤ ሽቍጥቍጥ። ወልድ ግሡጽ ያስተፌሥሕ በዊሁ፤ ሰብእ ግሡጻን ግሡ በትምህርተ መንፈስ ቢይ ወአኮ ሕጹጽ -(ፈላስ ስንክ -ጥር፰)

ግሣጼ -መገሠጽ፤ -(ጥገ) መገሠጽ፤ አገሣሠጽ፤ ግሠጻ ተግሣጽ ነቢየ ምህሮ ወግሣጼ -(ስንክ -ጥቅ፳፩)

ግስ -ጓዝ እክት ግስንግስ ዕቃ ግሴት የሚያዝና የሚዳሰስ ኹሉ ሰማይ ነግሱ ምድር ከነልብሱ እንዲሉ ከነጓዙ ሲሉ። ጋሰሰ አጋስስ ማለት ከዚህ ወጥቷል።

 -በቁሙ፤ የቋንቋ መጣፍ የዘርና የነባር መድበል መዝገበ ቃል ባቡ በፊደል ተራ የታከተ የተከተተ። ምስጢሩ ግን ተወራራሽ ቃል ማለት ነው አንዱ አንቀጽ እስከ ማንያ ነባሩና ጥሬው እስካሥር መርባቱ በመወራረስ ነውና

ግስላ -(ዐማርኛ) ያውሪ ስም ብስጩ ግልፍተኛ ተገሰለብኝ ይገስላል እንዲሉ ተቈጣ ሲሉ።

ግረት [1]-መገዛት አገዛዝ ሥጋዊ  ሥራ ስመ ረትሰ በሥጋ ኅዳጥ ዘመን ትበቍዕ -(፩ጢሞ - -፰። ገድ -)

[2]- ዕፅ፤ ግራር የግራር ይነት ዛፍ ቀንበር። ዕፀ -7ረት -(ስንክ -ኔ፲፯ መጽ -ምስ)

ግሩም -(ማን ማት ርምት) ቁሙ የተፈራ የሚያስፈራ አስፈሪ፤ ገናና ታላቅ፤ ውብ ድንቅ እስመ ልዑ ወግሩም እግ ግሩመ ገጽ ኮኑ ሩማነ ዘይገብር ሠናየ መጠን ግርምት ወለብሰት ልባሰ ክብራ ወኮነት ርምተ -(መዝ ፵፮ ዘዳ፳፰ -፶። ሮሜ፲፫ -፫።ቅዳ አስቴ -)

ግሩር -(ራን ራት ርርት) ዝኒ ማሁ የተገዛ ተገዥ ግሩር ታሕተ መከየድ -(አርጋ -፩። ግብ፳፮ -)

ግሪጳ -(ጽር -ግሪፕስ ዕብ ፔሬስ) ላቅ አሞራ ግድንግዲ ንጣቂ ግልገል ንሣ ቅልጥም ባሪ የሎስ ጐሤ ጐሤ ያንሣኽ እንዲሉ። ባለብሉዮች ግን ዘማች አሞራ ይሉታል -(ዘሌ፲፩ -፲፫። ዘዳ፲፬ -፲፫)

ግራ [1]-የንብ እንጀራ ዕጩ ጐመጩ ፈፉ ሳይቀር ነማሩ ከነወለላው። የማር ፈፍ የተነጠረ ልጥልጡ ግግሩ ነጋሪቱ። ነገረን እይ ዘሩና ምንጩ ርሱ ነው መጽሐፍ ግን ግራ መዓር በማለ ፈንታ መዓረ ግራ ይላል፤ መዓርን እይ -(ኢሳ፷፬ - ዮዲ፲፮ -፲፭ ሱቱ -ዕዝ፲፫ -) እንገር እንጀራ ሙጌራ ማለት ዚህ የወጣ ነው።

[2]-ግራ፤ -(ዕብ ጋሩዕ ሕጽጹ) በቁሙ ፀጋም ሀካይ ድኩም -(ዐማርኛ)

ግራም -የሚዛን ም፤ እጅግ ታናሽ ክፍል የኪሎ ሕኛ።

ግራብ -(ባት ዐረ ጅራብ ትግ -ገራቢት) ቀርብ ቀርበታ ርኮት ራዎት ርባብቻ የማር የቅቤ የዘይት ስልቻ ማሰሮ ገንቦ ለእ ሠሥከ ቅብዐ ዘይት ትረክብ ራባቲሃ -(መጽ -ምስ)

ግርማ -በቁሙ፤ ማስፈረት አስፈሪነት የመፈረት የመወደድ ሀብት ክብር ባለሟልነት የመልክ ውበት ደም ግባት ደመ ግቡነት። ዘበዝኀ ሠሐቁ የሐጽጽ ርማሁ አንበረ ርማሁ ዲበ ኵሉ ሕዛብ። ብኪ ግርማ ራእይ ዘየዐቢ እምግርማ ሱራፊል ኢትርአይ ርማ ርእየቱ ለኤልያብ -(ፈላስ -፳፩ ፩ዜና -፲፬ -፲፯ ውዳ -፩። ነገ -፲፮ -፲፯)

ግርጣጥ -ታናሽ ሙዚቃ የዘፈን ዕቃ የሙዚቃ ይነት ገንታ ወግርጣጥ -(ሥር -አኵ)

ግበ  ዐይን -ያይን ድጓድ ዋሻው ርጓዳው ምዕቃሉ ርንዶው እንደ ፈርጥ የተሰካበት ወይም  እንደ ውሃ የመላበት -(ምሳ፳፬ - ካ፲፬ -፲፪)

ግቡር -(ራን ራት ብርት) የተሠራ የተደረገ ፍጡር ቡር በጽድቅ ወበርትዕ ጺን ቡር ማእሰ በግዕ ቡረ መሓን ለግቡራንሂ ይቤልዎሙ ኮኑ ቡራነ ወኢተፈጥሩሂ አላ ሀለ ዘእንበለ ጥንት -(መዝ -፻፲። ሕዝ፳፯ -፲፱ ዘፀ፴፭ -፯። -ድ፳፪)

ግቡእ -(ኣን ኣት ብእት) የገባ፤ የተመለሰ ምልስ ቅልስ

ግብ -ድጓድ ጐሬ፤ገብቦ ገበበ

 -( ግበብ፤ ባት፤ አግባብ ዕብ ጎብ ሱር ጉባዐረ ጉብ) መክተቻ መከተቻ ድጓድ ዐዘቅት ዋሻ ጐሬ መቃብር የምድር ቤት የመሰለው ኹሉ። ዘከረየ ለቢጹ ይወድቅ ውስቴቱ በበ ምድር ድፍኑ በባተ እለ አብያቲሆሙ ውስተ በበ ኰኵሕ። ግበበ ራዊት እለ ይወርዱ ውስተ -(ሢራ፳፯ -፳፮። ዕብ፲፩ -፴፰። ዮሴፍ ኢዮ፴ -፮። ኤር፱ -፲፩ ሕዝ፴ -፲፰) ማለት ዐማርኛው ከዚህ ወጥቷል።

ግብሱስ -(ሳን ሳት ስስት) የተመረገ የተለሰነ፤ ምርግ ልስን ቅብ ልቅልቅ። አረፍት ብስስት መቃብር ግብሱሳን -(ግብ፳፫ -፫። ማቴ፳፫ -፳፯)

ግብስስ -(ጽር ጊብሶስ ዕብ ሲድ) ኖራ በረቅ የደንጊያ መድ ነጭ ደቃቅ አውዐዩ ዕፅምቲሁ ንጉሥ ለግብስስ ዐጥንቱ መድ እስኪኾን ኖራ እስኪመስል ማለት ነው፤ ባለብሉዮች ግን ግብስስ ለሚባል ጣዖት ይሉታል -(ዓሞ፪ -) አምጽኡ ግብስሰ። ከመ ግብስስ ድቁቅ -(ሄርማ -ገ፹፭። ኢሳ፳፯ -)

 -ልስናት ልቅልቃት። የተላጠ የተቀረፈ ምርጊት የፈረሰ የተናደ ቤት።

ግብረት -ማድረግ፤ መደረግ መሠራት መፈጠር አሠራር አደራረግ ሥራ ከመ ግብረተ ንፋል። ብረተ ዕጣን ግብረተ ፍትሎ ለኵሉ ብረቱ ደብተራ እምቅድመ ብረተ ሰማያት ወሠናይ ግብረቱ ወግብረቶንሂ ብረተ እግዚእ -(ዘፀ፳፬ - -፴፭። ፴፮ -፳፪። ፴፭ -፳፩ ቅዳ -ግሩ ዮሴፍ አርጋ -)

ግብር [1]-ርህ፤ ግድ ግዴታ። በግብር ዘእንበለ ፈቃዱ በግብር ይከውን ዘነበበ ዮናስ ግብረ ይመጽእ መንሱት -( - - -፲፪ ጦቢ -፲፱ -፰። ሉቃ፲፯ -፩። ዕብ፱ -፲፮) እወ አማን በማለት ፈንታ ግብር ይላል፤ አያሰኝም -(ሉቃ፬ -፳፫)

