~ኀ~

                                 

-ዘጠንኛ ፊደል የሆይ   ሦስተኛ፤ የሐውት ኹለተኛ። ስሙ ኀርም፤ ጸሐፍት ግን ብዙኃን ይሉታል ዘጠንኛነቱም በመልክ ብቻ እንጂ እንደ ጤት በተራ በፊደልነት አይዶለም፤ ሦስተኛና ኹለተኛነቱም ድምጥና በቅርጥ ባሠራረዝ ነው። ፀጰ የጸ ዲቃላ ስለ ካባቱ ከጸደይ እንዲደረብ ለብቻው እንዳይቈጠር፤ ኀርም ኀም የሐ ዲቃላ ስለ ኾነ ከሐ ቢደረብ እንጂ ለብቻው አይቈጠርም፤ እንደ ኻያ ኹለቱ ፊደላት መደበኛነት የለውም። በፊደል ቍጥር ግን ከታው በኋላ ሲጣፍ -(ሀቀ) -(ወቀ) ፮፻ ይባላል ፐም ነዚህ ቀጥለው ይገባሉ ፻ነቱም መሰና ምስት ምሳ የሚጣፍ በኀርም ነውና፤ ያምስትነት ምስጢር ስላለው ነው። ዳግመኛም በመልክና በተራ ቍጥር ታስዓይ ፊደል ስለ ኾነ ከፐ በኋላ የ፱፻ አኃዝ እየኾነ በታስዕነት ይጣፋል፤ ይህም ፯፻፤ እያለ መኼዱን ያሳያል፤ አቡጊዳን እይ በዐረብ ፊደል የኀና የፀ ድምፅ ከሐና ከጸ ድምፅ ልዩ ሲኾ መልካቸው አንድ ነው፤ ከነቍጣ በቀር መለዮ የለውም ገጐ ከኰ እንደ ማለት ነው በግእዝ ፊደል ግን የመልክ እንጂ የድምፅ ልዩነት የላቸውም በጥፈት ብቻ ምስጢርና ቃል የቋንቋ ክሼ ይለያሉ ልዩነታቸውም የጠፋ ከፍሬ ምናጦስ ወዲህ ነው ከዚያ በፊት ግን የኀርም ድምፅ እንደዚህ ነበረ ይባላል፤ ኅኻ -(ኃኻ) ኄኼ ኅኽ ኆኾ፤ ራብዑም እንደ መልኩ የድምጥና የምስጢር ልዩነት አለው፤ አፍ ያስከፍታል፤ ዝርዝር ያሳያል። ኑኅ ኑኃ። ብዝኅ ብዝኃ። በዐረብ ግን ግእዙ ይባላል። በዕብራይስጥም እንደዚህ አኹን እንደ ጣፍነው የካፍ ድርብ ኹኖ ይነገራል፤ ዕብራውያን ካፍን ነቍ ጨምረው ከ፤ ነቍጣውን ትተው ይሉታል መልኩም ዐይነት ነው ባማርኛና በትግሪኛ ካፍን እንደ ኀርም ማለት የዕብራይስጥ ሕግ ነው እንጂ የዐረብና የግእዝ አይዶለም።

ኀለየ -ለዘበ፤ ዘፈነሐልይ ሐለየ

ኀለፈ -ማለ ተረገመሐሊፍ ሐለፈ።

ኀሊል ሎት -(ኀለለ የኀልል ይኅልል ዐረ ኃለ ሱር ወዕብ ሓላል) መብሳት፤ መንደል መፈልፈል፤ ውስጠ ክፍት ባዶ ማድረግ እንደ ከበሮ።

ኀሊቅ ቆት -(ኀልቀ የኀልቅ ይኅልቅ ዐረ ኀሊቀ። ዕብ ሐላቅ ከፈለ) ማለቅ ማርጀት መጨረስ፤ ተካቶ መጥፋት ኵሉ ግብር ይበሊ ወየኀልቅ ወገባሪሁ የኀልቅ ምስሌሁ እስከ ልቀ ኵኩ ክርታስ በእሳት ልቀ ወይኖሙ ሐሊቀ የኀልቁ ምገጸ ምድር -(ሢራ፲፬ -፲፱ ኤር፵፫ -፳፫ ዮሐ፪ -፫። ሶፎ፩ -)

 -ማነስ መጕደል፤ ሕጹጽ መኾን። የኀልቅ ክብሩ ለያዕቆብ። ኢየኀልቅ ወርኅኪ -(ኢሳ፲፯ -፬። -)

 -መከፈል መከፋፈል፤ መለየት ልዩ ልዩ መኾን። ኢኀል ሥጋ ዘተደመረ -(ቄር)

 -መጨነቅ ለሞት መቅረብ፤ ነፍስ ሥጋ ልለይ ልውጣ ማለት፤ መቈረጥ፤ የትንፋሽ የነገር ሶበ ኀልቀት ነፍስየ። ይኅልቅ ነገሩ -(ዮና፪ -፰። መዝ፻፵፩። ጦቢ፯ -) ይባእ ነገረ ክልኤሆሙ ኀበ ፈታሕት በማለት ፈንታ፤ ይኅልቆሙ በበይናቲሆሙ ይላል የመላሽ ስሕተት ነው -(ዘፀ -፳፪ -)

ኀሊው ዎት -(ኀለወ ይኄሉ ይኅሉ) መጠበቅ፤ ዘበኛ የሌሊት። ሌሊተ ኅልዉ ወመዓልተ ተቀነዩ። ይተግሁ ወይኄልዉ። እምተግሀ ወእምኀለወ። ከንቶ ይተግሁ እለ ይኄልዉ። እለ  ይኄልዋ -(ነሐ፬ -፳፪ ሉቃ፪ -፰። ፲፪ -፲፱ መዝ -፻፳፮ ሰቈ፬ -፲፬)

ኀሊፍ ፎት -(ኀለፈ የኀልፍ ይኅልፍ ዕብ ወሱር ሓላፍ ዐረ ኀለፈ) ማለፍ ፈጥኖ መኼድ፤ መሻገር መራመድ፤ መራቅ መወገድ ዘኒ ኀለፈ ወዘኒ ይመጽእ ወእምድኀረ ኀለፉ እሉ እምቅድመ ገጹ ኅልፍ -(ሢራ፵፪ -፲፱ ማቴ፪ -፲፫ መክ፫ -)

 -መሞት መለየት መቅረት። ኀለፈ ሮን ወበከይዎ አሌ ለነ፤ ካህነ ምላክ ኤርምያስ ኀለፈ እምኔነ። ዘከመ የኀልፎ ብዙኅ ረባሕ -(ዘኍ፳ -፳፱ ተረ -ኤር ሢራ፴፯ -)

 -መናፈቅ፤ መሻት መመኘት። ኀለሰፈት ፍስየ ውስተ ድኅኖትከ -(መዝ -፻፲፳) ደግ መልካም ሲሉ ማለፊያ ማለት ማርኛው ዚህ የወጣ ው፤ ምኅላፍን እይ ባለመጣፎች ኀፈን ገባ ይሉና ምስክሩን ኀለፈት ሰንበት። የኀልፍ ሐጽ ውስተ ሥጋሁ ይላሉ፤ የተሳሳተ ነው -(ማር፲፮ -፩። ኢዮ፳ -፳፭) ዳግመኛም በኀለፈ ፈንታ ተኀለፈ ይላል፤ ስሕተት ነው ዑቅ አልቦ ዘይትኀለፈከ ኢትትኀለፎ ለዘይስእለከ -(ሄርማ ሢራ፬ -)

ኀላዊ -(ዊት ውያን ያት ለውት) የሚጠብቅ ጠባቂ ዘበኛ እረኛ ኖላዊ ዘመዓልት ኀላ ዘሌሊት ኀላዌ ብዕራይ -(ድጓ አዋል)

ኀላዪ -(ዪት ይያን ያት) የሚያስብ ዐሳ ኀላ እኩይ -(ሲኖዶ)

ኀላፊ -(ፊት ፍያን ያት ኀለፍት) የሚያልፍ መንገደኛ፤ ላፊ ጠፊ ሟች ተለዋጭ ወረተኛ።  ኀላፌ ፍኖት። ኵሉ ኀላፍያን። ዐበጡ አሐደ እምኀለፍት። ዓለም ኀላፊ። መብልዕ ኀላፊ። ዐርክ ኀላፊ -(መዝ -፸፱። ሰቈ፩ -፲፪ ቀሌ ዮሐ፲፫ -፲፪ ሢራ -) በኀለፍት ፈንታ ላፊት ይላል የተሳሳተ ነው።

ኃል -(ላን ልት ታት) -(ሐባብ ዐረብ) አጎት፤ -(ኃልት) አክሥት፤ ያባትና የናት ወንድም እኅት። -(ተረት፤ በቅሎ አባቷን ስትክ) ባዝራ እናቴ፤ ድንጕላ አጎቴ።

()          ኀልዮ ዮት -(ኀለየ ይኄሊ የኀሊ ትግ ሐባ ኀለነ) ማሰብ፤ ከልብ ማንቃት ነገርን ሥራን ከነቢብ ገቢር በፊት በሐሳብ በልብ መፍጠር ማስገኘት ማሰናዳት። መመርመር መፈለግ፤ ማውጣት ማውረድ። አልቦሙ ለኀልዮ። ልበ ወሀቦሙ በዘይኄልዩ ኀለ መጠነ ሐዱ ሰዓት ተኀልዩ ወኢምንተኒ -(ኩፋ -፳፪። ሢራ፲፯ - ዳን፬ -፲፮ ፊልጵ፬ -)

ኀልዶ ዶት -(ኀለደ ይኄልድ የኀልድ። ሱር ሕላድ በልብ ተሳበ፤ እባብኛ ደ። ዕብ ሓላድ፤ ፋረ ፈረ ዐረ ኀለደ፤ አረጀ) ብዙ ዘመን መኖር መቈየት ዕድሜ ማግኘት መጨረስ መፍጀት መክተት ድሜን ሥራን መቍረጥ መበጠስ ምክርን ፍርድን። አለደን ተመልከት የዚህ ጎር ነው

ኀመለ -ለቀመሐሚል ሐመለ

ኀመሰ -ዐመሰ ዋኘሐምሶ ሐመሰ

ኀመየ -ዐማ፤ ነቀፈ፤ሐምይ ሐመየ

ኀሙስ -የዕለት ቅጽልና ስም፤ ዐምስት፤ ዐምስተኛ ተዐገሡ ዓዲ ኀሙሰ መዋዕለ ወእምድኅረ ሙስ መዋዕል አመ ሙሱ ለሠርቅ ቅጽል -(ዮዲ፯ -፴። -፱። ሕዝ፴፫ -፳፩) ለተ ኀሙስ፤ ምሴተ ሙስ ስም። -(ግጥም ስላጤ ቴዎ ሞት) አምላክን መስሎ ቴዎድሮስ ንዑና ሑሩ ሲል ዐሙስ ሰኞ መቅደላ ተጨነቀ መኾኑ ታወቀ

ኀማሲ መኀምስ -(ስት ሳን ሳት) ዐምስት የሚያደርግ፤ ካምስት የሚከፍል ከፋይ፤ ዐምስት ባይ

ኀማዪ -የሚያስር አሳሪ፤ ባለወግ።

ኃምሲት -የኬክሮስ ዐምስቲያ ክፍል በራብዒትና በሳድሲት ማኽል ያለች። አንዲቱ ኃምሲት ስሳ ሳድሲት ትኾናለች፤ ኬክሮስን እይ። በመካነ ሳድሲት ኍልቈ ኃምሲት -(አቡሻ -፲፩)

ኀምሳ -() በቁሙ ዐምሳ ጊዜ ሥር ወይም ጊዜ ዐምስት ኀምሳ ወኀምስተ መዋዕለ። ኀምሳ በእመት በዓለ ምሳ ወበኀምሳ ዕለት ምሳ ዓመት አልብከ -(ጦቢ፩ -፳፩። ሕዝ፵ -፲፭። ዲድ -፴። ቅዳ ዮሐ፰ -፶፯)

ኃምሳዊ -(ዊት ሲት) ዝኒ ከማሁ ዘት ኃምሳይ ዘአውሰበ ራብዒት አው ኃምሲተ -(ያዕ -እል - - -)

ኀምስ -የቍጥር በሴት አንቀጽ ዐምስት ማለት ነው። ምስ  ዋልድ ኀምስ ህጉረ ብጽ ይነብባ። ኀምስ ኅብስት ዐሥሮን ደናግል፤ ወእምኔሆን ኀምስ አብዳት ወኀምስ ጠባባት -(፩ነገ -፳፭ -፵፪። ኢሳ፲፱ -፲፰ ማቴ፲፬ -፲፯ ፳፭ -)

