~ጰ~

                                 

-ትርፍ ዲቃላ ፊደል፤ በመልክ በተራ ፳፭ኛ፤ መልኩ ድምፁ የተዴቀለ ስሙ ጴት ጰይት፤ ይኸውም ቤት በይት እንደ ማለት ነው ቍጥሩ አኃዝ ሲኾን ሰብዐቱ ምእት ይባላል፤ ያቡጊዳን አኃዝ ተመልከት። የኋላ ሰዎች በራሱ ላይ ነቍጣ ምረው ጸን ብለውታል ግእዝ በፊት በነበረው በሳባ ፊደል ግን ዲቃልነቱና ድርብነቱ በመልክም በድምፅም የበ ብቻ በር የቀድሞ ቅርጹ ሠራረዙ እንዴት እንደ ኾነ፤ ፀንና የዐጰ ፍች ተመልከት ጰና ምንም ኹለት ዐይነት ቢኾኑ በምስጢር አንድ ርመት ናቸው ሲላላ ሲጠብቅ ደግሞ ይባል ነበረ ይባላል። ይኸውም ሊታወቅ በጰና በፐ የሚጣፍ ቃል ኹሉ፤ በጽርእና በቅብጥ በሮማይስጥ በዕብራይስጥም ኹኖ ይገኛል። ለግእዝ ቋንቋ በውድ እንጂ በግድ አይፈለጉም እንሆ ዐረቦች ጴጥሮስ ጳውሎስ ጲላጦስ፤ ወይም ፔትሮስ ፓውሎስ ፒላቶስ በማለት ፈንታ ቡጥሩስ ቡሉስ ላጦስ ይላሉና፤ ዕብራውያንም ፌጥሮስ ፎሉስ ፊላጦስ ይላሉና፤ ለግእዝም በጰና በፐ ፈንታ ወይም ይበቃው ነበር ጽርእና ቅብጥ ሮማይስጥ ቃል የመጣ የውጭ አገር ቋንቋ ያልተተረጐመ ፍጹም ጥሬና ባር ስም ወይም ጋላና ወላሞ ካልኾነ በቀር ለግእዝና ላማርኛ ለትግሬም ለትግሪኛም ጰንና ፐን የሚያስፈልግ ቃል የለም፤ አይገኝም። ጥንቅ የነበረ የግእዝ ፊደል አለመኾኑ የኋላ ቅጥል መኾኑ ዲቃልነቱ በዚህ ይታወቃል በጋልኛ ተርፏል፤ ፐም በወላምኛ ይገኛል፤ ጋልኛ ግን ሴማዊና ሳባዊ ይመስላል

ጰላሞን -ስመ ሰብእ።

ጰላጢኖስ -(ጽር፤ ፕላታኖስ) የዛፍ ስም አንድ ዐይነት ዛፍ፤ ታላቅ ገናና እንደ ዋርካና እንደ ዘግባ ያለ ባለብሉዮች ግን ለይተው ሾላ ብሳና ውዝ ገውዝ ይሉታል ኖኅኩ ከመ በቀልት ወዐበይኩ ከመ ጰላጢኖስ -(ሢራ፳፬ -፲፬)

ጰራልያ -(ጽር ፓራሊዮስ) የባሕር ዳር ጽንፍ ጠረፍ ወደብ ገደብ አጠገብ ጎረ ቤት ራልያ ዘምድረ ከነዓን ሰብአ ራልያ -(ዘዳ፩ -፯። ኢያ፲፩ -፫። ሕዝ፳፭ -፲፮)

ጰራቅሊጦስ -(ጽር ፓራክሊቶስ። ፕራቅሊጥ) አማላጅ አስታራቂ አፍ በቃ ትርጁማን አምጃር፤ እያጣፈጠ የሚናገር፤ ስብቅል ካፉ ማር ጠብ የሚል። ወእመኒ ዘአበሰ ብነ ኀበ አብ ጰራቅሊጦስ ኢየሱስ ክርስቶስ ጻድቅ። ወአፉየ ሙሴ ለእ ኮነ ጸያፈ፤ ራቅሊጦስ ሮን ይኩነኒ -(፩ዮሐ - -፩። ደራሲ)