[2]-በቁሙ፤ ጸባሕት አምኃ ድኻ ለመንግሥት የሚሰጠው ከመ የሀቡ ብረ እለ ይቀውሙ ላዕለ ብር። ርኡሰ ብር ይሁብዎ ብረ በበ ዓመት -(፪ዜና - - - ፲፰ ፳፯ -)

[3]-በቁሙ፤ ጸባሕት አምኃ ድኻ ለመንግሥት የሚሰጠው ከመ የሀቡ ብረ እለ ይቀውሙ ላዕለ ብር። ርኡሰ ብር ይሁብዎ ብረ በበ ዓመት -(፪ዜና - - - ፲፰ ፳፯ -)

ግብርናት -ባርነት ገባርነት ተገዥነት ዕዝክሙ እምግብርናእት ብር ለእመ  ግዕዘ እምግብርናቲሁ ፄወዎሙ ወወሀቦሙ ለግብርናት -(ዲድ -፴፫ ዮሴፍ።ስንክ -ኅዳ፳፮)

»ግብተ -ድንገት በድንገት ወዲያው ቶሎ በቅርብ ይቈይ ይዘገይ ግብተ መጽኡ ብተ በረቀ ግብተ ሀለዉ ሐደሰ ብተ -(ሉቃ፪ -፲፫ ግብ፬ -፫። ዮዲ፬ -፫። ዕብ፲ -)

»ግብታዊ -ድንገተኛ የድንገት በድንገት የኾነ ያልታሰበ ሞተት በሞት ግብታዊ -(አዋል)

ግብት -ድንገት ወጊብ ወገበ

 -»ግብት ድንገት፤ ግጭት፤ አደጋ አስቀድሞ ሳይታሰብና ይታወቅ እንዲያው ደርሶ የሚኾን ነገር እጅግ ታናሽ ጊዜ እንደ ደቂቃና እንደ ሴኮንድ እንደ ቅጽበት ያለ እመሰ ግብት ውእቱ ጢአት ዘግብት -(ዘኍ፴፭ -፳፪ - - -፲፩) ባዕድ ነግድ በማለት ፈንታ ዐርከ ብት ምላ ብት ይላል፤ ድንገት የተገኘ ማለት ነው -(ሢራ፱ - መዝ -)

ግብን ግብነት -(ዕብ ግቢና። ሱር ግቤንታ። ዐረ ጁብን) ጅብና ርጎ ይብ ያይብ ልጥልጥ፤ በሚዛን የሚሼጥ ከመ ሐሊብ ሐለብከኒ ወአርጋዕከኒ ግብነ የሐልቦሙ ለእንስሳ ወይገብር ግብነ ብነት ዘላሕም -(ኢዮ፲ - ስንክ መስ፲፰ ሥር -ጳኵ)

ግብአት -መግባት መመለስ፤ አገባብ አመላለስ ግቢ ምለሳ መያዝ መስጦት። ግብአተ መንጦላላዕት። ሑረት ወግብአት። ብአትከ ውስተ ርስትከ ዜና ብአቱ ለአግሪጳስ ሮሜ ፈድየከ በግብአትየ በእንተ ብአቱ ክርስቶስ -(ቅዳ። ዘካ፯ -፲፬ ቀሌ። ዮሴፍ። ሉቃ -፴፭። ማቴ፳፮ -፵፯)

ግብጦ -ያበባ እኽል መኬ የሚመስል ተርሙስ ግብጣዊ ማለት ነው።

ግብጽ -(ጽር ኤጊብት ዕብ ሚጽራይም። ዐረ ሚጽር) ግብጥ፤ ስመ ነገድ ሀገር የካም ዕፃ መካነ ጻዕር ልሳነ ባሕር የእስያና ያፍሪቃ ወሰን  ደንበር ማለት ነው። በግብጽ ፈንታ ቅብጥ ይላል ችው አንድ ነው ብሔረ ብጽ ልሳነ ቅብጥ -(መዝ -፻፬ ሃይ -አበ)

ግተት -ግትቻ ሰባራ የማይረባ ሥራ የማይዝ ዕላቂ ውዳቂ ውራጅ አሮጌ ወኮነ ተት በውስተ ሕዛብ፤ ግተት ዘለምንትሂ ይበቍዕ -(ሆሴ፰ - ኤር፳፪ -፳፰)

ግቱት -ያረጀ ያለቀ የተጠገነ የተናቀ -(ኢያ፱ -)

ግኑዝ -(ዛን ዛት ንዝት) የተገነዘ ግንዝ ውር ድብቅ ፍን። ሶበ ታወፅኦ ግኑዝ። ከሣቴ ትምህርት ግኑዝ -(ግንዘ ስንክ -ታኅ፲፰)

ግኑይ -(ያን ያት ኒት) የተገዛ ትሑት አገልጋይ -(አርጋ) ,

ግናሓት አግናሕ -ኸቶች ጣዎች ተግሣጾች ኀይለ ቃሎች። ወይእዜኒ ቤከ ነገርየ ዘልዑለ ታሌዕል አግናሒነ ዕለ ኵሉ -(ተረ -ቄር፰) መተርጕማን ግን አግናሒ ብለው ጥሬውን በቅጽልነት ይፈቱታል።

ግናሕ -(ዕብ ግኒሓ) ጩኸ ቡታ እሪታ ታላቅ ድምፅ ተግሣጽ ኀይለ ቃል ስድብ ብርቱ እዛዝ የኵራትና የቅቢት ቃል የሚገባ የማይገባ። እስመ ውእቱ ዘይትናገረክሙ በቃለ ናሕ መኰንን ወከመ ቢይ። ኮኑ ድንዚዛነ ንዘ ይትሜክሑ ወደለዎ ይትናገሮሙ በቃለ ናሕ ዘያሐምም በትዕቢተ ፀር በበግናሕ -(አፈ -ተ፬ ድር፳፩ -ገ፯)

ግናይ -(ያት) [1]-አገልግሎት፤ አገዛዝ ምስጋና፤ ቍልምጫ ልመና የመዝሙር ስም ግነዩ ግነዩ የሚል። አይኑ ናይ ወአይኑ አኰቴት ናይ ለክሙ ሥሉስ ቅዱስ ዘለከ ስብሐት ሰጊ ወግናይ። ያቅርብ ለእግ መሥዋተ ስብሐት ወግናየ ጸሎታት። እምድኅረ ንበቡ ዘመሩ  ግናየ ስብሐት -(ቅዳ -ዮሐ ደራሲ ድር ኪዳ ዜና - -፳፪)

 -ረድፍ ተራ የመዘምራን ክፍል ስድሩ ድርድሩ፤ ግራና ቀኝ ኹኖ  ግናያትን እየደገመና እያዜመ እያስተዛዘለ የሚኼድ የሚያውድ ወአቀምኩ ክልኤተ ናያት በይት እለ የሐውሩ ይምነ ወካልእ ግናያት እለ የሐውሩ ፅግመ፤ ወአነ ድኅሬሆሙ -(ነሐ፲፪ -፴፩ -፴፯) መዘምራኑን ግናያት ያሰኘ የመዝሙሩ ስም ነው

[2]-(ዕብራ ወትግሬ) ጕድ ድንቅ ባጣ ተርካሳ ዐጭ ግጭር ድንክ ኰሳሳ ልምሾ ዐንካሳ ዕውር ንባሳ ምኑን ኅሱር ሕሡም ጥፉ መልከ ክፋ። -(ግጥም ትግሪኛ) ሰበይቲ እንግዳ ግናይ ወሊዳ። ጕድ ለክፉም ለበጎም ለብርቅና ለድንቅ ይነገራል፤ እንደ ታምራት ነው። -(ግጥም) የሚጣቅ ማኔል ያንተ አያልቅም የፈረስ ገላ እንደ ርቅ ስትጠቅም።

ግንባር -በቁሙ፤ ፍጽምን እይ ከገጽ የመጣ ነው።

ግንባት -(ታት) ገንቦ ዳብሬ ዶጮ ርኮት ራዎት ታናሽ ቀርበታ ወወሀበታ ለወለታ ትጹር ንባተ ወይን -(ዮዲ፲ -)

ግንቦት -ስመ ወርኅ፤ ታስዕ እመስከረም ገቦ ክረምት ጎረ ክረምት፤ ገቦንና ዴን እይ። በግንብ ዘይቤ ሲፈቱት ግን ወርኀ ራሬ ያሰኛል የባቢሎን ግንብ ይቀር መቅደሶች በግንቦት ተመሥርተዋል -(፫ነገ - - ዕዝር፫ -፲፫) ያገዳን እኽል ገነበበ ማለት ማርኛው ከገነበ ሥር የወጣ ነው።

ግንዘት -(ዐረ ጅናዝ ፍታት) መገነዝ -(ጥገ) መገነዝ አገናነዝ ግነዛ ግንዛት። ግንዘት ሥጋኪ በመዋጥሐ ክታን ገነዞ ለጴጥሮስ ንዘተ ሠናየ። ያሤኒ ግንዘተ ደናግል -(ደራሲ ንክ -ሐም፮ -መስ፲፱)