ኃምስ -(ስት) ዐምስተኛ ካምስት ንድ፤ ዐምሾ ወለደት ወልደ ኃምሰ ወበኃምስ ትውልድ ዐርጉ እምግብጽ ኢዮብ ኃምስ ምአብርሃም። በኃምስ ወርኅ -(ዘፍ፴ -፲፯። ዘፀ፲፫ -፲፰ ታሪ -ኢዮ ኤር፩ -)

ኀምስት -ዝኒ ማሁ፤ በቁሙ በወንድ አንቀጽ ወነበረ በዘከመ ግብ ኀምስተ ዓመተ ኀምስቱ ዕደው በሩ ምስሌኪ ምስቲነ -(ፊልክ። ዮሐ፬ -፲፰ ስንክ -ሠኔ፲፱) ባርቲክልነት ወይም ባጸፋነት ሲፈታ ዐምስቱ፤ ዐምስተኛው ካምስት አንዱ ያሰኛል ውስተ ምስቱ ሰማይ -(ዕር -ኢሳ፰ -)

()          ኀምሶ ሶት -(ኀመሰ ይኄምስ የኀምስ ዐረ ኀመሰ ሱር ወዕብ ሓሜሽ) ዐምስት ማድረግ ካምስት መክፈል፤ ስካምስት ጊዜ መመላለስ። ዘይኄምሶን ለኬክሮሳተ ሰዓታት ከመ ይኩና መዓርገ ጸሎታት -(መጽ -ምስ)

ኀምራዊ -ዐይነቱ ወይም ቅላቱ የጥቍር ወይን ጠጅ የሚመስል መሻች፤ መሸተኛ፤ ሸያጩና ገዢው

ኀምር -(ዐረ) የወይን ጠጅ፤ የጥቍር ቀይ ደባባ።

ኀምዮ  ዮት -(ኀመየ ይኄሚ የኀሚ) ማሰር መቀፈድ መይዎ ለእግዚእነ አዘ የኀምይዎሙ ውስተ ክሣውዲሆሙ -(ማር፲፭ -፩። ዮሐ፲፰ -፲፪። ስንክ -ሠኔ፲፱)

ኀሠመ -ከፋሐሢም ሐሠመ

ኀሰሰ - ፈለገ፤ኀሢ ኀሠ ኀሠሠ

ኀሠሣ -(ሣት) ፍላጎት ፍለጋ፤ ጥያቄ ጥየቃ ምርምር ምርመራ ፈቃድ መፍቅድ፤ ሐሳብ ምኞት ብየ ኀሠሣ ምኂሩትክሙ። ንኄ በእንቲኣሁ በብዙኅ ኀሠሣ። ተተክለት ፍትወት በጠባይዕ እንስሳዊት ከመ ይትፈጸም ሠሣ ተራክቦ እምኔሁ ይከውን ዘርዕ ይኩን ፈቃዱ ወኀሠሣሁ ከመ ይኩኑ ትሑታነ -(ስንክ -የካ፳፰ አፈ -ድ፪። - -፳፬ -፩። -) ጐርፍን ዐሠሣ ማለት ዐማርኛው ዚህ ወጥቷል

ኀሠረ -ሰበሰበሐሢ ሐሠረ

ኀሰር -ገለባ ድፍ፤ሐሢር ሐሠረ

ኀሰት -ውሸትሐስዎ ሐሰወ

ኀሠወ -ዋሸ ዐበለ፤ሐስዎ ሐሰወ

ኀሢሥ ሦት -(ኀሠ ኀሠሠ የኀሥሥ ይኅሥሥ ሓሻሽ፤ ሐየጸ ቤቄሽ፤ ፈለገ) ማሠሥ መሟሰስ መጥረግ፤ ማበስ ማደፍ መወልወል፤ የምጣድ ኢትኅሥሥ ጽሕልተ ወኢትልሐስ መጻብኅተ ውሒዘ ንብዓ ኀሠሠ በአጽባዕተ ልምሉም። ወኀሠሠት አንብዕየ በአጻብዒሃ -(ሢራ፴፬ -፲፪ ደራሲ -መድ)

 -መሻት መፈለግ መለመን፤ ለማግኘት። ኅሡ አእዱጊነተኀሥሦሙ ወኢትረክቦሙ። ኅሡ አስተብቍዑ -(፩ነገ - -፫። ኢሳ፵፩ -፲፪ ቅዳ)

 -መጠየቅ መመርመር፤ ለማወቅ። እለ የኀሡ በእንተ ሕያዋን እምነ ሙታን ኢትኅሥሥ እፎ ይትሁነኑ ለኀሢ ወለፈቲን በጥበብ -(ኢሳ፰ -፲፱። ሱቱ -ዕዝ፬ -፲፬ መክ፩ -፲፫)

 -መውደድ መፍቀድ፤ መከጀል መመኘት። ምስጢሩ ያው መፈለግ ነው፤ ከመሻት አይወጣም ኅሥሥ ትግበር ኵሎ ዘያሠምሮ ለእግዚ ኀሰሰ መኰንን ይክሐዶ ክርስቶስ -(ዲድ -፩። ስንክ። መጋ፮) በኀሠሠና በተኃሠሠ ፈንታ ተኀሠሠ ይላል፤ የጣፊና የመላሽ ስሕተት ነው ይትኀሠሥ እኩየ ኵሎ መዋዕለ ሕይወትየ ትኀሠሥ አባግዕየ ምእደ ኖሎት እለ ይትኀንሠሡ በእንተ ፍልሰተ ሔኖክ ወኤልያስ -(ኩፋ -፴፭። ሕዝ፴፬ - አፈ -ድ፳፪)

ኀሲር ሮት -(ኀስረ የኀስር ይኅሰር ዕብ ሐሳር ሱር ሕሳር ዐረ ኀሰረ) መጕደል ማነስ መክሰር መዋረድ መጐስቈል፤ አይቶ ዐጣ አድጎ አነሰ መኾን። ኀስረ ክብሮሙ ኢታዕቢ ርእሰከ ከመ ኢትኅሰር እስመ ኵሉ ዘአዕበየ ርእሶ የኀስር -(ኢሳ፫ -፰። ሢራ፩ -፴። ሉቃ፲፬ -፲፩)

ኀሢዕ ዖት -(ኀሥዐ የኀሥዕ ይኅሣዕ ዐረ ኀሸዐ ዕብ ሐሻህ) ማረፍ ዝም ጸጥ ማለት አለመታወክ። መብረድ መቀዝቀዝ፤ የቍጣ የጠብ ኢሀሎ መዐትም የኀሥዕ ጋእዝ። መዐት ይኅሣዕ -(ምሳ፳፮ - ቅዳ -ኪዳ)

ኀሢፍ ፎት -(ኀሠፈ የኀሥፍ ይኅሥፍ ዐረ ኀሺፈ ዕብ ሐሳፍ) ማከክ ማቍሰል፤ መላጥ መምለጥ፤ መቅረፍ መግፈፍ መግለጥ

ኀሣሢ -(ሢት ሥያን ያት) የሚያሥሥ ሣሽ ፈላጊ መርማሪ። ኀሣሤ ቢብ ሰካዪ ኀሣሤ ዕዳ ውእቱ። ኀሣሥያነ መንግሥተ ሰማያት። ኀሣሥያተ ንዋየ ባዕድ -(ኢዮ፲፩ -፲፪። - -፵፫ -፯። ግንዘ። ዲድ -፲፬)

ኀሳር -(ራት) ሕጸጽ () ሳራ ውርደት መከራ ዕጦት ዳት፤ ጕስቍልና። ኀሳር ዐቢይ ሳርከኒ ወክብርከኒ ምቃልከ መዋዕለ ሳራ ኑሕ ሎቱ ኀሳር ዕጹብ ፍትወት እሞን ለኀሳራት ወለድካማት፤ -(ኩፋ -፲፪ ሢራ፭ -፲፫። ኢዮ፲፰ -፲፪። - -፳፬ -)

ኀሥል -ዳውላ፤ሐሲል ሐሰለ

ኀስል -ዳውላ፤ሐሲል ሐሰለ

ኀሥረ -ጐሰቈለኀሲር፤ ኀስረ

ኀረመ [1]:-ተወሐሪም ሐረመ

[2]-ኀረመ -(ኀረወ) ጣፈ ነደፈ ገረ፤ አመለከተ ከመቅረጥና መፈልፈል በፊት። የኀረወን ፍች ተመልከት

ኀረሠ [1]:-ዐረሰ፤ሐሪስ ሐረሰ።

[2]:-ወለደ፤ኀሪስ ኀረሰ

ኀረወ -ፈረሐሪው ሐረወ

ኀረደ -ዐረደሐሪድ ሐረደ

ኀረፋ -ዐረፋሐረፋ።

ኀሪስ ሶት -(ኀርሰ ኀረሰ የኀርስ ይኅ() ርስ) መውለድ መጨቀል፤ ዐራስ እመጫት መኾ ኢበፀኒስ ወኢበኀሪስ ዕለተ ሪሳ ለእምከ እማቲሆሙ እለ ኀረሳሆሙ ባግዕ ወዕጐላት የኀርሳ -(ኦርጋ። መጽ -ምስ ኤር፲፮ - ዘፍ፴፫ -፲፫) መወለድ ማሕፀን መውጣት፤ ርጥብ ጨቅላ መኾን። ዐራስ ልጅ እንዲሉ

ኀሪው ዎት -(ኀረወ የኀሩ ይኅሩ ዐረ ኀረተ ዕብ ሓራት ሱር ሕራት) መብሳት መንደል፤ መፈልፈል መቅረጥ ማንጠጥ ማስመጥ ማሳበጥ፤ የደንጊያና የንጨት የብረት።ዕርሻና ፋሮም ያሳያል እለ ይገልፉ ወየኀርዉ ዐይነ ማኅተም ሪወ ማኅተም ብን ዘኀረዎ ኬንያ -(ሢራ፴፰ -፳፯ አዋል) ረመንና ኀንፈጠን እይ ኀረመ የዚህ መንቲያ ነው

ኀሪፍ [1]-(ዐረብ ዕብ ሖሬፍ) ጸደይ ያመት ሩብ የዘመን ርቦ በሐጋይና በክረምት መካከል ያለ ወራት። ፪ኛም ከክረምት ደርበው መንፈቀ ዓመት ይሉታል፤ ይኸውም ከጥቅምት እስከ ሚያዝያ ማለት ነው፤ ባገራችን ግን ከሚያዝያ እስከ ጥቅምት ይኾናል።

[2]-ኀሪፍ ዘንድሮ ይህ ዓመት፤ መላው ፲፪ቱ ወር ድጋ ሪፈኒ -(ሉቃ፲፪ -) ገሪፍ ወኀሪፍ ዓምናና ንድሮ።

ኀሪፍ ፎት -(ኀርፈ የኀርፍ ይኅርፍ ዐረ ኀረፈ ዕብ ሓራፍ ከረመ) መልቀም መሰብሰብ፤ የፍሬ መክረም፤ ክረምት እስኪወጣ መቈየት

ኀራሲ መኀርስ -የሚያርስ ራሽ፤ ቀላቢ መጋቢ፤ ተከባካቢ።

ኀራስ -(ሳት) በቁሙ፤ ዐራስ ወላድ ትኵስ እመጫት፤ የጨቅላ እናት፤ የምታጠባ። ብእሲት ኀራስ እምኀራስ ወትክት ድብ ኀራስ ወተመጠዎ እምድኅረ ኀራሳት -(ቄድር ቀሌ ነገ -፲፯ -፰። መዝ -፸፯)

 -ቅላ ርጥብ ልጅ ለጋ ቀንበጥ ቅቤ የሚውጥ፤ ጡት የሚመጥ የሚመጠምጥ። ባማርኛ ልማድ ለወንድም ለሴትም ይከታል፤ በግእዝ ግን ለሴት ብቻ ነው

ኀራዊ -(ዊት ውያን ያት ረውት) የሚሥል፤ የሚቀርጥ። ራዌ ማኅተም -(አዋል)

ኀራውያ -ሕሪያሐረወ

ኀራዪ -(ዪት ይያን ያት) የሚመርጥ መራጭ ራዬ ሰዓት ወኀራዬ ዕለታት -(ቈስጠ)

ኀርም -የፊደል ስም ኀ፤ ልዩ ብቸኛ፤ ኂሩት

()          ኀርሶ ሶት -(ኀረሰ ይኄርስ የኀርስ) ማረስ፤ መቀለብ፤ መመገብ፤ መከባከብ፤ ያራስ የመጫት የወይዛዝር። ዘዘ የኀርስዎሙ። እለ የኀርስዎሙ። ረስኩኪ በስንዳሌ -(ዳን - -፭። ኤር፳፮ -፳፩ ሕዝ፲፮ -፲፫)