 -ናዛዚ መጽንዒ፤ መስተፍሥሒ፤ መንፈስ ቅዱስ። በዓለ ምሳ፤ የትንሣኤ ዐምሳኛ የዕርገት ዐሥረኛ፤ እሑድ ቀን የሚውል። እስእሎ ለአ ይፈኑ ክሙ ራቅሊጦስሀ ካልአ። ወቡሩክ መንፈስ ቅዱስ ጰራቅሊጦስ መጽንዔ ልነ ዕለተ ራቅሊጦስ ዘውእቱ ተፍጻሜተ ኀምሳ -(ዮሐ፲፬ -፲፮ ቅዳ። አቡሻ -፴፰)

ጰንገለ [1]-(ጽር አፓንጌሊን፤ ገንጰለ) ቀዳ፤ መለሰ፤ ተረጐመ ገለበጠ ጣፈ። አነበበ፤ አየ አስተዋለ፤ ተመለከተ፤ የመጽሐፍ መጽሐፍ ግን በጰንገለ ፈንታ እንደ ጽርኡ አጰንገለ ይላል፤ አያሰኝም። ዘያጰነግል መጻሕፍተ እግዚ ዘብሉይ ወዘሐዲስ። ይደልዎ ለኤጲስቆጶስ የኀሊ ተሓሥሦ ወአጰንግሎ መጻሕፍት በበ መትልው ፈከረ ሐዲሰ ወአጰንገለ ብሉየ። አጰንገለ ሎሙ መጻሕፍተ በነገረ ብሔሮሙ፤ መለሰ -(ቀሌ ዲድ -፬። ስንክ -ኅዳ፮ አዋል) ያጰነግሉ መጻሕፍተ ውስተ ጸሎታቲሆሙ ወአጰንግሎሙ። ይደሉ ለውጡናን ያብዝኁ አጰንግ ውስተ ትእዛዛት ወውስተ ትሩፋት፤ ተመለከተ -(ሥር -ጳኵ ፊልክ -፸፫። ፻፵፯)

[2]-(ፈንገለ) ፈነገለ፤ ፈንጋይ ኾነ። ንጰለን እይ።

ጰንጋሊ መጵንግል -የሚቀዳ የሚመልስ፤ አንባቢ ተመልካች። መጰንግል ዘይቤ ተርጓሚ ወአንባቤ መጽሐፍ በቃል -(ጥሬ -ሰዋ)

ጰንጠቆስጤ -(ጽር ፔንቲኮስቲ) በዓለ ኀምሳ የፋሲካ ዐምሳኛ፤ በዓለ ሠዊት፤ ጰራቅሊጦስ። በዓለ ጰንጠቆስጤ ቅድስት። መዋዕለ ንጠቆስጤ። ሰላም ለድሜጥሮስ ሐጋጌ አጽዋም ምስቴ ወሠራዔ መብልዕ በጰንጠቆስቴ -(ጦቢ፪ -፩። ግብ፪ -፩። -፲፮ ስንክ -ጥቅ፲፪)

ጰንጤን ጳንጦስ -(ጽር ፖንቶን) ሀገር፤ በእስያ ውስጥ ያለች -(ማቴ፳፯ - ጴጥ - -)

ጰይት ጴት -ስመ ፊደል፤ ጰ። በዪት ቤት ማለት ነው አንድ ወገን ናቸው ንጠቆስቴ ጰራቅሊጦስ ብለውም የሚፈቱ አሉ

ጲላጦስ -ስመ ሰብእ።

ጲክሶን -(ጽር ፒክሶስ) እሾኻም ዛፍ ግራር፤ የግራር ዐይነት ሰጢንን ተመልከት፤ ከዚህ ጋራ ንድ ነው ብሔረ ርዝ ወዕፀ ቅሶን -(ኢሳ፵፩ -፲፱)

ጳሒን -( ቅብጥ ፓዖኒ) ስመ ወርኅ ሠኔ በኡናህን እይ፤ ከዚህ ጋራ አንድ ነው -(ስንክ -ሠኔ፲፱) ዳግመኛም በጳሒን ፈንታ ጵዮን ይላል ፍችው ንድ -(መጽ -ምስ)

ጳልቃን -(ጽር ፔሌካን) ርኩም። ቀቀኖን ተመልከት ከዚህ ጋራ አንድ ነው። መምህራን ግን የከራድዮንንዕ ለጳልቃን ጥተው ይፈታሉ ራድዮንን እይ