 -የመቃበር ሸማ ክፈን፤ ሣጥን ሌን። ሬሳ የሬሳ ምስል አጐበር ዐልጋ የፍታት መጽሐፍ ያቅድም ግንዘቱ ይሑር ቅድመ ዐራተ ግንዘቱ ሥአት ንዘተ ወገነዘት አሠረ ንዘቱ ተኀድገ ንዘት ዘይትነበብ ዕለ ሙታን -( - -፵፪ -፩። ፳፪። ፩ነገ -፲፱ -፲፫ ስንክ -ጥቅ፳፰ ግንዘ -ገ፩)

ግንጱል -(ላን ላት ጵልት) የተለወጠ ልውጥ ግልብጥ።

ግንጵሊት -ግልብጮ የኋሊት የግርንግሪት። እመ ረስዎ ንጵሊተ ይከፍእ ጋሁ ምስጢር መልኩ -(ተረ -ቄር)

ግንፋል -(ላት) የጡብ ጭቃ የተቦካ የተገነፋ። ጡብ የሸክላ ዐይነት ደንጊያ ጭቃ ተሠርቶ በፀሓይ ደርቆ በእሳት የሚበስል የሚፈተን ለሕንጻ የሚኾን። ንጥፋሕ ግንፋለ ወናብስሎ በእሳት በጽቡር ወበግንፋል ወድቀ ግንፋል ሣእ ንፋለ ወሠዐል ዕሌሃ ሀገረ -(ዘፍ፲፱ -፫። ፀ፩ -፲፬ ኢሳ፱ -፲። ሕዝ፬ -) የጡብ ዱቄት የደቀቀው የተሰለቀው። በቍስሉ ወደዩ ግንፋለ ደመረ ምስለ ንፋል ከመ ይቅብዕዎ በጼው ወብሒእ ወግንፋል -(ስንክ -ግን፮ -፳፮ ሐም፰)

ግኡዝ -(ዛን -ዛት፤ እዝት) የተጋዘ የጠላ የተነቀፈ ንቁፍ

ግዑዝ -(ዛን ዛት ዕዝት) የተጓዘ ነጻ የወጣ። ግዑዝ ውስተ ምዉታን። እመኒ ዕዝት ደብተራ ይሬስዮሙ ግዑዛነ -(መዝ -፹፯። ዘኍ፩ -፶፩። ነገ -፲፯ -፳፭። - -፴፩)

ግዒር ሮት -(ግዕረ ገዐረ ይግዕር ይግዐር ዐረ ጀዐረ። ዕብ ጋዓር ሱር ግዓር) መጋር መጮኽ መጨነቅ፤ ማጣር ገዐርኩ ቤከ ግዕሩ እመዝራዕት ብዙኃን የዐወይዉ ወይግዕሩ ገዐሩ ምግብሮሙ ገዐረ በዐቢይ ቃል። ግዒ ሞተ -(ኢዮ፴ -፲፱። ፴፭ -፱። ኤር፳፱ - ዘፀ፪ -፳፫ ማር፲፭ -፴፬ -፴፯ -፴፱)

ግዒት ቶት -(ገዐተ ይግዕት ይግዐት ወግዐ ጠፍሐ) ማገንፋት መጋት ማጠጣት ማስጐንጨት በጋት ጥርኝ መስፈር መለካት። ኢይግዕቱ ሎሙ ወኢይፌትቱ ሎሙ ኅብስተ ኢያስትይዎሙ ማለት ነው -(ኤር፲፮ -)

ግኢዝ ዞት -(ግእዘ አው ገአዘ ይግእዝ ይግአዝ። ሱር ግዓጽ ጋየጸ) ማዘን መቈጣት መበሳጨት መንቀፍ ጥላት መጣላት፤ መውቀሥ መክሰስ ገአዝኩ ሕይወትየ ምንት ንከ ትግ ፈቃደ ግዚ ወዳእነ ግእዝናሆሙ ወግእዘ ጽንዐ ቦሙ ምንተ ረከቡ በላዕሌየ በዘይግእዙኒ ሶበ ይግእዘከ ርክከ ግእዞ ሕዝብ ለሙሴ -(ኩፋ -፳፯። ራ፵፩ -፬። ሮሜ፫ -፬። ር፲፮ -፲፬። ኤር፪ -፭። ምሳ፳፭ -፰። ፀ፲፯ - -)

 -ማጋዝ ግዞት ቤት ማግባት ግእዝ መማር እየቈጠሩ ማንበብ።

ግዒዝ ዞት -(ግዕዘ ይግዕዝ ይግዐዝ) መጓዝ፤ ካሉበት መነሣት እግርን መንቀል መዠመር ማዝገም ቀስ እያሉ መኼድ መዝመት። ወግዕፅዙ ደቂቀ ስራኤል ምራምሴ ውስተ ሱኮት። ወይግዕዙ ብጽ ድኅሬዎሙ ወግዕዝክሙ ውስተ ገዳም -(ዘፀ፲፪ -፴፯። ፲፬ - ዳ፩ -)

 -መበተን መበታተን፤ መዘራት መሠራጨት ዕዙ ሕዛብኪ ውስተ ድባር ወአልቦ ዘያስተጋብእ -(ናሖ፫ -፲፰)

 -ሐራ መውጣት፤ መፈታት መለቀቅ፤ ነጻ መኾን ዕዝክሙ ምግብርናት ገብር ለእመ ዕዘ ምግብርናቲኩ ይግዐዝ ገብር እምአግዚኡ -(ዲድ -፴፫ ዮሴፍ - -) በግዕዘ ፈንታ ተግዕዘ ይላል፤ ስሕተት ነው። ይትገዐዙ ወይፈቅዱ ይፃኡ እምኔከ ተግዕዝክሙ እምኀጢአት ግዕዛነ ተግዕዘት -(ሢራ፴ -፴፬። ሮሜ፮ -፲፰ ዘሌ፲፱ -)

ግዕት -ግት፤ ወሽ ት፤ የእንስሳት።

ግእዘ -ተጓዘ ነጻ ወጣግዒዝ ግዕዘ።

ግእዘት -ማጋዝ መጋዝ መንቀፍ መነቀፍ ነቃቀፍ፤ ነቀፋ ነቀፌታ፤ ወቀሣ፤ ከሰሳ። በእንተ እዘት ዘግእዝዎ እንበለ ተካሕዶ ወግእዘት -(ዘፀ፲፯ -፯። ደራሲ)

ግዕዘት -መጓዝ አጓጓዝ ነጻ መውጣት ነጻነት ርነት። ግዕዘት ምትፅርርት ሰላም -(ፊልክ -፻፭)

ግዕዛን -ነጻ ነጻነት እስብክ ግዕዛነ ለፂዉዋን ወጸጎከነ ምግብርናት ዕዛነ በእንተ ግእዛን ወግብርናት። ወኢይዔምፅ ዕዛኖሙ -(ሉቃ፬ -፲፱ ኪዳ። - -፴፩። ፊልክ -፻፹፩)

ግእዝ [1]-የቋንቋ ስም ማዊ አዳማዊ ቋንቋ የዕብራይስጥ ወንድም ከዐረብ ከሱርስት የሚገጥም። ዘይቤው አልፍ እንደ ማለት አንድ መዠመሪያ ምስጢሩ  ጥንታዊ አዳማዊ ልሳን ማለት ነው -(ዘፍ፲፩ -) ፪ኛም እንደ ሌላው ቋንቋ ብዙ ድካም ስለሌለበት ቅን ገር ብለው ይፈቱታል። ተርጐመ እምልሳነ ቅብጢ ለዐረብ እምዐረቢ ለግእዝ -(ሃይ -አበ -)

[2]-የፊደል አንድ ወጣት አንድ ቅንጣት አንድ በቀል ዕዝል ቅጥል ነቍጣ ምክትል ዋየል አጣማጅ ኹለተኛ ፈርጅ የሌለው ቀንጃ ነጠላ ፊደል -(ኮንሶን) ከአ እስከ ያለ ላማ ካዕብ እስከ ሳብ ድረስ ሳይኖረው ርሱው ራሱ ግእ ብቻ ነበረና ቋንቋውን ግእዝ ያሰኘው ይህ ነው ይባ ዚያ ወዲህ ግን ካዕብ ስከ ላሉት በኵ ግንባር ቀደም ለ፮ ወንድም ስለ ኾነ አንደኛ ወይም መዠመሪያ ይባላል ግእዝ ካዕብ ሣልስ፤ ራብ ኃምስ ሳድስ፤ ሳብዕ እንዲሉ። ግእዝ አንድ አንደኛ መባሉ በአ ምክንያት ነው።

[3]-የንባብ መዠመሪያ ንባብ፤ ሕፃናት የፊደልን ቍጥር እጅ እግሩን ለዩ በኋላ ከነቍ እስከ ነቍጥ እየጐተቱ የሚያግዙት ማጋዝ። ለንባብ ትምርት  በየስልቱ ስም አለው ግእዝ ወርድ ዐቢ ድጋም

[4] -የዜማ ም፤ አንደኛ ልት መዠመሪያ ዜማ፤ ኛው ዕዝል ኛው አራራይ ይባላል ሠለስቱ ዜማ ዘውእቱ እዝ ወዕዝል ወአራራይ ወእምዝ ትብል ጸሎተ ዘእምዳዊት በዜማ ግእዝ ህየንተ ዕዝል ዘነግህ እዝ -(ስንክ -ግን፲፩ ግንዘ። ድጓ)