ኀርይ ዮት -(ኀረየ፤ ኀርየ። ዐረ ኀረ። ዕብ ሓር) መምረጥ ማሻሻል፤ መውደድ ማቅረብ፤ ለሹመት ለሥራ። -(ተረት) ሰው መርጦ ለሹመት፤ ከንጨት መርጦ ለታቦት አኮ አንትሙ ዘኀረይክሙኒ አላ አነ ረይኩክሙ ወሤምኩክሙ ሕዝብ ዘኀረየ ሎቱ ርስቱ ዘበዳዊት ተነበየ ወበዮሐንስ ጥምቀተ ርየ -(ዮሐ፲፭ -፲፮። መዝ -፴፪። ድጓ) ኀረየ ባለው ዘንዱን ይኅሪ ኀርየ ባለው ይኅረይ ይላል፤ የቀተለና ገብረ ካኼድ ነው

ኀቀፈ -ዐቀፈሐቂፍ ሐቀፈ

ኀበ -(ዐቢይና ደቂቅ አገባብ) ዘንድ፤ ቦዝና ከመ እየ ይኾናል። ወኀበ በዝኀት ኀጢአ ህየ ፈድፈደት ጸጋሁ ለእግዚ ኀጢአት ከበዛች ዘንድ። ኀበ ጸንዐ ክረምት ይበዝኁ አንቅዕት -(ሮሜ፮ -፳። ዘረፋ) ሲኾን የቦታ ቅጽል ነው፤ በቂም ይኾናል ወንሰግር ውስተ መካን ኀበ ቆመ እግረ እግዚእነ። ዘየኀድር ውስተ ብርሃን ኀበ አልቦ ዘይቀርቦ። ከመ ተሀልዉ ሀሎኩ አነ -(መዝ -፻፴፩ ውዳ -፫። ዮሐ፲፬ -) የነቱን -(መኾኑን) ደግሞ የቦታ ቅጽል ስለ ኾነ እምና እንተ ገብተውም ሳይገቡም ይበዘብዙታል አንዳንድ ዜም አዳማቂ ኹነው ይቀራሉ ብሔር እምኀበ ይወፅእ ብሩር፤ የሚወጣበት የአምር ንተ አሐውር፤ የምኼድበትን። አልቦ በኀበ ይከብር ነቢይ፤ የማይከብርበት። ዝና ኾን በኀላፊ ይገባል -(ማር፲፮ -፬። ሉቃ፳፬ -) እየና ኾን በደጊም በትንቢት ይገባል ቤተሳኦል ኀበ ይትነሠት ሖረ ወቤተ ዳዊትሰ ኀበ ይጸንዕ እየ እየ ኀበ ይተብዕ ይትቃተል ኀበ ኀበ ይፈርህ ይጐይይ ሲ። በዚህ  አፈታት መንገዱ የእንዘ ነውና፤ በሩቅ በሩቁ የተባለው በቅርብ በቅርቡ ስስ ሳሳ ይኾናል ኀበ () ፈርህ ስስ። ኀበ ኀበ እረ -(ኢት) ሳሳ እዝ መኾኑ ሲናበብ ብቻ ነው፤ ሲረባና ሲዘረዘር ግን ኀቤየ -( ) ያለ ወደ ኃምስነት ይለወጣል ደቂቅ ሲኾን ደግሞ በቦታ በአካል እየገባ ንድ አጠገብ ወደ ይኾናል ዘንድና አጠገብ በምስጢር ነው እንተ ሀለወት አብ ነበረ ዐዘቅት ሐውር ኀበ አብ -(፩ዮሐ - - ዮሐ፬ -፮። ፲፮ -) ንዳንድ ጊዜም ለና ዳማቂና በቁም ቀሪ ኹነው ያጋንኑታል ባሕታውያን መያጥያን ለኀበ ዓለም፤ ወደ ተላውያን ለኀበ ቃሉ ቃሉን ወይም እንደቃሉ ያሰኛል። ይሠየም ለኀበ እግዚአብሔር ወደግዜር ለሚደርስ ነገር። ብዕል ዘይትዐቀብ በኀበ ዘአጥረዮ ንድ ሠረገላ በኀበ ይጼዐን አዳማቂ -(ፊልክ - ብ፭ -፩። መክ፭ -፲፪ ሔኖ፸፫ -) ዳግመኛም እስከ እም ቅድም በማለት ፈንታ ለኀበ በኀ ይላል፤ የመላሽ ስሕተት ነው መርሕ ለኀበ ክርስቶስ ኢትንሥኡ ቤዛ በኀበ ቀታሊ ዘበኀበ ሰብእ ቢይ በኀበ እግዚ ትሑት ወርኩስ -(ገላ፫ -፳፬ ዘኍ፴፭ -፴፩። ሉቃ፲፮ -፲፭) ር፲፱ -ቍ፸ ተመልከት

ኀበበ [1]:-ሰደበ፤ሀቢብ ሀበበ

[2]:-ወደደሐቢብ ሐበበ

[3]-(ሐንበበ) ዐሸ ረገጠ መቀ የወይን የዘይት ኬደንና ዐጸረን እይ

ኀበየ -ኀበየጠበቀሐብይ ሐበየ።

ኀቢር ሮት -(ኀበረ ኀብረ የኀብር ይኅበር። ዕብ ሓቤር። ሱር ሓባር) ማበር ማሤር አንዱ ካንዱ ጋራ መግጠም መዋደድ መሰማማት፤ መጨመር ብሮ መቈጠር ልብ ሐሳብ መኾን በሩ ቃለ ቢያት ወአሶርሁ ብረ ምስሌሆሙ። ትኅበር ምስለ ኃጥኣን እመ በዝኁ በነ ንኅበር በዘዚኣከ መንፈስ እለ የኀብሩ በሕጋ ለቅድስት ቤተ ርስቲያን -(ድጓ መዝ -፹፪። ሢራ፯ - ቅጻ )

ኀቢን ኖት -(ኀበነ የኀብን ይኅብን ዐረ ኀበነ) መሸጐጥ መክተት፤ ከኪስ ከሴደርያ ማግባት፤ የስዓት የገንዘብ የማረሚያ ማጥለቅ መልበስ፤ ሰውነትን በቀሚስ መክተት ራስን ማሰር፤ መጠምጠም

ኀቢእ ኦት -(ኀብአ የኀብእ ይኅባእ ከበተ ዕብ ሓባእሐባሀ ታባ ዐረ ኀባ) ማባት መሰወር መደበቅ መሸሸግ፤ እንዳይታይና እንዳይገኝ እንዳይታወቅ ማድረግ፤ መሸጐጥ መቅበር እግዚ ኀብኦ ለሔኖክ። ኀብአ ርእሶ። ኀብአ ለመለኮቱ። ኀብአ እዴሁ ሀካይ ውስተ ሕፅኑ። ኅብኦሙ ኅቡረ ውስተ ምድር -(ሢራ፵፬ -፲፮።  ውዳ -፯። ድጓ። ምሳ፳፮ -፲፭። ኢዮ፵ -) በተንና ወረን እይ የዚህ ጎሮች ናቸው።

ኀቢዝ ዞት -(ኀበዘ የኀብዝ ይኅብዝ ዐረ ኸበዘ) ማበዝ መጋገር ሊጥን ወደ እቶ ማግባት በምጣድ ላይ ማፍሰስ ማብሰል በዙ ሪጾሙ እቶን ዘአንደዱ ለኀቢዘ ኅብዝትረሰየ ሄሮድስ ሰብአ ብዙኃነ ለኀቢዘ ኅብዝት ወአዘዞሙ ከመ ይኅብዙ ወትረ -(ዘፀ፲፪ -፴፱። ሆሴ፯ -፬። ዮሴፍ)

ኀባሊ -(ሊት ልያን ያት) ደፋር ጨካኝ። ደፋሪ ወኀባሊ እምሰብእ ዐማፂ ወኀባሊ ባልሐነ -(ቄድር ሊጦን)

ኀባሪ -(ሪት ርያን ያት) የሚያብር ዐባ ሤረኛ ዐድመኛ መሳይ።

ኀባኢ -(ኢት እያን ያት) የሚያባ የሚሸሽግ ሸሻጊ፤ ታዳጊመንጦላዕት ኀባኢተ መለኮት -(ቅዳ)

ኀባዚ -(ዚት ዝያን ያት በዝት) የሚያብዝ በዛ ጋጋሪሊቀ ባዝያን -(ዘፍ፵ -)

ኀብለ -ዐበለሐቢል ሐብለ።

ኀብሎ ሎት -(ኀበለ ይኄብል የኀብል ዐረ ኀቢለ) መክፋት መጨከን፤ ማበድ መወግሸት፤ መድፈር አለማፈር፤ የማይገባውን መናገር መሥራት፤ ይገባኛል ማለት መጽሐፍ ግን በኀበለ ፈንታ ተኀበለ ይላል ስሕተት ነው እፎ እንከ ተኀበለ ልብከ። ተኀበሉ አግብርት ወወረዱ ላዕሌነ ደንገፁ ፋርስ እምተኀብሎታ ቀሲስ ዘተስዕረ በርትዕ በእ ኀጢአቱ ወእምዝ ተኀበለ ዕለ ብረ መልእክት። ዘተኀበለ ያውስብ ራብዓየ -(ኢዮ፲፭ -፲፪ ዮዲ፲፬ -፲፫። ፲፮ -፲። - -፮። - - -)

ኀብጠ -ዐበጠሐቢጥ ሐብጠ

ኀተተ -መረመረሐተተ

ኀቲም ሞት -(ኀተመ የኀትም ይኅትም ሓታም ሱር ሕታም ዐረ ተመ) ማተም፤ መዝጋት መቈለፍ፤ ማሸግ። እመ ኀተምከ ወርቀከ ወብሩረከ ሠናይ ኀቲም ላዕለ ብእሲት እኪት -(ሢራ፳፰ -፳፬። ፵፪ -)

 -መጣፍ መቍጠር ጥፎ ቈጥሮ ማኖር ኀተምከኑ ውስተ ናማቲከ ጌጋይየ -(ኢዮ፲፬ -፲፯)

 -መሸፈን ማልበስ መሰወር፤ መተው። ወገጸ ከዋክብት የኀትም። ኅትሞ ለዝ ራእይ። ኅትም ወኢትጽሐፍ ዘንተ -(ኢዮ፱ -፯። ዳን፰ -፳፮። ራእ፲ -)

 -ስምን መጣፍ ማመልከት፤ በብርዕ በቀለም ወይም በማኅተም፤ ማኅተምም ባይኖር የጥፈትና ያውራ ጣት ምልክት ፊርማ ማድረግ ኀተመ ንጉሥ በሕልቀቱ። ወኀተምዋ ለእብን -(ዳን፮ -፲፯። ማቴ፳፯ -፳፮)

 -ማጥቈር መክተብ፤ ገላን ጥቍር ቀለም ቀብቶ በመርፌ በሾኽ መንቀስ መጠቅጠቅ ኢትኅትሙ ባለክሙ በመርፍእ -( - -፵፭)

 -መጨረስ መፈጸም። ኢይፃኡ እምቤተ ክርስቲያን ዘእንበለ ይኅትም ካህን ይኅትሙ ጸሎቶሙ በጸሎተ እግዝእትነ ማርያም -(ቀሌ - -፲፬)

 -መመስከር፤ ማስረዳት ማጽናት፤ የነገር እስመ ዝስ እግዚአብሔር ተሞ። አኀትም ቃላትየ በጽድቅ -(ዮሐ፮ -፳፯ ቄር)

 -መቅባት መቀደስ ማክበር በሜሮን የኀትም አንፈ ወፍጽመ ልበ ወእዝነ። እመ ቀሲስ ዘኀተማ በቅብዕ ቅዱስ -(ኪዳ - - -፲፪) የኀተመን ፍች ፲፱ ብለው የሚቈጥሩ አሉ ምስክራቸው አያጠግብም። ከተመንና ተበን እይ፤ የዚህ ጎር ነው።

ኀቲው ዎት -(ኀተወ የኀቱ ይኅቱ ዕብ ያቃድ ሱር ቃድ ዐረ ወቀደ) መቃጠል መንደድ ቦግ ቱግ ብልጭ ቍልጭ ማለት፤ መብራት ብርሃን መኾን -(መዝ -፲፯ ኢሳ፷፪ -) ቅድሜሁ የኀትዉ ሰብዑ መኃትው ዕንቍ ዘየኀቱ ርእየተ ገጽከ ምሳለ መብረቅ ተወ -(ራእ፬ -፭። ዘፍ፪ -፲፪ ስንክ -ነሐ፲፫)

ኀታሚ -(ሚት ምያን ያት) የሚያትም ዐታሚ ባለማኅተም። ዓለመ ኀታሚ። ፈጣሪ አስመሳይ ፍጥረቱን በፍጥረት የሚያትም -(ኪዳ)