ጳሲካ -(ጽር ፓስኻ) ፍሥሕ፤ ፋሲካ። ወይገብሩ ጳሲካ -(ኩፋ -፵፱። )

ጳስጦፎርያ -(ጽር ፓስቶርዮን) የዕቃ ቤት፤ ቤተ መዛግብት -(ኤር፴፭ -)

ጳሬኑ -(ጽር ፓሪኑ) -(907) -(ጽር ፓሪኑ) ጥሩ ደንጊያ፤ ፍጹም ነጭ፤ የእብነ በረድ ዐይነት። ዕንቍ የዕንቍ ስም

ጳኵሚስ -(ቅብጥ ፓኹም) ስመ ብእ፤ ዐቢይ መንኮስ የእንጦንስ ሦስተኛ፤ እንጦንስ መቃርስንና ጰላሞንን ጰላሞን ጳኵሚስን፤ ጳኵሚስ ቴዎድሮስን፤ ቴዎድሮስ አረጋዊ ዘደብረ ዳሞን ይወልዳል ጳኵሚስ ዘመን ምሉ አበ ማኅበር ኹኖ የኖረ ነው። ራእይ ዘአባ ጳኵሚስ። ሥርዐተ ጳኵሚስ።

ጳኵምስ -(ቅብጥ ፓኾን ፓሾንስ) ስመ ወርኅ ግንቦት -(ስንክ -ሠኔ፲፱)

ጳኵሲማ -(ጽር ፓክሳማስ። ዕብ ፓክሳም) ደረቅ ዳቦ፤ ርኵሪት፤ የለከት የብስኩት ዐይነት፤ እንዳይነቅዝና እንዳይሻግት ታምሶ ተጠብሶ ብዙ ቀን የሚኖር የመነኮሳት ምግብ። ክልኤቱ አእሩግ ዐደዉ ፈለገ ወነበሩ ይብልዑ ወጠምዐ ሐዱ እምኔሆሙ ጳኵሲማሁ ወይቤሎ ካልኡ ምንት ታርሕሳ ወታስተፌሥሖ ለልብከ በዕለተ ሰንበት ይበልዕ አሐደ ጳኵሲማ። ወይትሜጦ አሐደ ጳኵሲማ ምኅብስት ወሐምል -(ፊልክ -፸፰። ስንክ -ታኅ፲፭ ፲፯)

ጳውሎስ -(ጽር ፓፍሎስ ሮማይ ፓውሉስ) ንኡስ ትንሽ።

ጳውቄና -(ጽር ፍኪና) ንጨት ሉሕ ጠርብ የሚኾን፤ የሚቃነጥ የሚቀረጥ፤ እንደ ጥድ እንደ ዘግባ ያለ ባለብሉዮች ግን ለይተው ጥድ ኵሓ ይሉታል -(፫ነገ - -፱። -፲፭ -፴። -፲፩ ፪ዜና - -)

ጳዝዮን [1]-(ጽር ቶፓዚዎን) ብጫቴ ንቍ፤ ወራውሬ -(ዘፀ፳፰ -፲፯ ፴፮ -፲፯ ሕዝ፳፰ -፲፫) በወራውሬ ፈንታ ጳዝዮን በጳዝዮን ፈንታ ወራውሬ ይላል -(ራእ፳፩ -)

 [2]-(ዕብ ፓዝ። ጽር ቶፓዚዮን) ፋዝ የአፌዝ ወርቅ ጥሩ ወርቅ ፎዘን ተመልከት ምወርቅ ወእምጳዝዮን -(መዝ -፻፲፰)