ግዕዝ -(ዛት) ኹነታ ኳኻን ጽንዕ ልማድ፤ ሐሳብ ኅሊና ፈቃድ፤ ባሕርይ ባይ የባሕርይ ሥራ መል መንገድ አካኼድ አረማመድ የክፉ የበጎ ሰብአ ዐይን ንትሙ ወመጻእክሙ ትርአዩ ዕዘ ብሔር ሰብእ ሠናያነ ግዕ ስምዐ ግዕዝነ። ወልድከ ዘኢየሐውር በገዕዝከ ምከመ ረዩ ዕዛቲሆሙ። ሰማይ ጥቀ ሠናይት ወብርህት ፈድፋደ በግዕዛ በግዕዘ ጠባይዕ ወበባሕርይ። ወነያ እቲ በዓልተ ጥዒና ሐዳስ፤ ምስለ ራዊት ዘተኀድር ነፍስ ንዘ እምነ ሰብእ ትትገሐሥ፤ ስመ ዕዘ ርዌ ቢይ ወግዕዘ ሰብእ ንኡ ዝንቱ ውአቱ ግዕዝኪ ምንእስኪ -(ዘፍ፵፪ -፱።ዮሴፍ ራ፴፭ -፳፪ ፊልክ -፬። አፈ -ተ፲፮ ድር፪ ቅኔ ኤር፳፪ -፳፩)

ግዕዝና [1]-ዝኒ ማሁ ጻነት -(ሄርማ -ገ፶፬)

ግዘት -በቁሙ ውግዘትወጊዝ ወገዘ

 [2]-»ግዘት -(ታት) ዝኒ ከማሁ፤ መገዘት -(ጥገ) መገዘት አገዛዘት በቁሙ ግዝት ርግማን። ግዘት ዘነበበ ባቲ ዮሐንስ ዘቡርልስ ንቀጸ ግዘት ንባበ ግዘት -(ሃይ -አበ ስንክ -ታኅ፮)

ግዙም -(ማን ማት ዝምት) የተቈረጠ የተጨፈጨፈ ርጥ ምልምል። ዕፀው ዙማን -(መጽ -ምስ)

ግዙር -(ራን ራት ዝርት) በቁሙ የተገዘረ ግርዝ ብልተ ጥሩ፤ ይሁዲ ፈላሻ እስላም ቢጽ ሐሳዊ ወንጌል እንበለ ኦሪት ጥምቀት እንበለ ግዝረት አትረባም አትጠቅምም አታጸድቅም የሚል ዙር ወቈላፍ በእንተ ኅጽዋን ወግዙራን -(ሮሜ -፴። - -፴፫። ግብ፲፭ - - ፳፬)

ግዙእ -(ኣን ኣት ዝእት) ግዙ ግዝ፤ የተገዛ ተገዥ ዜጋ ገብር ገባር

ግዙፍ -(ፋን ፋት ዝፍት) ቁሙ ዝኒ ማሁ ይኩን ብሶሙ ምፀምር ዙፍ ግዙፈ ክሣድ ግዙፋ ልብ -( - - -፮። ዘዳ፱ -፲፫። አርጋ -)

()          ግዛም -(ማት) ጕማጅ ራጭ ጭፍጫፊ ዝንጣፊ

()          ግዛዕ -(ዓት ዕብ ጌዛዕ። ዐረ ጂዝዕ) ንደ ሥር በላይና ከዐጽቅ በታች በመካከል ያለው አዕጹቅን እንደ ምድ ኹኖ የሚሸከም። በትግርኛ ግን አንዳች ማለት ነው

ግዝመት -መግዘም መገዘም አገዛዘም አቈራረጥ፤ ቈረጣ ምልመላ ጭፍጨፋ።

ግዝረት -በቁሙ መግዘር መገዘር አገዛዘር ገዘራ ግዙርነት፤ ግዝራት ወሀበክሙ ሙሴ ግዝረተ ወግዝረትሰ ዝረተ ጽላሌ ልብ በመንፈስ ወምንትኑ ስላጤሃ ለግዝረት። በእንተ ግዝረት -(ዮሐ፯ - ሮሜ፪ -፳፱ -፩። - -፶፩)

ግዝሮ -ግዝረት ግዝራት ደመ ግዝሮሁ ወልድየ የሐጽጽ ሕማመ ዝሮሁ ለአረጋይ ምሕማመ ሕርደቶሙ ለንኡሳን -(ዘፀ፬ -፳፭ መጽ -ምስ) ግዝረት የሚገባ ለወንድም ለሴትም ሲኾን በወንድ ላይ ብቻ ይነገራል ልጅ ካልተገዘረች ጡቷ አይገንም አይፋፋም ታላላቅ አይኾንም። የፈላስፎች መጽሐፍ፤ ጡት የሚገዝፍበት የሚያብጥበት የሚነፋበት ምክንያቱ ግዝረት ነው ይላል አነ ቅጽር ወአጥባትየ ማኅፈድ ያለውም ይህንን ያስረዳል -(ማሕ፰ -)

ግዝአት -መግዛት መገዛት፤ አገዛዝ ግዙነት ግዛት ይዘታ ርስት ልት ስመ ሙንቱ ቅኑያቱ ወምልክናሁ ወግዝአት ሎቱ ሐዱ ዝአት -(ቅዳ -ሕር አዋል)

(ኣት)         ግዝእ -ጋሬዳ ድግስ መሰናዶ ፍሪዳ ያለበት የመብል የመጠጥ የምሳ በዓል ወገብረ ግዝአ ዐቢየ ቤተ ግዝእ መዋዕለ ግዝእ -(ኩፋ -፲፯ መክ፯ -፪። ኢዮ፩ -)

ግዝፈት -መግዘፍ መወፈር አወፋፈር ወፍራምነት ውፈራ ወፍር ውፋሬ ድንዳኔ በግዝፈተ ልብከ በግዝፈተ ክሣድከ -(መቃ -ገ፮ ፲፬። ስንክ -ታኅ፮) .

ግዝፍ ግዘፍ -ቁሙ ወፍር ድንዳኔ። ግዝፈ ምድር ዝፈ ልብ ዘፈ ደመናት ግዘፈ ዕፅ ግዘፊሆን ለአልባቢከ -(መዝ ፻፵ አርጋ - -፩። ሕዝ፵፩ -፳፭ ዮሴፍ)

ግዩር -ግዩር፤ -(ዕብ ጌር ሱር ጊዮራ) መጤ መጣተኛ ስደተኛ ካገሩ ሕጉ የፈለሰ ፈላሻ የአይሁድ ጥገኛ በኦሪት ያመነ ግዙር አሐዱ ሕግ ይኩን ለክ ወለግዩር ዘማእከሌክሙ ግዩራን ወፈላስያን -(ዘፀ፲፪ -፵፱። ዘሌ፳፭ -፳፫)

 -የተለሰነ ልስን ቅብ ልቅልቅ

ግያሬ -ኖራ አወጣጥ አለላለን ልቅለቃ

ግይርና -ስደት ስደተኛነት ፈላሽነት -(አርጋ)

ግዮን [1]-(ጽር ጌዖን። ጊሖን) ስመ ፈለግ ካራቱ በበይት አፍላጋት ኹለተኛው ወንዝ ነጭ ባይ ከአፍሪቃ ደቡብ ተነሥቶ ወደ ሜን ወደ  ሱዳን አገር የሚፈስ -(ዘፍ፪ -፲፫) ነቁን ባለጊዎግራፎች ያኽል ነው ይሉታል ውሃው ነጭ ኒል ስለ መሰለ ነጭ አባይ ይባላል፤ አባይን ፍች ተመልከት። ጊሖን ማለት ግን ዘየሐውር በኀይል ወይርዕም ወድምፀ ማዩ ዐቢይም ወግሩም ማለት ነው የውሃውን ብዛት የመልካውን ስፋት ያካኼዱን ኀይል የጩኸቱን ግርማ ፏፏቴውንና ተመማውን ድምጡ እንደ ነጐድጓድ መኾኑን ያሳያል ከአፍሪቃ ወንዞች ተለይተው ነጭ ኒል ጥቍር ኒል የሚመስሉ ኦሪትም ግዮን ኤፌሶን የሚባሉ ነጭ አባይና ጥቍር አባይ ናቸው ይባላል። እሊህም ኹለቱ ወንድማማች ወንዞች ከየምንጮቻቸው  በኀይል ተነሥተው ግርማቸውን ለብሰው ተሰልፈው በየፊታቸው ያለውን ሐይቅ እንደ መርከብ ሠንጥቀው ልፈው ራዊታቸውን ከግራና ቀኝ አስከትለው እንደ ኹለት ንጉሥ ርቱም ሲገናኙ ኹለትነታቸው ይቀርና ንድ ወንዝ ብቻ ይኾናሉ ከክርቱም ደግሞ እስካትበራ ወርደው ተከዚ ጋራ ይገጥማሉ ከዚያ በኋላ ግን የሌላ ወንዝ ውሃ ሳይጨምሩ ባንድነት መላ ምድረ ግብጽን ላይ እስከ ታች አጠጥተው አጥግበው አርክተው ዐልፈው ተርፈው ወደ  ስሜን ጐርፈው ሜዲተራኒ ሚባለው ታላቁ ባሕር ይገባሉ።