ኀነፊ -ሐናፊ -(ዕብ ሐኔፍ። ሱር ሐንፋእ፤ ሐንፋያ) ዐላዊ ሓዲ፤ ሸንጋይ አታላይ ግብዝ አረመኔ፤ ስመ ነገድ ካራቱ ነገደ ተንባላት አንዱ፤ የቀሩትም ሦስቱ ሐንበሊ መለኪ ፍዒ ይባላሉ ሃይማኖታቸውም እንደ ስማቸው ራት ነው አይተባበርም እምውሉደ ኀነፊ አረማውያን -(ስንክ -ግን፯)

ኀነፋዊ -(ዊት ውያን ያት) የኀነፊ ወገን፤ አረመኔ ተንባላታዊ ወበመዋዕሊሁ ስተርአየት አሐቲ ብእሲት ኀነፋዊት። ንጉሠ ምስር ኀነፋዊ -(ዮሐ -መደ ስንክ -ጥቅ፳፩)

ኀኒቅ ቆት -(ኀነቀ የኀንቅ ይኅንቅ ዐረ ኀነቀ ሱር ሕናቅ ዕብ ሐናቅ) ማነቅ ማስጨነቅ፤ ጕረሮን ዐንገትን አጥብቆ ቅስቆ መያዝ ማሰር ለመግደል፤ አፍን አፍንጫን ማፈን መድፈን፤ ትንፋሽ መከልከል። ዐነቀን እይ፤ የዚህ ጎር ነው ለክፋም ለበጎም ይኾናል ኀነቀ ግን ለክፉ ብቻ ነው -(ማቴ፲፫ -፯። ፲፰ -፳፰ ፩ነገ፲፯ -፴፭) ኀነቀኒ አፈ መልስየ። ኀነቆ መንፈስ እኩይ። ወሰዶ እንዘ የኀንቆ ክሣዶ ወያረውጾ ጕጕአ። ንኅንቃ ለነፍስነ ወንለጕማ ከመ ፈረስ ኀያል ወድሩክ -(ኢዮ፴ -፲፰። ነገ -፲፮ -፲፬ ገድ -ተክ አፈ -ተ፴፩)

ኀናቂ -(ቂት ቅያን ያት ነቅት) የሚያንቅ ዐናቂ ዐንቆ ገዳይ

ኀንቦ -አንቦ፤ነብዐ አንብዕ።

ኀንገረ -ዐነከሰ ንካሳ ኾነ ተሸከመ እንኮኮ ወይም አሽኮኮ አለ እግር ለሌለው እግር ኾነ ማለት ነው በገድል በታምር በድርሰት ይገኛል

ኀንገር -(ዕብ ሒጌር) ዐንካሳ ልምሾ ጥምልምል፤ የሚድኽ የሚንፏቀቅ። ግሔ ሽኮኮ እግረ ኵንትሽ፤ ዐጫጭር ገሐየን እይ

ኀንጽጾ ጾት -(ኀንጸጸ የኀነጽጽ የኀንጽጽ። ሐንፈጸ) መጠርጠር ማውለብ፤ በጥርስ ማንጠርጠር ማበጠር ማንዘርዘር በሰፌድ በወንፊት -(ሉቃ፳፪ -፴፩) ማንጠጥ መቅረጥ፤ የቀንድና የንጨት

ኀንፈጠ [1]:- ጐፈጨረ፤ሐንፈጠ

[2]:-ቀረጠኀፊጥ ኀፈጠ

[3]-(ስሯጽ ግስ) ዐተመ፤ በማኅተም መታ ረገጠ ፈረመ። ወይም ሣለ መሰለ፤ ደፈ ቀረጸ በማኅተም ላይ።

ኀንፈጸ -አጐለበ፤ነፍጸ ሐንፈጸ

ኀወ -ኀወወ -(ኀዊው ከዊው ከወ ከወወ) ከፈተ ፋፈተ፤ ተከፈተ ክፍት ኾነ።

ኀወጸ -ጐበኘሐውጾ ሐወጸ

ኀዊሥ ሦት -(ኆሠ፤ ኀወሠ የኀውሥ ይኁሥ) መቀላቀል መደባለቅ አንዱን ንዱ ጋራ መለወስ መቀመም፤ እንደ ውሃና እንደ መሬት እንደ መድኀኒት።

ኀውሥ -ዝኒ ከማሁ። ቅልቀላ ድብለቃ ቅልቅልነት፤የባሕርይ ፍልሰት ዘእንበለ ውሥ -(ቄር -ገ፳)

ኀዘለ -ዐዘለ ተሸከመ፤ሐዚል ሐዘለ

ኀዘነ -ዐዘነሐዚን ሐዘነ

ኀዘዘ -ዐነቀ አስጨነቀሐዚዝ ሐዘዘ

ኀዝል -(ዐረ እልኀዚል) ጣብ የጨዎታ ስም፤ በጠጠር ወይም በተነጠጠ ዕንጨት የሚጫወቱት ጨዎት፤ እንደ ገበጣና እንደ ሰንጠረዥ ያለ -( - -፵፫ -፲፪)

ኀዝዐ -ነዳ አባረረ፤--ሐዚእ ሐዝአ

ኀየል -ዋሊያሀየል

ኀየሠ -ተሻለኀዪ ኀየሰ

ኀዪል ሎት -(ኄለ የኀይል ይኂል ዕብ ሓል ያሒል) መጮኽ ቡታ መስደድ ድረሱልኝ ማለት፤ ምጥና ጭንቅ የተነሣ ሕዝብን ሰራዊትን በጩኸት በቀንዳ መለከት መሰብስብ መጥራት፤ ወይም መጠራት ተካቶ መሰብሰብ። ወኄለ ኵሉ ሕዝብ ወተለውዎሙ -(ኢያ፰ -፲፮)

ኀዪስ ሶት -ኀየሰ ይኄይስ ይኂስ ረወ) መሻል መብለጥ ይኄይሰኒ መዊት እምሐዪው ይኄይሰክሙ እሑር ፈሪሀ እግ እምኵሉ ትኄይስ -(ጦቢ፫ -፮። ዮሐ፲፮ -፯። ሢራ፳፭ -፲፮)

 -ማማር መወፈር፤ ማሸብረቅ፤ ኀየሰት ፍስቶሙ ወሠነየት ራእዮሙ -(ዳን፩ -፲፭) በኀየሰ ፈንታ ተኀየሰ ይላል ስሕተት ነው ኢትፍቅድ ተኀይሶ እምኔሆሙ፤ አላ ኩን ዕሩየ ምስሌሆሙ -(ሲኖዶ)

ኀዪር ሮት -(ኄረ ኀየረ የኀይር ይኂር። ዐረ ኃረ) መቸር፤ መለገስ ፊት ለፊት እያዩ እያሳዩ መስጠት ማቅረብ፤ ማደል ማሳለፍ

ኀዪጥ ጦት -(ኄጠ የኀይጥ ይኂጥ) መሸንገል መደለል ማባበል በምክር በነገር ማሳት ማታለል በመብልዑ የኀይጠከ ኄጥዎሙ ለሕዝብ ወኦሆ አበልዎሙ ዑቁ ይኂጡክሙ በተጥባበ ነገር። ኄጦሙ ሰብእ በነገረ የውሀት -(ሢራ፲፫ -፯። ማር፲፭ -፲፩። ላ፪ -፰። ገድ -)

ኀያል -(ላን ላት የልት) ቁሙ፤ ኀይለኛ ዐርበኛ ጥኑ ብርቱ ንካራ ጕልበታም ኢይዘኀር ኀያል በኀይሉ ነፋስ ያል እብነ ድማስ ኀያል። እግዚአ ያላን። ሠለስቱ የልት -(ኤር፱ -፳፫ ኢሳ፲፩ -፲፭ ቅዳ መዝ -፵፯። ዜና -፲፩ -፲፬። ፪ዜና -፳፫ -)

 -ዐያሌ ብዙ እጅግ -(ግጥም በራስ ዐሊ ጊዜ) አንድ ሰው ሞተ አሉ በጋሎች ከተማ፤ ዐያሌ አይሞትሞይ ደስ እንዲለኝማ -(አያ -ዐሊ)

ኀያጢ -(ጢት ጥያን ያት) የሚሸነግል ሸንጋይ፤ አታላይ

ኀይል -(ላት) ቁሙ፤ ልበት ብርታት ናት ጥንካሬ ችሎት እመ ደክመ ይሉ ወስእነ በኵሉ ይልየ ኀይላቲሁ ዘውስጥ -(ሢራ -፲፱ -፳፰ ዘፍ፴፩ -፮። - -፵፭)

 -ምራት ድንቅ ሥራ ኀይላተ ብዙኀ ገበርነ ህጉር እለ በውስቴቶን ገብረ ኀይለ ብዙኀ በእንተ ኵሉ ዘርእዩ ይል -(ማቴ፯ -፳፪ ፲፩ - ሉቃ፲፱ -፴፯)

 -ብዕል ብዙ ገንዘብ፤ ጥሪት ድልብ። ይለ ደማስቆ እለ በልዑ እምነ ኀይላ በጽንዕየ ገበርኩ ሊተ ዘንተ ኀይለ ዐቢየ -(ኢሳ፰ -፬። ራእ፲፰ -፫። ዘዳ፰ -፲፯ -፲፰)

 -ውቀት ማያዊ ጸጋ፤ መንፈሳዊ ሀብት። ኀይል ታኄይል እስከ ትለብሱ ኀይሰ -(መክ -፲። ግብ፩ -፰። ግብ፩ -)

 -ራዊት ፍራ የጦር ሕዝብ ጓዝ ኢዮአብ መልአከ ይል። በኀይል ክቡድ ይለ ሰማያት። ኀይላት ዘዝ ዓለም -(፫ነገ - -፳፪ - ማቴ፳፬ -፳፱። ዕር -ኢሳ፬ -)

ኀይሎ ሎት -(ኀየለ ይኄይል የኀይል) ማየል መበርታት፤ መጐልበት ይለኛ መኾን፤ መድፈር፤ ማሸነፍ። ጽንዑ ወኀይሉ በዘይኄይል ድካምየ። ወሬዛ ዘይኄይላ ለድንግል -(፪ነገ - -፲፪ አርጋ ቀሌ)

 -መብዛት መበርከት፤ ዐያሌ መኾን። ድምፀ መጥቅዕ ይበልኅ ወይኄይል ቀ። ወኀየለ ሎሙ። እስከ ኀየሎሙ ደም -(ዘፀ፲፱ -፲፱ ሉቃ፳፫ -፳፫ ነገ -፲፰ -፳፰) በገበረ ፈንታ ተገበረ እንዲል  በኀየለም ፈንታ ተኀየለ ይላል ስሕተት ነው። ተኀየሉ ከመ ትባኡ ጽገዑ ወተኀየሉ እለ ይትኄየሉ በፈቃድ በተኀይሎ ተኀየሉ ንዋየ ክርስቲያን -(ሉቃ፲፫ -፳፬ ፪ዜና - -፯። ዘፀ -፲፰ ቄድር -ገ፴ ቀሌ)

ኀይመት -(ታት ዐረ ኀይም ኀይመት) ድንኳን፤ ማደሪያ ፀምር ክታን ከማእስ የሚሠራ፤ የጓዝ የሰፈር ቤት የሚነቀል የሚተከል፤ የሚታጠፍ የሚዘረጋ -(ዘፍ፲፰ - -፮። ዕብ፲፩ - ማሕ፩ -) ጳውሎስ ኮነ መስተገብረ ይመት ዐረብ እለ ይነብሩ በኀይመታት -(አፈ -ተ፳፮ ኖዶ)

ኀደመ [1]:-አንቀላፋሀዲም ሀደመ

[2]-ኀደመ፤ተረተ፤ሐድሞ ሐደመ

ኀደየ -አበሰለሀድይ ሀደየ።

ኀዲር ሮት -(ኀደረ የኀድር ይኅድር ቤተ ሓዳር ዐረ ኀደረ) ማደር ከሠርክ እስከ ነግህ ባንድ ቦታ መኖር፤ ተኝቶ ተጋድሞ ሌሊትን በንቅልፍ ማሳለፍ። ገሐሡ ቤተ ገብርክሙ ወኅድሩ፤ ወይቤልዎ ነኀድር ውስተ መርኅብ። ረቢ አይቴ ተኀድር፤ ወርእዩ ኀበ የኀድር -(ዘፍ፲፱ -፪። ዮሐ፩ -)

 -መግባት መክተት፤ ወደ ውስጥ ማለፍ ውሳጣዊ መኾን። ኀደረ ቤተ ነዳይ፤ ኀደረ ውስተ ማኅፀን -(ቅዳ -ዮሐ)

 -ከሰው መጠጋ፤ አሽከር ሎሌ ዐማች መኾን። ደረ ሐዱ ዐዱላማዊ -(ዘፍ፴፰ -)