ጳጕሜን -(ጽር ሄፓጎሜኔ) በቁሙ፤ ግሜ፤ ጭማሪ ተውሳክ ቀን ተሩብ ኹለተኛም ከፀውደ ወርኅ ስለ ረፈና ባመት መጨረሻ ስለ ተገኘ ተረፍ ይባላል ሩቡ ደግሞ ባራተኛ ዓመት ይመላና የነበረው ይባላል ይህም ስድስተኛ ጳግሜ አራቱ ወንጌላውያን በሰዓትና በኬክሮስ ካራት አድርገው ስለ ተካፈሉት እንዳምስተኛው ከአበቅቴ ገብቶ ይቈጠርም። ስድስተኛነቱም ላለፈው ለሉቃስ ጳግሜ ነው እንጂ ገና ወደ ፊት ሚመጣው ለዮሐንስ ጳግሜ አይዶለምና፤ ዮሐንስም በመስከረም አንድ ባተ እንጂ በጳግሜ አልባተምና በዮሐንስ መን በዓለ ልደትን በጳግሜ ምክንያት ማፋለስ ታላቅ ስሕተት ነው ይህም ስሕተት የተዠመረ ባፄ ምደ ጽዮን ዘመን ነው። ማውረድና ማፋለስ ከኾነም በልደት ብቻ ምን መጥቷል፤ ኹሉን ካመት እስካመት መናድ ያስፈልጋል፤ ትንሣኤም ቅዳሜ ይውላል

ጳጦስ (ጽር ቶስ) ባጦስ የሾኽ ጥቋጦ ሐመልማል። ባጦስንና ሳቤቅን ተመልከት በኀበ ዕፀ ጦስ (ሱቱ ዕዝ፬ ፫። ማር፲፪ ፳፮ ግብ፯ ፴፭። ዲድ ፴፮ ድጓ)

ጳጲራ -ፓፒራ።

ጳጳስ -(ሳት። ጽር ፓፓስ) ቄስ፤ ቆሞስ ዐርከ ኤጲስቆጶስ ሢመተ ዴሆሙ ጳጳሳት -(፩ጢሞ - -፲፬) ቄሱ ጳጳስ እንዲባል ጳሱ ደግሞ ቄስ ይባላል -(፪ዮሐ -፩። ፊልጵ፩ -)

 -ኤጲስቆጶስ፤ ሠያሜ ቀሳውስት ወዲያቆናት። ዘይፈቅድ ይሠየም ጳጳሰ -(፩ጢሞ - - ቲቶ፩ -፯። ግብ፳ -፳፰ ኪዳ) ክልኤቱ ምእት ጳጳሳት -(ስንክ -መስ፲፪)

 -በቁሙ፤ ጳጳስ፤ መጥሮጶሊስ፤ የኤጲስቆጶሳት አለቃ አዛዥ ወለእመ ጳጳስ ሐደ ኤጲስቆጶሰ ምኤጲስቆጶሳት -( - -)

ጴጥራ -(ጽር ፔትራ) ኰኵሕ፤ ንጥፍ ደንጊያ፤ ጭንጫ

ጴጥሮስ -(ጽር ፔትሮስ) ኰኵሓዊ ዘኰኵሕ ብእሴ ኰኵ የግእዝ መላሽ ግን በጴጥሮስ ፈንታ ኰኵሓዊ እንደ ማለት ኰኵ ይላል፤ የተሳሳተ ነው፤ አያሰኝም። ጴጥሮስ ልዩ እንደ ኾኑ ኰኵሓዊና ኰኵሕም ልዩ ናቸው ወኰኵሕሰ ክርስቶስ ሃይማኖተ ጴጥሮስ ዘተብህለ በአፈ ጴጥሮስ፤ አንተ ውእቱ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር፤ ስመ ይቤ ወዲበ ዛቲ ኰኵ አሐንጻ ለቤተ ክርስቲያንየ፤ ከመ ዘይቤ ወዲበ ዛቲ ሃይማኖትከ -(ትር -ወን ማቴ፲፮ -፲፰ ፩ቆሮ - -፲፫ -)

ጴጥያስ ጲጦን -ጦን፤ -(ጽር ፒቲስ ፒቲዬስ) ጥሩ የተክል ንጨት ዛፍ ምዑዝ ገናና ጢጤንን ተመልከት፤ የዚህ ጎር ነው። ዕፀ ጴጥያስ -(ሕዝ፴፩ -፰። ኩፋ -፳፩)

ጵልንትዩ -(ጽር ፕሊንቲዩ ዕብ ማልኬን) የጣዖት ቦታ ምሥዋዐ ጣዖት ደቂቀ አሞን ሞሎኽ ለሚባል ጣዖት ልጆቻቸውን የሚጠብሱብት የሚያቃጥሉበት የሞሎኽን ፍች ተመልከት። ባለብሉዮች ግን ግዞት የግዞት ቤት ይሉታል -(፪ነገ -፲፪ -፴፩)