 [2]-የየሩሳሌም ወንዝ ሊሖም ሎሞን የነገሠበት ከከተማዪቱ በስተደቡብ ያለ -(፫ነገ - -፴፫። ኢሳ፰ -)

ግደት -መገደድ፤ ማስገደድ፤ ግዴታ ግድ ግዳጅ፤ ጥናት ብርታት። እመ ወድቀ ብሑት ውስተ እከይ እመ በእንተ ድካመ ሥጋ በእንተ ደተ ገድል -(ፊልክ -)

ግዱል -(ላን ላት ድልት) የተገደለ የተጣለ ገደል የገባ

()          ግዱድ -(ዕብ ግዱድ ወራሪ ዘራፊ) በግድ የተያዘ ወይም የሚይዝ የሚያስገድድ ካኝ ወንበዴ ሽፍታ። ወኀይላኒ ብእሲ ዱድ -(ሆሴ፮ -)

 -የባሰ የጸና የበረታ ብርቱ። እስመ ጢአቶሙ ቢይ ወግዱድ በኀበ እግዚ -(ቄድር)

ግዱፍ -(ፋን ፋት ድፍት) የተገደፈ የተጣለ የወደቀ የተኛ የተጋደመ የጠፋ የታጣ፤ የረከሰ የተናቀ። ከመ ፀፍዕ ዱፍ ማሁ ሀካይ በኀበ ሰከበ ረከበ ቢድኖ ዱፈ ውስተ ምድር። ዱፍ ውስተ ዴዴሁ። ዱፋነ ይርከብ ኵሉ ተግባረ እግ ሠናይ ወአልቦ ዱፍ ወኢምንትኒ -(ሢራ፳፪ - ዮዲ፲፬ -፲፭ ሉቃ፲፮ -፳። ኪዳ ጢሞ - -)

ግዳሜ -ጋድም፤ የመስቀል ክንፍ። በትረ ርካዕ ዕፀ መስቀል ወበትረ ለውዝ ይትሜሰል በግዳሜሁ -(መጽ -ምስ ኤር፩ -፲፩)

ግድ -በቁሙ ውድና ፈቃድ የሌለበት መጽሐፍ ግን በግድ ፈንታ ግዱድ ይላል ያሰኝም። አዘዘ ይጥዐምዎ በግዱድ -(ግንዘ)

ግድም -( ግደም ግድማት) በቁሙ፤ አግድሞ፤ ወርድ ስፋት መኒ ሖርክሙ ድመ አነኒ ሐውር ግድመ ምስሌክሙ። ወግድሙ ስድስቱ በእመት ልብነ ኑኅ ወግድም። ኢይትአመር ኑኃ ወግድማ ወኢቆማ ምግደሚሁ ደብተራ -(ዘሌ፳፮ -፳፩፳፬። ዳን፫ -፩። ቀሌ ዘፀ፳፮ -፲፫)

ግድዓ እንግድዓ -(ዓት) ደረት እንቢያ ፍርእንቢያእን ምልአተ ንባብ ነው ከአንጐድጐደ መጥቷል ግድዓ ደረት በሐዘን ጊዜ የሚመታ የሚደሰቅ ድጕዓን እይ ንግድዓሁ ዘብሩር። ልብሰ እንግድዓ በጐዲዐ ንግድዓ ንጕዳዕ ንግድዓቲነ ምኔከ ስመ ኬድከ በሰኩናከ ንግድዓቲሆሙ ካህናት -(ዳን፪ -፴፪። ዘፀ፳፰ -፬። -ተ፳፯ ልክ -፻፲ ግንዘ) ልብ ሆድ ትዕግሥት አእምሮ። ሑሪ በእንግድዓኪ። ጸቢበ ንግድዓ በግዕዙ ይጸልእዎ ሰብእ። ጥሪ ዕግሥተ ወርሕበተ እንግድዓ እሲ ድኩመ ኅሊና ወጸቢበ እንግድዓ ብድ ውእቱ -(ዘፍ፫ -፲፬። ፈላስ -ገ፶፮ ፶፯። አፈ -ተ፲፱)

ግድፈት -በቁሙ መግደፍ መጣል፤ መገደፍ አገዳደፍ ገደፋ ርሳታ  ዝንጋታ ገዳፍነት ግድፈተ ቃል -( - -መጨረሻው)

ግጋጼ -ማፈግፈግ፤ ፍረት ፍርሀት ድንጋጤ ሽሽት ቀርበት መዊት እንበለ ጋጼ ማዕታተ ርስቶስ እንበለ ግጋጼ -(ዮሴፍ። ስንክ -ነሐ፲)

ግግጽና -ዝኒ ማሁ፤ አፈግፋጊነት። ሖረ ምስሌሆሙ እንበለ ግግጽና -(ስንክ -ሚያ፪)

ግጻዌ [1]-መታየት መገለጥ፤ መታወቅ መረዳት፤ ባለሟልነት ትርጓሜ አፈታት። በከመ ደለዎ ጻዌ ዮሐንስአእምሮትከ ዘመልዕልተ ኵሉ ጻዌ ግጻዌ ትምህርተ ሕግ ወሥርዐት ወተግሣጽ ግጻዌ ድርሳን ዘቅዱስ ቄርሎስ ሐዱ ክርስቶስ -(ፊልክ። ጥበ -ጠቢ ኖዶ ቄር -ጰላ) ባለመጣፎች ግን ግጽው ብለው በቅጽል አፈታት ይፈቱታል

[2]-ግጽው ባብ መጣፍ እንደ ድጓ ካመት እስካ የተሠራ፤ በጸሎት በቅዳሴ ጊዜ የሚነበብ ቃሉ ለዘመን ለበዓል የሚማማ ብሉይ ከሐዲስ የወጣ። መጽሐፈ መቃርስ መጻሕፍተ ዌ። በውስተ ግጻ -( -መስ፲ ኅዳ፲፯ ግን፲፪)

[3]-ግጻዌ ገጽ ያለው አካል ህላዌ። ነአምን በአካሉ ወበግጻዌሁ ዘኢይትፈለጥ ምከዊነ ከዊነ ወልድ።አቀመ ጻዌ ባሕቲቶ በአ መን በሥላሴ ወተጋነይ በግጻዌ መለኮት። በስመ ጻዌ ሠላስ ዕሩያነ ብር ወንግሥ አሐዱ ውእቱ ዘበሠለስቱ ጻዌ -(አትና። መጽ -ምስ አዋል ቅዳ -ሕር)

ግጽው -(ዋን ዋት ጹት) የታየ የተገለጠ፤ ግልጥ ልሕ ፊት ለፊት ያለ ሥዕል ምስል፤ ባለሟል ግጽው መንገለ ሰሜን ሊተ ግጽው ቅድመ ዕይንትየ የሱስ -(መጽ -ምስ)

 -የመጽሐፍ ስም ሐዋርያት ሲኖዶስ አንዱ ክፍል። ፍትሐ ነገሥት ረስጠብ ይለዋል፤ ሐዋርያት ቀሌምንጦስ የሰጡት ኹለተኛ መጽሐፍ ማለት ነው ግጽው ወሥርዐት ወአብጥሊስ -(ሲኖዶ)

ግፉዕ -(ዓን ዓት ፍዕት) ቁሙ የተገፋ የተበደለ የተጠቃ ውያተ ፉዕ ድኅኑ ፉዐ ሰብእ ግፉዓን -(ሢራ፴፪ -፲፮ ኢሳ፩ -፲፯። ፳፭ -)

ግፍቱዕ -(ዓን ዓት ትዕት) የተለወጠ የተገለበጠ ልውጥ ግልብጥ፤ ጠማማ ልማማ ይወፅእ ሕግ ፍቱዐ ትውልድ ዕሉት ወግፍትዕት ፍቱዓነ ልብ ዐላውያን ወግፍቱዓን -(ዕን፩ -፬። ዘዳ፴፪ -፭። ሔኖ፻ -፰። ፊልጵ፪ -፲፭)

ግፍታዔ -መገልበጥ መደፋት መፍረስ ሥራዌ ጥፋት። ወአውፅኦ ማእከለ ፍታዔ ግፍታዔ ሰዶም -(ኩፋ -፲፮። መጽ -ምስ)

ግፍዐት -መግፋት መገፋት፤ አገፋፍ።

ግፍዕ -(ዓት) ቁሙ፤ ግፍ በደል ቅሚያ ሕገ ወጥ ሥራ፤ ስድብ መከራ። ዐመፃ ወግፍዕ ከመ ትግበሩ ዕሌነ ዐቢየ ፍዐ ወባሕቱ እነግረከ ግፍዐከ ተዐገሥክሙ ፍዐክሙ -(ኩፋ -፴፭ ዮዲ፯ -፳፬ ኢዮ፴፫ -፰። ጴጥ -)

ጎሀ -ነጋ በራ ገዊሕ ጎሐ

ጐሓሊ -(ሊት ልያን ያት ሐልት) ሕልያ -(ያት) ክፉ ድራጊ ሌባ ቀጣፊ ዳንዴ ወንበዴ ቀማኛ የቀን ወራሪ የሌት ሰባሪ ቤት አቃጣይ ነፍሰ ዳይ ሒላ እንዲል -(ትግሬ) መጽሐፍ ግን ሰራቂ -ወጕሕልያ ሰረቅት ወጕሕልያ እያለ እንደ ፀር እንደ ቢጽ ንድም ብዙም ያደርገዋል የጣፊ ሕተት ነው -(፪ጢሞ - -፱። ዮሐ፲ - -፰። ዐብድ -፭። ስንክ -ኅዳ፲፪)