 -መኖሮ መጽናት መተባበር መሰማማት የኀድራ አእባን ውስተ ንድቅ። ዘቦቱ የኀድር ሕንጻ ርእስ ዘቦቱ የኀድር ኵሉ ሥጋ ወይትዋደድ -(ሄርማ -ገ፱ ኤፌ፪ -፳፩ -፲፮ ላ፪ -፲፱) በኀደረ ፈንታ ተኀድረ ይላል፤ አያሰኝም ጽናፍ ዘይትኀደር እምሰማይ -(ምሳ፰ -፳፮)

ኀዲግ ጎት -(ኀደገ የኀድግ ይኅድግ ዕብ ሐዳል፤ ዐዛብ) መተው መጣል ይቅር ማለት፤ መፍታት መልቀቅ፤ ማራቅ። ሰበቀን እይ የዚህ ጎር ነው ለምንት ኀደገኒ ኅድግ ለነ በሳነ ኵሉ ዘየኀድግ ብእሲቶ አኀ ወኢትኅድጋ። ትኅድግ ምሕረተከ እምነ ቤትየ -(መዝ -፳፩ ማቴ፮ -፲፪ ራ፮ -፳፯)

ኀዳሪ -(ሪት ርያን ያት ደርት) የሚያድር ዐዳሪ እንግዳ ጥገኛ፤ ደባል ሎሌ አሽከር ቤተ ሰብ ፍረት ለኀዳሪ ሰሪቀ ማኅደር ዳሪ ዘአሐት ዕለተ ኀደረ ኀደርቱ ካህን ዳሪ ወገባኢ ባእ ኀዳሪነ ኀዳሪነ -(ሢራ፵፩ -፲፱ ጥበ፭ -፲፭ ዘሌ፳፪ -፲። ዘፀ፲፪ -፵፭ ራ፳፱ -፳፮ -፳፯)

ኀዳጊ -(ጊት ግያን ያት) የሚተው፤ ይቅር ባይ ኮነ ተሐራሜ ወኮነ ዳጌ ክርስቶስ ኀዳጌ ኀጢአት -(ስንክ -የካ፳፭። ቄር። - -)

ኀዳፍ [1]:-ማዥራት፤ሐዳፍ።

[2]-ኀዳፊ፤ -(ፊት ፍያን ያት) የሚቀዝፍ ቀዛፊ፤ መሪ ጠባቂ መምር ወኵሉ ዘኀዳፍ ዳፍያንኪ። ኅዳፌ ፍሳት ዳፍያነ ክርስቲያን -(ራእ፲፰ -፲፯ ሕዝ፳፯ -፰። ቅዳ -ኪዳ)

[3]-( አኅዳፍ) መቅዘፊያ ትርክዛ መያዣው እንደርፍ ጫፉ እንደ ድግር ያለ ዝርግ ጠፍጣፋ፤ ቀላል፤ ዕንጨት -(ሕዝ፳፯ -)

 -የመርከብ ዥራት በስተኋላ ኹኖ የመርከቡን ፊት የሚመልስና የሚቀልስ ወደ ወደዱበት የሚያስኼድ ይመይጦን ብእሲ በኀዳፍ ንኡስ ወያበውኦን ውስተ መርሶ ኀበ ፈቀደ -(ያዕ -)

-ዕውቀት ምክር፤ ሥልጣን። ዘሰ አጥረየ ዳፈ እለ ልቦሙ ኀዳፍ። እንቲኣከ ዳፍ አብ ትሠርዕ -(ምሳ፩ -፭። ፲፩ -፲፬። ጥበ፲፬ -) )

ኀድአ -ጸጥ አለሀዲእ ሀድአ

()          ኀድፎ -(ኀደፈ ይኄድፍ የኀድፍ። () ዘፈ) መቅዘፍ ባሕርን በትርክዛ መክፈል መሠንጠቅ፤ ታንኳን መርከብን መምራት ማስኬድ፤ ማዘዝ መጠበቅ፤ እንዳይሰጥም ከመ ዘየኀድፍ ውስተ ብዙኅ ሞገድ። ደፈቶ በንዋየ ምኑን ድፈኒ እማዕበሰ ኀጢአት፤ ዘይኄድፎ ዓለም ማዕበለ ጣውእ በራግናተ ወንጌሉ ቅዱስ -(ምሳ፳፫ -፴፬። ጥበ፲ -፬። ርጋ)

 -መወልወል ማደስ ማጽናት ነኀድፍ ልቦሙ መሀይምናን ወመንፈስ ቅዱስ ይኄድፍ ድፍ ልቦሙ በፈሪሆትከ ለኀድፎ ፍስ፤ -(ቅዳ -አት ሕር ቄድር -፲፩ ፶፫)

 -መምከር ማስተማር። ምስጢሩ ከመምራትና ከማጽናት ይገባል። ወኃጥኣን ይኄድፉ ሕብለ -(ምሳ፲፪ -)

-ጥፋት

ኀጢአት -( ጣውእ፤ ይእ) በቁሙ፤ በደል ዐመጥ ግፍ ሕገ ወጥ ሥራ፤ በኀልዮና በነቢብ በገቢር የሚሠራ። ተኀድገ ለከ ኀጢአትከ። ወይስረይ ለነ ኀጣውኢነ። ክልኤቲ ኀጣይእ። አአምር ሕማምከ ወኀጣይአከ -(ማር፪ -፭። ቅዳ ሢራ፯ -፰። ራእ - -)

ኀጢእ ኦት -(ኀጥአ የኀጥእ ይኅጣእ ዕብ ሐጣእ ሱር ሕጣእ። ዐረ ኀጢአ) ኀጢአት መሥራት፤ መበደል ሕግ ያዘዘውን መተው ያላዘዘውን ማድረግ፤ ጽድቅን መቃወም ትኅጣእ ፈድፋደ ለኄ ወለዘሂ የኀጥእ። ከመ ይኅጣእ ከመ ኢይኅጥኡ ለከ። ነፍስ እንተ ጥአት ይእቲ ትመውት -(መክ፯ -፲፯ - -፲፰። ዜና -፳፪ -፫። ኩፋ -፩። ሕዝ፲፰ - -)

 -ማጣት መቸገር፤ ፈልጎ አለማግኘት ዕጦተኛ አይቶ ዐጣ መኾን። ይግዕሩ ወየኀጥ እክለ። ይመውቱ በኀጢአ ማይ። አርመሙ ወኀጥ ቃለ እን ያወሥኡ ማሰነ ብሔር በኀጢአ ሰብእ ወእንስሳ -(ሰቈ፩ -፲፩ ኢሳ፶ -፪። ነሐ፭ -፰። ኤር፵ -፲፩)

ኀጢጥ ጦት -(ኀጠ፤ ኀጠጠ የኀጥጥ ይኅጥጥ ሐጸ ዕብ ሓጣጥ ወጋ በሳ ነቈረ) ጠጥ ጥቃቅን መኾን ማነስ መቅጠን። ኀጢጥና ሐጺጽ አንድ ናቸው ኆጻ ከነዚህ ወጥቷል

ኀጣኢ -(ኢት እያን ያት) ኀጢአት የሚሠራ ኃጥእ ኀጢአተኛ። ያጣ የሚያጣ

ኀጣጥ -(ዕብ አጣድ) በቁሙ፤ ዐጣጥ እሾኻም ንጨት እሾኹ ታናናሽ

ኃጥኣዊ -ኃጥኣዊ ዝኒ ዓዲ ማሁ ለእመ ርኢከ ማዌ ወኃጥኣዌ -(ፊልክ -፴፭)

ኃጥእ -(እት ኣን ኣት) ዝኒ ማሁ በቁሙ ኀጢአተኛ፤ ሕግ አፍራሽ ተላላፊ -(ዕጦተኛ ይቶ ዐጣ) ብእሲ ኃጥእ ብእሲት ኃጥእት ኃጥኣን ወመጸብሓን -(ሉቃ፭ -፰። -፴፯። ማቴ፱ -) አነ ወወልድየ ሰሎሞን ንከውን ኃጥኣነ ድኾች አይቶ ጦች፤ ወይም በቁሙ -(፫ነገ - -፳፩)

ኀጸረ -ዐጠረ ቀጠረሐጺር ሐጸረ

ኀጸበ -ዐጠበኀፂብ -ኀፀበ

ኀጸነ -አሳደገሐፂን ሐፀነ

ኀፀነ -አሳደገሐፂን ሐፀነ

ኀፀየ ዐጨ ሐፅይ ሐፀየ

()          ኀጺር -(ራን ራት ጻር) ዐጭ ታናሽ ድንክ ኵንትሽ ነውኆ ለዕፅ ጺር ዘበሕቁ ኀጺር ጺራት አጻብዒሁ -(ሕዝ፲፯ -፳፬ ዘሌ፳፩ - ሄርማ)

ኀጺር ሮት -(ኀጽረ የኀጽር ይኅጽር ዕብ ቃጻር ዐረ ቀጸረ) ማጠር ማነስ ዐጭር መኾን የቁመት የጊዜ አእባን እለ የኀጽራ ሶበ ዘኀጽራ እማንቱ መዋዕል -(ሄርማ -ገ፰ ማቴ፳፬ -፳፪)

ኀፂብ ቦት -(ኀፀበ የኀፅብ ይኅፅብ ዐረ ኀፀበ ቀለም አገባ) ማጠብ ጥራት ማንጻት። ይኅፅቡ አልባሲሆሙ። ኀፀብ በማይ ፀባ ለምድር እምኵሉ ርስሐት የኀፅቦሙ እግዚ ደቂቀ ጽዮን -(ዘፀ፲፱ -፲። ሕዝ፲፮ -፱። መቃ -ገ፯ ኢሳ፬ -) በኀፂ ፈንታ ኀፅበት እንደ ማለት ፀባ ይላል። ኢታስትት ኀፀ እገሪሆሙ ለአኀው -(ሲኖዶ -ኒቅ) በኀፀበም ፈንታ አስተኀፀበ ይላል፤ ስሕተት ነው ታአንግዱ በአስተኀ() () አላ በፍቅር -(አፈ -ተ፴፫)

ኀጺን -(ናት፤ ኀጻውንት) ብረት፤ የታወቀ ማዕደን፤ ከምድር የሚገኝ፤ ካፈር ከመሬት የሚወጣ ብርቱ ባድ ጥኑ ጠንካራ ብርትንና ብሩርን ተመልከት፤ ብረት ማለት ከዚያ የወጣ ነው ኀጺንም ከኀጸወና ከመሐጸ ከ፪ቱ ወጥቷል ወኀጺንሂ እምውስተ ምድር ይትገበር። ምድር እንተ እበኒሃ ጺን ምንሃብ ያሜክርዎ ለኀጺን -(ኢዮ፳፰ -፪። ዘዳ፰ -፱። ራ፴፬ -፳፮)

 -መቍረጫ መፍለጫ የብረት መሣሪያ ማናቸውም ኹሉበየስሙና በያይነቱ ብልኀ ጸራቢ ኀጺነ ወለኀጺናትሰ ገብሮሙ ሰንጐጐ ተፈትሓ ሎን ጻውንት ጻውንተ መስቀል -(ኢሳ፵፬ -፲፪ ገድ -ክ። ቄድር። አርጋ -)

ኀጺው ዎት -(ኀጸወ የኀጹ ይኅጹ ዐረ ኀጸ ሱር ሕጻእ) መቍረጥ መሰንጋት ማኰላሸት፤ መስለብ መጕመድ ጃን ደረባ ማድረግ፤ ራስን ወይም ሌላውን፤ መሐጸን እይ ዘየኀጹ ርእሶ በፈቃዱ። ብእሲ ዘኀጸወ ኀፍረተ ሥጋሁ በፈቃደ ርእሱ አው ጸላእቱ ጸውዎ -(ቀሌ - -፴፫ -፪። ማቴ፲፱ -፲፪)

ኀፃቢ -(ቢት ብያን ያት፤ ፀብት) የሚያጥብ ጣቢ፤ ቀለም አግቢ ኀፃቤ ብስ -( - -፴፮)

ኀጻዊ -(ዊት ውያን ያት፤ ጸውት) የሚሰልብ፤ ሰላቢ ራጭ

ኀጽድ ዶት -(ኀጸደ የኀጽድ ይኅጽድ ዐረ ሐጸደ፤ ዐሰደ) መጠምዘዝ ማረቅ ማጕበጥ፤ መጠቅለል፤ የሐረግ የንጨት የሽቦ የብረት

ኀፈሠ -ዐፈሠሐፊሥ ሐፈሠ

ኀፈነ -ዐፈነሩሐፊን ሐፈነ

ኀፈወ -ወዛሀፊው ሀፈወ

ኀፊር ሮት -(ኀፍረ ኀፈረ የኀፍር ይኅፈር ዐረ ኀፊረ ዕብ ሓፌር ሱር ሕፋር) ማፈር መፍራት፤ ከራቍትነት የተነሣ እንደ አዳም። መደንገጥ መለወጥ፤ ዐመድ መምሰል ከኀፍረት ብዛት የተነሣ። ኀፍረትን ዕርቃንን መሰወር መክደን።ኀፊረ ኢኀፍሩ ተዐቢ ፊሮትየ ኢየኀፍር ገጸ ክቡር ኢንኅፈር እምሢበተ ልሂቅ -(ኤር፮ -፲፭ ዘፀ፲ -፫። ኢዮ፴፬ -፲፱ ጥበ፪ -) በኀፍረ ፈንታ ተኀፍረ ይላል ስሕተት ነው ይግባእ ነዳይ ተኀፊሮ። መኑ ተአመነ በእግዚ ወተኀፍረ ይሑሩ ተኀፊሮሙ። ተኀፍሩ ነሀብት በእንተ ግልፎሆሙ። ይእተ አሚረ ትትኀፈር እምጌጋይከ -(መዝ -፸፫። ሢራ፪ -፲። ኢሳ፵፭ -፲፮ ኤር፲ -፲፬። ዘካ፫ -፲፩)