ጵስጥቂስ -(ጽር ፒስቲኪስ) ጥሩ ሽቱ፤ ውድ ክቡር -(ዮሐ፲፪ -)

ጵሩጳጣ -(ጽር ፕሮባታ) አባግዕ በጎች የበግ መንጎች።

ጵሩጳጥቄ -(ጽር ፕሮባቲክ) አባግዓዊ፤ ዘአባግዕ፤ የበጎች። አንቀጸ ጵሩጳጥቄ -(ነሐ፫ - -፴፩። ዮሐ፭ -) ባለሐዲሶች ግን ዘብዙኃን ዘፈውስ ዘበዓል ይሉታል

ጵርስፎራ -(ጽር ፕሮስፎራ) መባአ ኅብስት፤ ሰንበቴ እንደ ዛቲና እንደ ተስፋ ያለ ወይም ኅብስተ አኰቴት፤ ምእመናን የሚያቀርቡት ርባን። ጵርስፎራ ዘሰንበት። ወያብኡ ርባዕተ ጵርስፎራ በዕለተ ሑድ ወሠለስተ በካልኣን ዕለታት -(ኪዳ ሥር -ቅዳ)

ጵርንሶ -ጵርንሶ፤ -(ጽር ፓሪኒስ) ዝኒ ከማሁ ዕንቍ -(አስቴ፩ -)

ጵርዮን ዮኖ -(ጽር ፕሪዮን) የሰው ወጥመድ፤ መጋዝ፤ ጥርሳም ብረት፤ መኪና የሚቈርጥ የሚበጣጥስ። አንበሮሙ ውስተ ጵርዮን -(፪ነገ -፲፪ -፴፩ ዮዲ፫ -)

ጵርድክይሴ -(ጽር ፔርዲክስ) ድርንቅ የባሕር ቆቅ፤ ወይም ሶረን -(ገድ -)

ጵርጵግ -(ጽርእ) ስመ ብእሲት፤ መበለት ኤልያስን ያስተናገደች -(ሉቃ፬ -፳፮) ይህ ስም የተገኘ ካንኮበሮች መምህር የኔታ ወልደ ሥሉስ ቃል ነው ርሳቸው ከመምህራቸው አፍ ወይም ከአዋልድ መጽሐፍ አግኝተው እንዲህ ይሉ ነበር ይባላል

ጵርፍርዮና -(ጽር ፖርፊሪዮና) የባሕር ሮ፤ የማይበላ -(ዘዳ፲፬ -፲፰)

ጵኒኖ -(ጽር ፒኒኑ። ዕብ ፍኒኒም) ንቍ፤ የዕንቍ ስም፤ ሰደፍ ወይም ሌላ -(አስቴ፩ -)

ጵንጋሌ -መቅዳት መገልበጥ፤ አገለባበጥ፤ ግልበጣ ምለሳ ንባብ ምልከታ።

ጵዮን -ሠኔጳሒን

ጵጱስ -(ሳን) የጰጰሰ የተጰጰሰ ጳጳስ የኾነ፤ የተሾመ -(መጽ -ምስ)

ጵጳሴ -መጰጰስ፤ አጰጳጰስ ጳጳስ መኾን ጵጰሳ ጳጳስነት  ሢመተ ጵጳሴ -(ስንክ -መስ፬)

ጵጵስና -ጳጳስነት፤ ከዊነ ጳጳስ ማዕርግ። ወሶበ ተሠይመ ጵጵስና ዝንቱ ዘዝኩር በስመ ሊቃናት -( - -)

ጶሊስ -(ጽር ፖሊስ) መዲና ታላቅ ተማ ጳጳሳት ስምዖን ዘእስክንድርያ ሲስ -(ስንክ -ሐም፳፯)

ጶዴሬ -(ጽር ፖዲሪስ) የላይ ልብስ ጥሩ ክቡር በርኖስ ጀባ መጐናጠፊያ፤ ነገሥታት ካህናት የሚለብሱት። ልብሰ እንግድዓ፤ የደረት ልብስ ሳንቃ ከአልባሰ ክህነት አንዱ። ዘይለብስ ዴረ ልብሰ ጶዴር -(ሕዝ፱ - ሢራ፳፯ -፰። ራእ፩ -፲፫ ዘፀ፳፭ -)



 

No comments:

Post a Comment

ማውጫ

ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