ጐሃኒ -(ኒት ንያን ያት፤ ሀንት) የሚሰውር ደባቂ የሚጕን፤ የሚያጕን

ጐሐየ -(ዐረ -ጀሓ) ዐረመ፤ ነቀለ መነገለ አፈለሰ

ጎህ -ወገግታገዊሕ ጎሐ ጎሕ

ጎሕ -ወገግታ ውጋጋን ፈገገን የንጋት ብርሃን ጽባሕ በፊት የሚታይ ያጥቢያ ኮከብ መን ነግህ ጽባሕ እንዲቀድም ጽባሕ ደግሞ ጎሕ ይቀድማል፤ ጨርሶ  እስኪታይ ይባላል ታየ በኋ ፀሓይ ስክቶጣ ጽባሕ ይባላል ነግህ ዚያ በኋላ ነው። የሦስቱ ኹሉ ዘራቸውና አንቀጻቸው የተለየ ነው ሶበ ርገ እምጊዜ የዐርግ ሕ። ከመ ድልው ወሊደ ፀሓይ ርእየ ጎሕ ወኢርእየ ጽባሐ -(መሳ፲፱ -፳፭። ነሐ፬ -፳፩ አርጋ -፪። )

ጐሊሕ ሖት -(ጐልሐ ይጐልሕ ይጕላሕ ጋሌሕ ትግ ገልሔ ላጨ) መጕላት መግዘፍ መታየት መገለጥ፤ እንደ ልጩ ራስ መኾን። የጥፈት የሥ የመልክአ ፊደል የነገር የምስጢር የድምፅ የቃል

ጐሊም ሞት -(ጐለመ ይጐልም ይጕልም ዕብ ጎሌም) መጐለም፤ ጕልማ መስጠት መጐልመስ ማደግ፤ መጐላመም ጐልማማ ባለጕልማ መኾን ጐለም እንዲሉ ጐልማሜ ሲሉ።

ጐላቲ -(ቲት ትያን ያት) የሚጐልት ጐላች፤ ሰጭ አውራሽ። ወለእመ ፈቀደ ጐላ ይሠየም ዲበ ዘጐለተ -( - -፲፰)

ጎላት -መንቀሎችጐልሎ ጐለለ።

ጎል [1]-( አግዋል ላት) በረት የከብቶች ማደሪያ መታጐሪያ። ወአልሕምትኒ ይትረከቡ በውስተ ጎል። አግዋላት ለእንስሳሁ -(ዕን፫ -፲፯ ፪ዜና -፴፪ -፳፰)

[2]-(ዐረ ማዝወድ። ዕብ ኤቡስ) ግርግም፤ በዚያው በበረቱ ውስጥ ዙሪያውን ወይም ባንድ ወገን እንደ ገንዳ ኹኖ የሚሠራ የእንስሳት ማእድ ገለባ ደፈጫ የሚቅሙበት አስከበቶ እሙ ውስተ ጎለ እብን በጎለ እንስሳ ተወድየ -(ድጓ። ቅዳ -ዲዮ) በግርግም ውስጥ ማለት ነው።

[3]-(ዐረ ማዝወድ። ዕብ ኤቡስ) ግርግም፤ በዚያው በበረቱ ውስጥ ዙሪያውን ወይም ባንድ ወገን እንደ ገንዳ ኹኖ የሚሠራ የእንስሳት ማእድ ገለባ ደፈጫ የሚቅሙበት አስከበቶ እሙ ውስተ ጎለ እብን በጎለ እንስሳ ተወድየ -(ድጓ። ቅዳ -ዲዮ) በግርግም ውስጥ ማለት ነው።

ጐልሎ ሎት -(ጐለለ ይጔልል ይጐልል) መጐለል፤ በቤት ራስና በጕልቻ ላይ ማስቀመጥ ማኖር፤ መጣድ ማስረር

ጐልበተ -(ትግ ገልበተ ገለበጠ) ቁሙ ጐለበተ ልበታም ኾነ የለ በረታ -(ዐማርኛ)

ጐልቶ  ቶት -(ጐለተ ይጔልት ይጐልት) መጐለት መትከል የጕልቻ ማውረስ መስጠት የገንዘብ የርስት ይጐልቶሙ ለአብያተ ርስቲያናት። በጊዜ ጐልቶቱ ወለእመ ለተ ትሰድ -(ስንክ -ጥር፳፫። - -፲፰ ፳፬ -)

ጎልጎል [1]-(ዕብ ጊልጋል) ሀገር -(ዘዳ፲፩ -)

 [2]-(ዕብ ጉልጎሌት) የራስ ቅል የራስ ዐጥንት መላው ካንገት በላይ ያለው። ናላን አንጎል ማለት ዚህ የወጣ ነው።

ጎልጎታ -(ዕብ ጎልጎልታ) መካነ ርእስ መካነ ድማኅ ይችውም የአዳም ራስ ቅል የተቀበረባት ዳግማይ ዳም የተሰቀለባት ቀራንዮ ናት -(ዮሐ፲፱ -፲፯)

ጐልጐታ -ጎልጎታገዊል ጎለ፤ ጎል

ጐሚት -ታላቅ ጐምቱ እባብ ዐይጥ የሚውጥ የሚሰለቅጥ ባላገሮች ጐሚት ገና የሚሉት

ጐሜእ -(ዕብራ) ስመ ዕፅ በግብጽ ወንዝ ዳር የሚበቅል፤ ውስጠ ክፍት የሸንበቆ የቀርክሓ ይነት ታንኳ ፍልኳ የሚኾን ንዋየ ሜእ -(ኢሳ፲፰ -)

ጐምር -ቁሙ የበሰለ የደረሰ እሸትነቱን የጨረሰ -(ዐማርኛ)

ጐሞር ጎሞር -(ጽርእ። ዕብ ሜር) ታናሽ ልክ የኽል መስፈሪያ እንደ ድርጎና እንደ ልቢጥ እንደ ቈለምሸሽ ያለች የኢፍን ካሥር አንድ የምቲዝ -(ዘፀ፲፮ -፲፰) ኢፍን እይ

ጐሢዕ  ዖት -(ጐሥዐ ይጐሥዕ ይጕሣዕ ዐረ ጀሸአ ጀሸዐ ሱር ግሣእ። ጋሣህ ጋዓህ) መግሣት ማግሣት መጮኽ፤ አፍን መክፈት፤ መትፋት መቀርሸት ማለት፤ የጠብ የጥጋብ። -(ግጥም) ሚጣቅ እሾላው ሥር ዐማኔል ቢያገሣ በሽታዬ ኹሉ እክቱን ነሣ። ቀወ ዶርሆከ ወጐሥዐ ሶረ ብዕራይከ ህየ በር። ወእጐሥዕ ምሐዘነ ልብየ ኵሉ ዘይጐሥዕ ማይ -(ታሪ -ነገ መዝ -፴፯። ሌ፲፩ -)

 -መናገር፤ ኀይለ ቃል ማውጣት ደፍሮ ተራቆ፤ የክፉ የበጎ የድርስት የትንቢት እለ ይጐሥዑ በእንቲኣየ ቃላተ መፃ ዕለ ለዕለ ትጐሥዕ ነቢበ ጐሥዐ ልብየ ቃለ ሠናየ ወጐሥዐ ልብየ ጥቀ ጥበበ ዘጐሥዐ መጻሕፍተ ጥበብ -(ተረ -ር፲፭ መዝ -፲፰ ፵፬። ሱቱ -ዕዝ፲፬ -፵፪። ንክ -የካ፲)

 -መፍላት፤ መገንፈል፤ መልቶ ተርፎ መፍሰስ። መንፈስ ቅዱስ ይጐሥ ውስተ ልቡ በከመ ይጐሥዑ ፍላጋት ወይውሕዙ እምነ ሐዋርያት ጐሥዐ መንፈስ ቅዱስ ላዕለ ሎሙ ቅዱሳን መሀይምናን -(ስንክ -የካ፲ ጥቅ፳፩)

ጐሪጽ ጾት -(ጐረጸ ይጐርጽ ይጕርጽ) ብጣት መፍቃት መቍረጥ መሠንበጥ፤ መውጋት መጋረጥ፤ መሰርሰር መንደፍ ደም ለማውጣት የግንባር ያፍንጫ ማጕረጥ ማፍጠጥ ያይን ርጥ ጐረጥ ማለት ዚህ ወጥቷል