ኀፊድ ዶት -(ኀፈደ የኀፍድ ይኅፍድ ነደቀ ሐነጸ፤ ሣረረ) መገንባት መናስ መንደቅ ቤትን ግንብን፤ አስፍቶ አስረዝሞ አጠንክሮ መሥራት እንደ ባቢሎን ሕዝብ።

ኀፊጥ ጦት -(ኀፈጠ የኀፍጥ ይኅፍጥ ዐረ ኅበጠ ዕብ ሓባጥ ሱር ሕባጥ) መምታት መውቃት መደብደብ፤ የበትር መደሰቅ መሰጐድ መጠፍጠፍ የቡጢ የጥፊ ፍጣ አጥባተክን -(ኢሳ፴፪ -፲፪)

ኀፋሪ -(ሪት ርያን ያት) ያፈረ የሚያፍር፤ ዐፋር ደፋሪ ወኢኀፋሪ ብእሲት ኀፋሪት -(ግንዘ ሢራ፳፮ -፲፭)

ኀፋጢ -መኅፍጥ የሚመታ ተማች፤ ደብዳቢ ወቂ ደሳቂ

ኀፍረት -(ታት) ቁሙ፤ ዕፍረት ፍራት ከመ ኀፍረተ ሰራቂ ሶበ ይእኅዝዎ ማሁ የኀፍሩ ወከደነኒ ፍረት ገጽየ ኀፍረት እንተ ታመጽእ ኀጢአተ ወቦ ኀፍረት ለክብር ዘአልቦ ፍረት -(ኤር፪ -፳፮ መዝ -፵፯። ምሳ፳፮ -፲፩። መክ፰ -)

 -እድፍ ጕድፍ ገመና ነውር ስድብ ስንፍና፤ የሚያሳፍር የሚያስነቅፍ ነገር። ኢሜጥኩ ገጽየ እምኀፍረተ ምራቅ። ተዐገሠ ኀፍረተ መስቀል ኀፍረት ለነ እን ከመ ዛቲ ብእሲት ረኪበነ ተናገርናሃ። ገብረ ኀፍረተ ነገረ ኀፍረት -(ኢሳ፶ -፮። ዕብ፲፪ - ዮዲ፲፪ - ዘፍ፴፬ -፯። ቆላ፫ -)

 -ዕራቍት ዕርቃን፤ የወንድ የሴት ገላ አባለ ዘር አፈ ማሕፀን። ኢትክሥት ኅፍረተ ቡከ ወእምከ ከደንኩ ፍረተኪ ከመ ኢይሑር ዕራቆ ወኢያስተርኢ ፍረቱ -(ዘሌ፲፰ -፯። ሕዝ፲፮ -፰። ራእ፲፮ -፲፭)

ኁሠት -( ቀደ) መቀላቀል መደባለቅ አቀላቀል ቅልቅልንት፤ ድብልቅነት ኮነ ሰብአ ዘእንበለ ሠት ቱስሕት ወኁሠት -(ቄር -)

ኁሣሤ -ማሠሥ  መታሠሥ -( ) መሻት መፈለግ፤ መመርመር አመራመር። ምርመራ ምርማሪ መላ ግምት፤ ጥንቈላ ርት -(ኩፋ -፲፩)

ኁባሬ -ዝኒ ከማሁ ድማሬ ወኁባሬ -(ቅዳ)

ኁጻድ አው ኆጻድ -(ዳት ዕብ ቄሬስ፤ ዋው) ሜንጦ፤ ቀለበት፤ ዘለበት የድንኳን መግጠሚያ ማያያዣ፤ ማቈላለፊያ። ወግበር ጻዳተ ኀምሳ ዘወርቅ፤ ወደምር ዕጻደ አሐተ ምስለ ካልእታ በኆጻዳት ወይኩን ደብተራሁ አሐደ -(ዘፀ፳፮ -)

ኁፋሬ -ማፈር፤ ድል መኾን መሸነፍ ዕፍረት ፍራት ይዜከሮ እንከ ለኁፋሬሁ -(ማር -ይሥ፬ -)

ኍሉቍ -(ቃን ቃት ልቀት) የተቈጠረ ከቈጥር የገባእንዘ ኍሉቅ ምስሌነ ወምስሌሆሙ ኍሉቍ ተርፉ ይከውኑ ኍሉቃን። ሥዕርተ ርእስክሙ ኵሎን ኍሉቃት ማንቱ -(ግብ፩ -፲፯ ቅዳ -ሕር ኢሳ፲ -፲፱ ማቴ፲ -፴። ሉቃ፲፪ -)

ኍላቌ -(ቍያት) መቍጠር መቈጠር አቈጣጠር ቈጠራ፤ ቍጥር፤ ያእምር ኍላቌሁ ወኍላቌሁኒ ስድስቱ ምእት ስሳ ወስድስቱ -(ራእ፲፫ -፲፰)

ኍልቍ -ጥር ሒሳብ የስሙና በያኃዙ ልክና መልክ ውሳኔ ያለው ካንድ እስከ ምእልፊት በየቤቱ በየመክብቡ የሚጣፍና የሚነገር። በዝኀ እምኍልቍ። አልቦ ኍልቍ ለጥበቢሁ። በአምጣነ ልቆሙ ደቂቀ አስራኤል በኍልቈ መዋዕል ዘሰከብከ በኍልቈ ህጉሪከ አማልክቲከ (መዝ ፴፱። ፻፵፮። ሢራ፵፭   ፲፩። ሕዝ፬ ፬። ኤር፪ ፳፰)

ኈልቆ -ቆት (ኈለቈ ይኄልቍ ይኈልቍ ዐረ ኀለቀ ፈጠረ ለየ አስታወቀ በቍጥር ዕብ ሐላቅ ከፈለ) መቍጠር መተርተር መደመር ማብዛት መክፈል አኀዘንና ሐሰበን ተመልከት የዚህ አግዋር ናቸው ርኢ ከዋክብተ እመ ትክል ልቆትሙ አቡየሰ ይኄልቍ መዋዕለ ለቍነ ሎሙ ኵሎ ወደለውነ ብፁዕ ብእሲ ዘኢኈለቈ ሎቱ እግዚ ኀጢአቶ (ኵፋ ፲፬ ቢ፱ ፬። ዝ፰ ፴፬። መዝ ፴፩)

ኈላ -(ቍት ቍያን ያት) የማቈጥር ቈጣሪ ቍጥር ዐዋቂ

ኂሳን -መሻል ብልጫ ላቂያ። ኂሳነ ህላዌሁ ብዙኅ ኂሳኑ እግዚ እምሰብእ -(ቄር -ጰላ)

ኂረት -መቸር መስጠት፤ ቸርነት ደግነት ይኩን ኂረትኪ በሥነ ግዕ ወይዋሄ -(አፈ -ተ፳፰)

ኂሩት -(ታት) ቸርነት ደግነት፤ በጎነት። በኂሩተ ጻድቃን ትረትዕ ሀገር። ልቦ እኩይ ዘእንበለ ሩት ይኄይስ እከዩ ብእሲ እምነ ሩታ ለብእሲት ርእስ ኂሩታት -(ምሳ፲፩ - ኩፋ -፴፭። ራ፵፭ -፳፫ ፊልክ -)

ኂሩና ኂርውና ኄረውና -ዝኒ ከማ ሩት በኂሩና ፍሱ ምሕረት ወኂርውና ኢበቍዖ ርውናሁ -(ሢራ፵፭ -፳፫ አፈ -ተ፲፩። - -)

ኂጠት -መታለል፤ ማታለል መሸንገል ሸነጋገል ሽንገላእምኂጠተ ጸላኢ ትዐቀብ እመረ ከመ ውእቱ ኂጠ ምሰይጣን -(ኪዳ ንክ -መስ፳፩)

ኂጣን -ሽንገላ ድለላ፤ ጕሕሉት ተንኰል፤ ልዝብ ጥዑም ቃል ንባበ ደግ ምስጢረ ክፉ -(ፑሊቲክ) በኂጣነ ነገር ወበተየውሆ። በኂጣን ወተጥባበ ነገር። በትምይንት ወኂጣን በኂጣን እኩይ ኄጦ -(ሮሜ፲፮ -፲፰ ፩ቆሮ - -፩። አፈ -ድ፳፮ ቄድር -ገ፷፩)

ኄላ -የወይን ዘለላሄላ።

ኄሰ [1]-ነቀፈሐዪስ ሔሰ

 [2]-ነቀፈሐዪስ ሔሰ

ኄረወ [1]-(ይኄሩ ይኄሩ ኀየረ) ተቀጥላ ነው ቸረ ለገሰ ደግ ቅን መልካም ኾነ። ሶበ ኄረወ እግዚ ለደቂቀ እስራኤል። ኄርዎተ ነፍስ ይትሌዐል ላዕለ ኵሎን ኂሩታት። በኂሩቱ ለኖላዊ ይኄርዉ መርዔት -(መጽ -ምስ። ፈላስ -ገ፴፪። አዋል)

-በለጠ ተሻለ ደቂቀ አቡከ እለ ይኄርዉ እምኔከ ዕረፍተ ሞት ይኄሩ ሊተ ምግባራ ለዛቲ ሕይወት -(፪ዜና -፳፩ -፲፫ ፊልክ -፻፸፪)

[2]ቸረ ኀዪር ኀየረ

ኄር [1]-(ርት ራን ራት ዐረ ይር ዕብ ጦብ) ለጋስ፤ ደግ ቅን፤ በጎ ደኅና መልካም፤ ተንኰልና ክፋት ቢስነት የሌለው። ምንተ ትብለኒ ኄር በእንተ ር፤ አልቦ ኄር ዘእንበለ ሐዱ እግዚአብሔር ጻድቅ ወኄር ለቤተ አስራሌል። ብአሲት ርት። እኩያን ወኄራን የሐውር ፍናወ ዘኢኮና ኄርት -(ማቴ፲፱ -፲፮ ኢሳ፷፫ - ሣራ፯ -፲፱። ማቴ፭ -፵፭። ምሳ፮ -፲፪) ራን በማለት ፈንታ ራት ይላል የመላሽ ሕተት ነው -(ግብ፲፫ -፵፫። ፲፯ -)

 [2]-ቸርኀዪር ኀየረ

()          ኅለት -(ታት) ውስጠ ፍት ዘንግ ብርዕ አገዳ ቅልጥም ያለው የጐሽ መቃ ወይም ቀለም፤ ሸንበቆ ቀርክሓየመሰለው ኹሉ ራዊተ ኅለት ኅለት ዘዐቅም ዐቃቤ ኅለት። ብሔረ ኅለት ውስተ ኅለት ዘውጡሕ -(መዝ -፷፯ ሕዝ፵ -፫። ኢሳ፳፯ -፬። ፴፭ -፯። ኢያ፪ -)

 

ኅሉቅ -(ቃን ቃት ልቅት) ያለቀ የተጨረሰ፤ ቍርጥ። ኅሉቀ ወምቱረ ነገረ ሰማዕኩ። ሉቀ እነግር -(ኢሳ፳፰ - -፳፪ ኤር፲፰ -፯። ሮሜ፱ -፳፰)

ኅሉይ -(ያን ያት ሊት) የታሰበ ዕስብ

ኅሉፍ -(ፋን ፋት ልፍት) ያለፈ የኼደ እሴፎ ርአይክሙ ኅሉፈ ስመ ኅሉፍ ገጾሙ ለኢየሩሳሌም ካህናትሰ ኅሉፋነ ፍኖት -(ሮሜ፲፭ -፳፬ ሉቃ፬ -፶፫። ሆሴ፮ -)

 -የተለየ ልዩ ልውጥ እስመ ኮነ ኅላዌሁ ኅሉፈ እምኔሆሙ -(ገድ -ኪሮ) የታለፈ፤ የተዘለለ

ኅሊ ኅልያ -(ያት። ኀለየ) ኅሊና ሐሳብ፤ ምኞት ልብ የሚነቃ ነቅዐ ልብ፤ ውሳጣዊ ሕዋስ። ጽርየት ኅሊሁ ንጹሐ ሥጋ ወኅልያ ጽዱላነ ልብ ወኅልያ -( - - -፬። ንክ -ግን፲፱ የካ፮)