ጐሪፍ ፎት -(ጐረፈ ይጐርፍ ይጕርፍ) በቁሙ መጕረፍ መፍሰስ።

ጎሬም -( ጎራይም) ጋሚ ሐኪም ባለዋገምት። ማገሚያ ዋገምት የቀንድ የብርጭቆ

ጎር -(ዐረ ዕብ ሽኼን) ጓሮ የቤት ኋላ በቁሙ ጎረ ቤት ቤቱ የቤት ቅርብ ጐን ሕፅን  አጠገብ የኾነ የርስት የመሬት የቦታ አዋሳኝ ደንበረተኛ በዙሪያ ለቅርብ ኹሉ ይነገራል። ካልእ ዘጎሩ ወቤቱ ምኵራብ በኀበ ጎርየ ጎር ኩይ እለ ይገስሱ ርስትየ ወቦ ዐጸደ ሐምል ቤቱ -(ዘፀ፲፪ -፬። ግብ፲፰ -፯። መዝ - ኤር፲፪ -፲፬። ዳን፩ -)

 -ጎረ ቤትገወረ

ጐርዐየ -(ተቀ ) ዐነቀ ፈጠረቀ ረሮ ያዘ ጐርጐረን እይ

ጎርየመ [1]-(ይጎረይም ይጎሪም) ዐገመ ዐከመ ጠባ ሳበ መጠመጠ፤ ደምን እንደ ወተት ለማውጣት ሐገመን እይ

 [2]-ዐገመጉር ገወረ።

ጐርጐረ -(ዕብ፤ ጋርጌር) ቁሙ ረጐረ፤ ጓጐጠ ነካ ቋቅ  አለ ለማስመለስ የጕረሮ። ረሮ ቅሉ ዚህ ወጥቷል የዚህ ዘር ነው በረበረ አጥብቆ ፈለገ ለማግኘት። -(ተረት) ዓሣ ጐርጓሪ ንዶ ያወጣል የሰው ፈላጊ የራሱን ያጣል ጐርጐረ ካማርኛ በቀር በግእዝ ቃላት ውስጥ አለልማድ አይነገርም።

ጐኒድ ዶት -(ጐነደ ይጐንድ ይጕንድ) መጐነድ ንድ ጐናዴ መኾን ጐዦ ውጣት፤ ለብቻ መቆም መተክል ራስን መቻል፤ መወፈር መደንይን፤ የዛፍ የሰው።

ጐናኵ -(ኵት ያን ያት) ሰብሳቢ ሰንዳቂ ከማ ቈላይ ተሸካሚ።

ጎን [1]-(ዕብራ) መልክ ሕብር ይነት፤ አንጻር አርኣያ ምሳል። በቁሙ ጐን ገቦ -(ዐማርኛ)

 [2]-መልክ፤ገወን

ጐንኮ  ኮት -(ጐነኰ ንኵ ይጐንኵ) መሰብሰብ፤ መጐቸት መሰንደቅ፤ መከመር መቈለል ቤት ማስመሰል ወይም እያሰሩ መሸከም መደብለል የነዶ የሣር። ያክይዱ ወይነ ወይጔንኩ ከላስስተ በዕለተ ሰንበት -(ነሐ፲፫ -፲፭)

ጐንደር -ንደ ሀገር የፋሲል ተማ ግራኝ በኋላ የቀናች ባላ፵፬ ደብር፤ ዳግም ግራኝና ልስ ግራኝ -(ቴዎ -ደር) ተከታትለው እስኪያጠፏት ድረስ መናገሻ ታላቅ መዲና የነበረች።

ጐንደየ -(ተቀ ) ቈየ ዘገየ ነበተ ሥር ያዘ ቀረ ወደ ኋላ አለ ኖረ ተቀመጠ ጐንደየ እን ይጐደጕድ ይጐነዲ ዋዩ ወልድየሰ ሞተ ወበእንተ ንደየኢትጐንዲ ውስተ መካና ጐንደዩ አንጾኪያ። ከመ ይጐንዲ ውስተ ስያ -(ግብ፲፪ -፲፮ ኢዮ፲፭ -፳፱ ጦቢ፲ -፩። ምሳ፱ -፲፰ ግብ፲፭ -፴፭። ፲፮) በጐንደየ ፈንታ ጐናደየ ይላል። ኢትትጐናደይ ዕለ ገቢረ ሠናይ ኢመፍትው ትጐናደይ ተጠምቆ ሶበ ተጐናደየ ሞተ በሁ ፈቀደ ይቅትሎ -(ፈላስ አፈ -ተ፲፫ ዮሴፍ)

ጐዕተየ -አሞኘ አታለለ ተሞኘ ታለለ።

ጐዝጐዘ -(ዐማርኛ ገለደ ነጸፈ) በቁሙ፤ ጐዘጐዘ አነጠፈ፤ አመቻቸ።

ጐዝጐዝ -( ጐዛጕዝ ዛት) ልጋ በቁሙ ጕዝጓዝ ሰርፍ ስጋጃ ምንጣፍ የሌት ልብስ ለሐፍ አምጽኡ ዐሠርተ ዐራታተ ወጐዛጕዛተ -(፪ነገ -፲፯ -፳፪)

ጐየጸ -(የጌገየና የጐየ ጎር) ለቀቀ፤ የሕፃን የድውይ ሸሸ አመለጠ ያይነ ምድር ፈስ ሽሽ እንዲሉ ፈሰወን ተመልክት።

-(ዪት ይያን ያት የይት) የሚሸሽ ሸሽታ ብላይ ፈሪ ደንባሪ፤ ሯጭ ፈርጣጭ ዐመለኛ። ጐያዬ ዊኖ ብእሲ ያዪ እንስሳ ያዪ -(ቄር - -፳፫ -፬። - -፴፫ -፫። )

ጐይ ዕብ ጎይ -ሕዝብ አገርና ያንድ መንግሥት ቋንቋውና ሕጉ ንድ የኾነ ሲያበዛ ጎይም ይላል አሕዛብ ማለት ነው፤ ጐይይ ማለት ዚህ ሥር ወጥቷል።

ጐይይ ዮት -(ጐየ ጐየየ ይጐይይ ይጕየይ ዕብ ጎይ፤ ሕዝብ) መሸሽ መኰብለል። መራቅ መሰደድ ካሉበት ከነበሩበት መጥፋት መታጣት፤ ወደ ሌላ ሕዝብ መኬድ መጠጋት ሕግን ባንዲራን መለወጥ ሌላ ሕዝብ መኾን መባል። ፈለሰን እይ የዚህ ጎር ነው ምገጸ ዔላው። ዘይጐይይ ምአርዌ ኩይ ማሁ የይ እምኀጢአት ጕዩ ማእከለ ባቢሎን ወአይቴ እጐይይ ምቅድመ ጽከ የይ ብሔረ ግብጽ -(ኩፋ -፴፩። ራ፳፩ - ኤር፳፰ -፮። መዝ ፻፴፰ ማቴ፪ -፲፫ -፳፫)

ጐደላዊ -(ዊት ውያን ያት) ዝኒ ከማሁ ያነሰው የጐደለው ጐደላውያን እምውስተ ትምህርት ዘበንተ አእምሮ ወጽን ወሙቀተ ፍቅር። ጐደላውያን ሕነ ምአበው -(ፊልክ -፵፭። ፪፻፲፯)

ጐደሎ -በቁሙ፤ ጕዱል ያነሰ የጐደለ ሕጹጽ። ዘርቱዐ ግዕ ወሥርዐቱ ጐደሎ እንተ ኅላኄ ኅሊናሁ -(ፊልክ -)

ጐደዳ -(ዐማርኛ) ያዛባ የኵበት ጠገራ ባድ ጥፍጥፍ ማገድ ከእሳት ዋሐ የሚጓደድ ርቱ ጠንካራ -(ተረት) ሆድ ያስበላል ጐደዳ

ጐደፈ -በቁሙ፤ አደፈ ተኵለፈለፈ እድፋም ድፋም -(ዐማርኛ)

ጐዲል ሎት -(ጐደለ ይጐድል ድል ዐማርኛ) ጺጽ ነቲግ ንኢስ መጕደል ማነስ፤ ሕጹጽ መኾን ለእ ኮነ ምግባራቲከ ሕጽጽተ ምጸብአ ሰይጣናት አላ ኅሊናከሰ ርት ወኢጐደለ -(ፊልክ -፵፯ ፶፬)

ጐዲብ ቦት -(ጐደበ ይጐድብ ይጕድብ) መጐደብ ማረድ መቈፈር ማጐድጐድ፤ መቍረጥ የመሬት። መመንደብ መጕረድ መጕመድ መጨፍጨፍ መመንጠር መለበድ ካንቻ መምታት የንጨት መገደብ መወደብ፤ መክተር ማገድ የውሃ። የሦስቱ ኹሉ ስልት አንድ ነው ምስጢሩ መቍረጥ አይወጣም ገዘመንና ገመድን ይመስላል አንቀጹ ካማርኛ በቀር በግእዝ ቃላት አይገኝም።

ጐዲዕ ዖት -(ጐድዐ ይጐድ ይጕዳዕ። ዕብ ጋዳ) መጕዳት መንካት መጐነጥ መምታት መደሰቅ፤ መሰባበር ማድቀቅ። መውጋት፤ መውገጥ መለጥልጥ። ጐድዖ ገቦሁ። ጐዳዐ እንግድዓሁ ጐድዖ ነፋስ ለቤት ለሊ ትጐድዕ ወለሊ ትኬልሕ አኀ ይጕድዖሙ ልኩ አባግዕ።ኢይጐድዖ ይነ ኩይ። ቅበ ንሒጕ ንጕዳዕ ወጐድዑ በተባርዮ -(ግብ፲፪ - ሉቃ፲፰ -፲፫። ፳፫ -፵፰ ኢዮ፩ -፲፱ ራ፲፫ -፪። ሔኖ፹፭ -፬። ደራሲ ድር -መድ)