ኅሊና -(ናት። ኀለነ) በቁሙ ዝኒ ማሁ ሐሳብ ምኞት። ኅሲናሁ ዘከመ የሐርስ ትለሚሁ። ልብ እንተ ትወልድ ኅሊና እኩየ። ኅሊናት ዘሥጋ -(ሢራ፴፰ -፳፮ ምሳ፮ -፲፰። ይሁ -)

-የአፍኣ የውስጥ ሕዋስ ተነሣሽ ተንቀሳቃሽ ማለት ነው ሖሰንና ሎሰን እይ በእንተ ዐቂበ ኅሊናት ዘአፍኣ ውስጥ። ወግብረ ኅሊናት ዘውእቶሙ ነጽሮ ወሰሚዕ (አረጋ ድ፲፭ ማር ይሥ፳፪ )

ኅሊናዊ -የሐሳብ ሥራ፤ ኅቡእ ረቂቅ ውሳጣዊ ድብቅ፤ ካሳቢው በቀር ለሌላ የማይታወቅ ተውህበ ላቲ አእምሮ ብራት ሊናውያት -(ስንክ -ሚያ፲፩)

ኅላፍ -(ፋት) (ፋት) በቁሙ፤ የብራና ስሯጽ ቀንጃ ኹኖ ታጥፎ ተቀንፎ ባንድ ወገን፤ ወይም ተቀናጅቶና ተላልፎ በ፪ ወገን በጥራዝ መካከል የሚገባ ገጽ ያለው አንዳንድ ሉሕ ወይም ቅጠል ቀንጃና ቅንጁም ባይኾን አንዱ ቅጠል ታጥፎ ወስፌ ያለፈበት ሰንበሩ ኅላፍ ይባላል ሢራክን እይ

ኅልቀት -ኅልቀት፤ ማለቅ ተጨርሶ መጥፋት፤ መክሳት ማነስ መጕደል ዘተነበይከ በይሁዳ ኅልቀተ ኃጥኣን እምድር እምብዝኀ ልቀተ ሥጋሁ በእንተ አጽዋም -(ስንክ -ሐም፬ ገድ -ተክ)

 - መጨረሻ ፍጻሜ እስከ ኅልቀተ ዓለም -(፲፪ -)

ኅልቅ [1]-ረሮ ድሪምሐሊቅ ሐለቀ

 [2]-ኅልቅ፤ ዕልቀት ዕልቂት፤ ዕልቂያ ጥፋት። ቀርበ ዕለተ ልቆሙ -(ዘዳ፴፪ -፴፭)

ኅልድ -(ዳት። ዕብ ሔሌድ) ፋሮ ታናሽ አውሬ ምድር የሚፍር የሚቈፍር

ኅልፈት -በቁሙ፤ ማለፍ መኼድ፤ አስተላለፍ በኅልፈተ ዐውሎ የኀልፍ ብረትነ ሠረ ኅልፈተ ደመና ልፈቶሙ ውስተ ባሕረ ኤርትራ -(ምሳ፲ -፳፭ ጥበ፪ - አፈ -ድ፮)

 -መሞት፤ መውጣት፤ ከዓለም ሥጋ መለየት መታጣት እንዳልነበረ መኾን  ከመ ትዘከርዋ እምድኅረ ኅልፈትየ። ኅልፈተ ዝንቱ ዓለም -(፪ጴጥ - -፲፭ ስንክ)

 -መውጫ መጨረሻ፤ ፍጻሜ ኅልፈተ ዜያት ወዓመታት። ኅልፈተ መንግሥትከ እምከመ ሰምዐ ኅልፈቶ ለጊዜ ምንዳቤ -(ጥበ፰ -፰። ዮሴፍ። አፈ -ድ፩) በኅልፈትና በፍልጠት ፈንታ ተኃልፎት ይላል፤ አያሰኝም ፍስ ናሁ በጽሐ ተኃልፎትኪ እምሥጋ -(ማር -ይሥ፲፫ -)

ኅሙስ -(ሳን ሳት ምስት) ዐምስት የኾነ የተባለ፤ ካ፭ የተከፈለ ፭ነት ያለው

ኅሙይ -(ያን ያት ሚት) የታሰረ፤ እስር እስረኛ፤ ግዞተኛ። ወፈነዎ ሐና ኅሙዮ የሱስ ኅሙይ በእንቲኣነ -(ዮሐ፲፰ -፳፬ ደራሲ)

ኅማሴ -ዐምስት መኾን ዐምስትነት

ኅማዬ -ማሰር፤ መታሰር፤ አስተሳሰር እስራት። በእንተ ኅማዬከ በእደ አይሁድ ከመ ራቂ -(አዋል)

ኅምስ [1]-ዐምስት። የልክና የጊዜ ቅጽል፤ በቂ። ዕሥር ወኅምስ በእመት። ኅምሰ ቀሠፋኒ ይሁድ -(ዘፀ፴፯ -፲፪ ፪ቆሮ -፲፩ -፳፬)

[2]-(ዕብ ኤምጻእ ውስጥ መካከል ሖሜሽ ሱር ሑምሻሆድ የወገብና የጭን መገናኛ ብሽሽት ) በቍሙ ማሕፀን፤ አፈ ማሕፀን የሴቶች ዐምስተኛ ሕዋስ ፭ኛነቱም ካንገት በላይ ላሉት ላራቱ ነው ኅምሳ ለወላዲትከ ዘይፈትሕ ኵሎ ኅምስ -(ኩፋ -፳፭። ዘፀ፲፫ - -፲፪ -፲፫ -፲፭)

ኅምር -ዝኒ ከማሁ ለኀምር ቀይ ዐይነት

ኅምዝ -መርዝሐሚዝ፤ ሐመዘ

ኅሠፍ -(ፋት) ዕከክ ብግር፤ ኪንታሮት ስል የገላ ነውር

ኅሡሥ -(ሣን ሣት ሥሥት) የታሠሠ የተሻ የተፈለገ

ኅሱር -(ራን ራት ስርት) በቁሙ ያነሰ የጐደለ፤ ሕጹጽ። የተዋረደ ትሑት ወራዳ ስቋላ ምናምንቴ በእንተ ልባሲሁ ኅሱር ኅሱረ ነፍስ ረሰይኩክሙ ኅሱራነ ወለተ ባቢሎን ኅስርት -(ስንክ -ጥቅ፳፯ - -፳፮ -፰። ሚል -፱። መዝ -፻፴፮)

ኅሡፍ -(ፋን ፋት ሥፍት) ያከከ የታከከ ቍስላም ዕከካም -(ዘሌ፳፪ -፳፪)

ኅሳል -ልባብ፤ሐሲል ሐሰለ

ኅሥሥት -በቁሙ ዕሥሥት፤ የንሽላሊት ዐይነት መልኳ እንደ ሌታ ቀን የሚለዋወጥ ጠንቋዮች አጥበቀው የሚሿት

ኅሩይ -(ያን ያት ሪት) ተመረጠ ምርጥ ዳኛ አስታራቂ ዋይ ሩይ ወአልልኩ ኅሩይየ እምሕዝብየ ኅሩይ ዘይፈትሕ -(ቅዳ መዝ -፹፰። ኢዮ፱ -፴፫)

ኅሬ -መረጣ ምርጫ ምርጥነት። ስመ ገድ እስራኤል። ነገ -(ስንክ -ኅዳ፫) ዳግመኛም ኅሩይ ኅርየት በማለት ፈንታ ኅሬ ይላል -(ሮሜ፲፩ - - -፳፰)

ኅርመት -የፊደል ቅንጣት፤ አንዳንዱ ቅርጽ፤ በየስሙና በየመልኩ ልዩ ልዩ ኹኖ የሚጣፍ፤ ብቻ ብቻውን የሚቈጠርና የሚነገር ይህን የመሰለ የውጣ -(-) እንተ አሐቲ ኅርመታ ወአሐቲ ቅርጸታ -(ማቴ፭ -፲፰። ድጓ)  

 -ብቸኛ ቃል ንባቡ ፊደሉ ከነቍጥ እስከ ነቍጥ የሚጣፍ በነቍጥ የሚወስን አልፍ ቤት ገምል ድልት ሆይ ዋዌ ዛይ አብ ወልድ መንፈስ ቅድስት ሥላሴ አሐዱ አምላክ፤ ይህን የመሰለ ኢንኤዝዝ አሐተ ቃለ ሐተ ኅርመተ ይትወለጥ እምዘሀሎ ህየ -(ተረ -ቄር፲፭)

ኅርስ -ዐራስነት፤ ወሊድ ወለዳ፤ የወሊድ ወራት ርስሐት እስኪነጹ ድረስ ወይም ቀን የወንድ የሴት ልጅ በመዋዕለ ትክቶሃ ወኅርሳ ኢትቅረባ እንዘ ውእቶን ኢንጹሓት አምኅርሶን ፅኑሳቲሆሙ ይድኅፃ ወይድኅና በኅርሶን -( - - -፭። - - -፩። ኢዮ፳፩ -)

ኅርወት -(ታት) መብሳት መበሳት፤ አበሳስ ብስ ነዳላ ፍልፍል ቅርጥ። አሰርዎሙ ውስተ ኅርወተ ጕንድ ክቡደ እስረት፤ ብስ። ኅርወተ ዐይነ ማኅተም፤ ቅርጥ -(መቃ -ገ፪። ስንክ -ሠኔ፲፱። ዘፀ፳፰ -፲፩)

ኅርው -(ዋን ዋት ሩት) የተበሳ የተቀረጠ፤ ያበጠ የሰመጠ ወኅርው ሰኰናሁ በአምሳለ ጕንድ። ኅርው ዐይነ ማኅተም -(ስንክ -ኔ፬ ሢራ፵፭ ፲፩)

ኅርየት -መምረጥ መመረጥ፤ አመራረጥ መረጣ ምርጥነት፤ ፈቃድ። ሰብአ ኅርየት ኅርየተ ሠያጢ ዘቦቱ ኅርየት -( - -፬። ፴፫ -)

ኅሮ -መብሻ መንደያ መፈልፈያ፤ መቅረጫ ማንጠጫ፤ መሮ አፈ ምሣር ወስፌ፤ የመሰለው ኹሉ መጽሐፍ ግን በኅሮ ፈንታ ኅርወት ይላል ጸቍር አንፎ በኅርወት -(ኢዮ፵ -፳፩)

 

ኅቡል -(ላን ላት ብልት) የተደፈረ የተናቀ፤ ጥቁ። ክፉ እብድ ደፋር ጨካኝ። ኅቡላን ወዝሉፋን -(፪ጴጥ - -)

ኅቡረ -(ደቂቅ አገባብ) ብሮ ንድ ኖ፤ ባንድነት አንድጋ ዘበልዐ ኅቡ ይመውት ኅቡረ። ምስሌሆሙ ኅቡረ። ሶበ ይሄልዉ አኀው ኅቡረ። ኢታድርግ ኅቡረ -(አዋል መዝ -፪። ፻፴፪። ሢራ፯ -)

ኅቡር -(ራን ራት ብርት) ያበረ የተባበረ አንድ የኾነ፤ እኩያ ዐብሮ አደግ ባልንጀራ። ኅቡር ምስሌነ በዛቲ ጸጋ። ኅቡረ ህላዌ። ኅቡረ መንበር። ኅቡረ ካህንየ። ኅቡራነ ግዕዝ -(ቄር - ተረ ንክ -ሚያ፳፰)

ኅቡኣዊ -የውስጥ የልቡና፤ ጥልቅ ረቂቅ ኅሊና ኅቡኣዊት -(ፊልክ -፻፳፪)

ኅቡእ -(ኣን ኣት ብእት) በቁሙ፤ የታባ የተሸሸገ፤ ሽሽግ ድብቅ፤ ስውር ጥልቅ ረቂቅ መዝገብ ኅቡእ ወክቡት ኅቡእ ምዕጓለ መሕያው ምእመናን ኅቡኣን፤ ትምህርተ ቡኣት በእድ ኅብእት። በዐውሎ ኅቡእ -(ዮሴፍ ራ፲፩ -፬። ኪዳ ዘፀ፲፯ -፲፮ መዝ -)