ጐዲድ ዶት -(ጐደ ጐደደ ይጐድድ ይጕድድ) መጓደድ መቈነን ያካኼድ ያረማመድ የታቦት የዑደት

ጐዳና ጐድን -(ዐማርኛ) ቁሙ፤ ውራ መንገድ ገቦ ዐፅመ ገቦ

ጐዳዒ -(ዒት ዕያን ያት) ሚጐዳ የሚነካ ዳት የሚያመጣ።

ጎድ [1]-ኀይልገወድ

 [2]-(የግዱድ ከፊል) ኀይል ራዊት ይመጽእ በጎድ -(መቃ) ንግሊዝ ቋንቋ ግን አምላክ ማለት ነው።

ጐድአ -መታ ደሰቀጐዲዕ ጐድዐ

ጐድጐደ [1]-(ጐዲዕ ጐድዐ) ደጅ መታ ቀበቀበ እጅ ጸፋ አጨበጨበ፤ ለማስከፈት። ግስነቱ ጐዲዕና ገዲድ ኹለቱ የተዴቀለ ነው ሶበ ጐድጐደ ኅተ ሥአ እብነ ወጐድጐደ ንቀጸ ቦአ ወጐድጐደ በኀበ ዐጸድ ዘቅድመ ደብተራ። ወለዘኒ ድጐደ ይትረኀዎ -(ፊልክ -፶፭። ስንክ የካ፪ ዮዲ፲፬ -፲፬ ማቴ፯ -)

 [2]-ተተ ቤት ከጓዳ ከጕድጓድ አገባ። ጐደጐደ ጕድጓድ ኾነ -(ዐማርኛ)

ጐጕኦ ኦት -(ጐጕአ ይጔጕእ ይጐጕእ መጓጓት መመኘት ተስፋ ማድረግ፤ መሠየት መጐምዠት ዚህ የተነሣ ቸኰል መጣደፍ መፍጠን መቀልጠፍ መጣር መፍጨርጨር መትጋት። ጉጕአ ከመ ይፃእ እምህየ ጐጕአ ይዕርግ ይጔጕእ ዘተነድፈ ይምላኅ ሐጸ እስመ ዘይጔጕእ ወይሰርሕ። ይጔጕእ ይብዐል -(፪ዜና -፳፮ - -፲፰ ሢራ፲፱ -፲፪። ፲፩ -፲፩ ምሳ፳፰ -፳፪ ፪ጴጥ - -፲፭ -፲፬)

ጎግ -ጎግ፤ ሰራዊት መንጋ በዝቶ የሚኼድ የሚንጋጋ

ጎግ ማጎግ -ጎግ ሀገር ማጎጋውያን የወረሱት -(ቃውቃዝ) ማጎግ ስመ ነገድ የያፌት ልጅ፤ የመስኮቦች አባት -(ሕዝ፵፰ -፪። ራእ፳ -፰። ዘፍ፲ -) ኹለተኛም ብዙ ማጎግ የብዙ ብዙ ወይም ጎግ ጀርመን ማጎግ መስኮብ ይባላል ምስጢሩ ብዛት ነው። አይሁድ ግን ኦሪት ዘዳግም -(፴፪ - -) አያይዘው ቋንቋ ነገድ ብለው በፊደል ጥር ይፈቱታል አፈታታቸውም እንዲህ ነው ሳብዕ መኾኑ ወን ጐርዶ ነውና ሲጥፉ ገወግ ማገወግ ሲያነቡ ግን እንደኛ ጎግ ማጎግ ይሉታል። ገወግ ፲፪ ማገወግ ፶፪ -፷፬። በዚህ ላይ ደግሞ ገወግ ማገወግ ብለው ነጠላ ጥር ይቈጥሩና ከ፷፬ ጋራ ሲገጥሙት ፸፩ ይኾናል። ፸ው ወይም ፸፩ አሕዛብ ፸፪ኛው እስራኤል ይላሉ ይህ ደግሞ -(ዘፍ፩ -፳፰) ብዝኁ ወተባዝኁ ወምልእዋ ምድር ያለውን ያዳምን ዘር ኹሉ ያሳያል

ጎግዎ  ዎት -(ጎገወ ይጎጉ ይጎጉ ገዊግ) መሳት መሳሳት ሕግ ሥርዐት መንገድ መውጣት፤ ከጽድቅ መራቅ። ጌገየንና ሳኰየን ጠዐወን እይ የዚህ ጎሮች ናቸው

 -መንጋጋት መርባት መብዛት መንጋ መኾን፤ የሰው የከብት መንጋ ማለት ቅሉ ዚህ ወጥቷል

ጐጓኢ -(ኢት እያን ያት) የሚቸኵል ቸኳይ አንተ ብእሲ ጐጓኢ -(ሄርማ)

ጐጣዪ -(ዪት ይያን ያት) ሚወጋ የሚጓጕጥ የሚያጣብቅ የሚቈነጥጥ።

ጐጥ ጕጥ -በቁሙ ባጣ ሸካራ፤ የምድር የመሬት፤ የበትር የንጨት ለእጅም ይኾናል እጄ አወጣ እንዲሉ

ጐጥይ ዮት -(ጐጠየ ይጐጢ ይጕጢመጓጐጥ መጐጥጐጥ መሠቅሠቅ መቈፈር  መሰርሰር ውጋት መትከል። ማጣበቅ መቈንጠር አጣብቆ መያዝ።

ጐጻጕጽ -(ጻት) ጐጣጕጥ ሥርጥ ዐባጣ ጐባጣ ንከልካላ። ፍኖት ንተ ልባቲ ማዕቅፍ ወአሥዋክ ወጐጻጕጽ ወአጽዳፍ። ብነ ዝየ ሀገር ጽዳፍ ወጐጻጕጽ -(ሲኖዶ ቅዳ -አትና) ,

ጐጽፈረ -(ዲቃ ደጐጸ ጸፈረ) ጐደፈረ ማሰ ፈረ ሟጨ ጐፈጨረ ያውሬ ዐከከ ፎከተ የሰው የደጐጸና የጸፈረ ዘር ነው

ጎፍ [1]-(ትግ ዕብ ጉፍ) ህላዌ ባይዕ ገላ ግዘፍ፤ ሥጋ የሚታይና የሚዳሰስ ማናቸውም ግዙፍ ነገር ኹሉ ገፋፋ ጐፋፋ ፋያ ማለት ከዚህ ወጥቷል።

 [2]-ሀላዌገወፍ

-(ንኡስ አገባብ) እኮን ቢያ እንኳ ስንኳ። አንተሂጓ ተሠገርከ ማነ አንተስጓ ሀሎከ ምስሌየ ከለባትኒጓ -(ኢሳ፲፬ -፲። ሉቃ፲፭ -፴፩። ፊልክ -፫። ማቴ፲፭ ፳፯)

ጓሕለወ -(ይጓሐሉ ይጓሕሉ) ሸነገለ አታለለ ዋሸ ዐበለ ተተነኰለ ወዘኢጓሕለወ በልሳኑ ወጓሕለዉ በልሳናቲሆሙ -(መዝ፲፬ -፫። ሮሜ፫ -፲፫) ብዙ መጽሐፍ ግን በጓሕለወ ፈንታ ተጓሕለወ ይላል -(ዘኍ፳፭ -፲፰ - -፳፱ -፴፮) ሐውርኑ በተጓሕልዎ ወበተጠብቦ -(ዮሴፍ)

ጓሕላዊ -(ዊት ውያን ያት) የሚነግል የሚያታልል፤ ሸንጋይ አታላይ ዋሾ ባይ ዐላዊ ከዳተኛ ተንኰለኛ -(አፈ -ተ፳፫) መጽሐፍ ግን በጓሕላዊ ፈንታ ሕልያ እንደ ማለት ሕላዊ ይላል አያሰኝም። ብእሴ ደም ወጕሕላዊ ስመ ውእቱ ብእሲ ሕላዊ ሰይጣን ሐሳዊ ወጕሕላዊ ኩያን ወጕሕላውያን ኖሎት -(መዝ -፭። ዮሴፍ - -፳፫ -፩። ዲድ -፮። ሮሜ፩ -፳፱) ፪ኛም በጓሕላዊ ፈንታ ሕልው ይላል፤ ስሕተት ነው መስተመይናን ወጕሕልዋን -(አፈ -ድ፴፫)

ጓልሕ -ድሪ ቅንጥ፤ የአፍኣ። ወይም የውስጥ መገላለጥ

ጓያ -በቁሙ፤ የታወቀ ያበባ እኽል፤ እግርን ከጕልበት በታች የሚሰብር የሚያወጫምድ የሚያስነክስ የሚያሽመደምድ። -(ተረት) አህያና ጓያ ባምሳያ

ጓጓ -ጋጋ እኅወ ቀቀኖ። የጥንብ አሞራ እንደ ጋጋኖ በዝቶ ተንጋግቶ የሚኼድ

No comments:

Post a Comment

ማውጫ

ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