ኅቡዝ -(ዛን ዛት ብዝት) የታበዘ የተጋገር ግግር

()          ኅባኔ -(ንያት) ቀሚስ፤ ያንገት የደረት ልብስ የቀሚስ ተካሪስ ኅባኔ ፀፈረ ውስተ ክሣድየ ይኩን መልበሱ ለካህን ርሒብ ዘእንበለ ኅባኔ። ጽሕሙ ኮነ ነዊኀ ወይበጽሕ እስከ ኅባኔሁ ትጥቅ -(ኢዮ፴ -፲፰። ሲኖዶ ስንክ -ግን፲፫ መዝ -፻፴፪) ልብሰ ምንኵስና፤ እንደ ሞጣሕት ያለ ባንገት ተጠልቆ ወደ ፊትና ወደ ኋላ እስከ የሚወርድ። የራስ ማሰሪያ፤ ጥምጥም መጠምጠሚያ። የልብስ ዘርፍ፤ የኩታ ጥለቱ ዕዳያቱ፤ ወይም ጥልፍ ዝምዝማት።

ኅባዝ አው ኅንባዝ -አጣብቂኝ የሥቃይ መሣሪያ፤ እንደ ወፍጮና እንደ ምጣድ ያለ፤ ዐላውያን ሰማዕታትን የሚሣቅዩበት። አዘዘ ዕርግዎሙ መልዕልተ ኅንባዝ ስከ ይውሕዝ ደሞሙ ዲበ ምድር። አዘዘ ያዕርግዎ ላዕለ ኅንባዝ ወየዐጽርዎ ሥጋሁ እስከ ውሕዘ ደሙ ከመ ማይ ዘዘ ይስቅልዎ ዲበ ኅንባዝ ወየዐጽርዎ በመንኰራኵረ እሳት ዘኀጺን ወሰበሮ መልአክ ኅንባዝ -(ስንክ -ሚያ፲፰ ግን፲፱ ሠኔ፬ -) ስሯጽ ኹኖ ገብቷል፤ የግእዝ መላሾች ዐረቡ ሐብ ሕቡብ ያለውን ሕባብ በማለት ፈንታ ሕንባብ እንዳሉት ኅባዝንም ኅንባዝ ብለውታል።

ኅብል -ድፍረት፤ ክፋት ጭካኔ።

ኅብስት -የተጋገረች እንጀራኀቢዝ ኀበዘ።

ኅብረት -(ታት) በቁሙ፤ አንድነት፤ ማበር መተባበር አንድ መኾን፤ መሰማማት። ኅብረተ ህላዌ። ኅብረተ ሥላሴ። ኅብረተ ዜማ። ኅብረተ ቃል። ኢይፈቅዱ ኅብረተ አበዊሆሙ -(ቄር -ጰላ። አርጋ። አዋል። - -፳፬)

ኅብር [1]-ቀለም፤ ዐይነት፤ሓብሮ ሓበረ

 [2]-ኅብር፤ -(ራት) ወገን ክፍል ዳርቻ የቦታ የሰፈር ውስተ ሐዱ ኅብር እምነ ገራህቱ ውስተ አሐዱ ኅብረ ሀገር። ኅብረ በድው። ኅብር ዘባሕረ ኪኔሪውት ኅብር ዘደብረ ኤፍሬም ቁም መንገለ የማን አሐደ ኅብረ -(ሩት፪ -፫። ፩ነገ - -፳፯ ዘኍ፴፫ -፮። ኢያ፲፫ -፳፯ መሳ፲፱ -፮። -ዕዝ፪ -፶፬)

ኅብአት -ማባት መታባት ሽሸጋ ድበቃ ከመ ኢይትከሀሎ ብአተ አበሳ ሰአሎ ኅብአተ ሀገር -(ጥበ፲ -፰። ዮሴፍ)

ኅብዝ -(ዛት ኀባውዝ ኅብ() ዝት ታት ዐረ ኹብዝ ዛት) እንጌራ ዳቦ ጠቢታ መጽሐፍ ግን በኅብዝና በኅብዝት ፈንታ ኅብስት ይላል በልማድና በጸሓፊ ስሕተት ገባ ነው ደነባ ገነባ ብሎ ደምብ ግምብ እንደ ማለት ኅብስተ ሰገም ኅብስተ ስንዳሌ ብስተ በረከት። ባውዘ ርባን -(መሳ፯ -፲፫ ዮዲ፲ -፭። ሲኖዶ ማቴ፲፪ -)

ኅቱም -(ማን ማት ትምት) ታተመ ዕትም፤ የተጻፈ ጽሑፍ የተዘጋ ዝግ ውር መጽሐፍ ኅቱም። ዕዳ ዘኅቱም ላዕለ ዘመደ ዕጓለ መሕያው ዐዘቅት ኅትምት ስመ ዕጽው ወኅቱም ገሩ -(ኢሳ፳፱ -፲፮። ንክ -መጋ፲፯ ማሕ፬ -፲፪ ዳን፲፪ -)

ኅትመት -ማተም መታተም አስተታተም ዕተማ ዕትማት፤ ቡራኬ ጸሎተ ኅትመት -(ቅዳ ንክ -የካ፯)

ኅትው -(ቱት ትውት ዋን ዋት) የበራ የተቃጠለ -(ሉቃ፲፪ -፴፭) አዕናቍ ኅትዋን -(ስንክ -ሠኔ፳፮)

ኅኑቅ -(ቃን ቃት ንቅት) የታነቀ የተጨነቀ፤ ታንቆ ታፍኖ የሞተ። ዘርዐ ትሩፋቲሆሙ ኅኑቅ በሦከ ዓለም። ምቱረ ልሳን በመጥባሕት ወኅኑቀ ርዔ በእድ በሊዐ ወኅኑቅ -(ፊልክ -፫። ንክ -ጥቅ፭ -፲፰። - -፳፫)

ኅንቅርት [1]-በቁሙ፤ ዕንቅርት፤ ኵልኵልት ያንገት የማንቍርት ቀጥላ ጕረሮ የሚያንቅ የሚያስጨንቅ -(ተረት) የግፍ ግፍ በንቅርት ላይ ደግፍ። ኅንቅርት ዘወፅአ በክሣዱ -( -) ከኀነቀና ከነቀ የተዴቀለ ነውና ነቀረንና አንቀረን እይ

[2]:-ከውር፤ሕንቅርት ነቀረ

ኅንቀት -ማነቅ መታነቅ አስተናነቅ፤ ዕንቂያ ዕንቂቅ ድንገተኛ ሞት -(ስንክ -ም፪ መጽ -ምስ) ኅንቀተ ፍትወት -(ግንዘ)

ኅንባብ -ፍሬሐንበበ

ኅንንት -ዕንቅርት ያንገት ደዌ

ኅንጻጽ -(ጻት) ጥርጣሪ እንጥርጣሪ ንፋሽ ገለባ ልቃሚ ብጣሪ ኑፋቄና ኅንጻጽ ባማርኛ ይተባበራሉ። -(ግጥም፤ አቶ ይፉ ድተዋል ተብለው ከታ በኋላ በፍቅር መጥተው ሲገናኙ) አለጊዜው ጊዜ ማን እሸት ምጥቷል፤ በዚህ በቤታች ጥርጣሪ መልቷል። የእሳት ፍንጣሪ፤ የምጣድ ብልጭልጭታ። ቀለምጺጸን እይ

ኅዋ -( ዋኅው ዕብ ሖዋሕ ሐዋሒም) ነቅ ሥንጥቅ በቁሙ፤ ክፍት ባዶ ወለል የቤት የደጃፍ የር የሰማይና የምድር መካከል የርጉዕ ነፋስ መጣፍ ግን በኅዋ ፈንታ ዋኅው ይላል ኅዋኅወ ሰማይ። ኅዋኅወ ፈለክ ኅዋኅወ ቤተ ክርስቲያን -(ሔኖ አቡሻ። ቅዳ)

ኅዉሥ -(ሣን ሣት ውሥት) የተቀላቀለ ቅልቅል፤ ድብልቅ ቅይጥ ኀጺን ወልሕኵት ኅዉሥ ከማሁ ኅዉሣን በዘርዐ ዕጓለ መሕያው ምጽአ ኅዉሠ ርቤ ወዐልወ አፈዋተ ርቤ ዉሥ -(ዳን፪ -፵፫። ዮሐ፲፱ -፴፱ ቅዳ -አፈ)

ኅዉር -(ዐረ ኀዋር) ደካማ ድዉይ ቀጭን ኰሳሳ ወአነ ኅዉር እምሕል ለክሙ -(ጦማር)

ኅዩል -ኅዩል -(ላን ላት ይልት) የበረታ ብርቱ ብዙ ኀይለኛ። ኅዮለ ማየ ኅዩል ውእቱ ማዕበል ኅዩል -(ጥበ፲፫ - -፬። ፲፱ -)

ኅዩጥ -(ጣን ጣት ይጥ) የተታለለ የተሸነገለ ተላላ ሽንግል

ኅዱር -(ራን ራት ድርት) ያደረ የኖረ የሰፈረ ወኵሉ ምግባረ መንፈስ ኅዱር ውስተ ሥጋሁ ኩን ምስሌሆሙ ኅዱረ ኅዱራን ምድር -(ኦፈ -ድ፲፭ ፊልክ -፻፹፩። መዝ -)

ኅዱግ -(ጋን ጋት ድግት) የተተወ የተሰረየ፤ የተፈታ የተለቀቀ፤ ልቅ ስድ። ኀጣይኢሃ ኅድግት። ብእሲት ኅድግት። ወዘሰ ኅድግት አውሰበ -(ፊልክ -፴፭። ኢሳ፶፬ -፮። ማቴ፭ -፴፪) ዱግ ኩር በማለት ፈንታ ኅዳግ ይላል፤ አያሰኝም -(መዝ -፸፯። ኢሳ፳፬ -)

ኅዱፍ -(ፋን ፋት ድፍት) የታደፈ የተቀዘፈ፤ ጥብቅ

ኅዳር -(ዕብ አዳር፤ መጋቢት። ቅብጥ አቶር) በቁሙ፤ የወር ስም የመስከረም ሦስተኛ፤ ያዝመራ ወራት ጠባቆች ከዱር የሚያድሩበት ሰሙኑ ለኅዳር መንፈቀ ኅዳር። -(ስንክ -ኅዳ፰ ፲፭)

ኀዳሪ (ሪት ርያን ያት ደርት) የሚያድር ዐዳሪ እንግዳ ጥገኛ ደባል ሎሌ አሽከር ቤተ ሰብ ፍረት ለኀዳሪ ሰሪቀ ማኅደር ዳሪ ዘአሐት ዕለተ ኀደረ ኀደርቱ ካህን ዳሪ ወገባኢ ባእ ኀዳሪነ ኀዳሪነ (ሢራ፵፩ ፲፱ ጥበ፭ ፲፭ ዘሌ፳፪ ፲። ዘፀ፲፪ ፵፭ ራ፳፱ ፳፮ ፳፯)

ኅዳግ -(ጋት) በቁሙ የመጽሐፍ እግር ከቀለሙ በታች እጅ የሚያርፍበት ባዶ ብራና ፋቱ ከአርእስትና ገጽ ከግልየት የሚበልጥ። ሥርው ጥንት። ንግባእኬ ኅዳገ ነገር (መጽ ምስ)

ኅዳጥ [1]-(ኅጣጥ፤ ጣን) ጥቂት፤ ትንሽ ብዛት የሌለውማእረሩሰ ብዙኅ ወገባሩ ኅዳጥ ወኅዳጣን ኅሩያን። በእንተ ኅዳጥ ኀጢአ -(ማቴ፱ -፴፯። -፲፮ ኢሳ፶፯ -፲፯) ሕድ ክልኤ ማለት ፈንታ ኅዳጥ ይላል፤ ፍሬ ፍሬ እንደ ማለት ነው ኅዳጥ የአክል በኅዳጥ ዓሣ -(ሉቃ፲ - ቅኔ)

[2]-ጥቂትጣጥ ኀጠ ኀጠጠ

ኅዳፌ -መቅዘፍ፤ መቀዘፍ አቀዛዘፍ ቀዘፋ። ትእዛዝ ውቀት ፈሊጥ። በኅዳፌ ይከውን ጸብእ -(ምሳ፳፬ -)

ኅድረት -ማደር መኖር አስተዳደር ዐዳር ትዳር ኑሮ በእንተ ድረተ አኀው ወኅድረቶሙ ለእስራኤል -(ፊልክ -፻፹፩ ፀ፲፪ -)

ኅድገት -(ታት) ( ) መተው መጣል መፍታት መፈታት አፈታት፤ ዕረፍት፤ ስሬት። የሥራ፤ የሴትየኀጢአት ከመ ትጸውዕ ድገተ ዓመተ ኅድገት በእንተ ከሊአ ድገተ ብእሲት ድገተ አበሳ -(ኤር፵፩ -፰። ዘሌ፳፯ -፲፯። - -፳፬። ቅዳ) በኅድገት ፈንታ ኅዳጋቅ ይላል፤ ስሕተት ነው። ወገብረ ኅዳጋቲሃ ኵሎ ደወለ መንግሥቱ -(አስቴ፪ -፲፰) በሚገዛው አገር ላለው ሕዝብ ኹሉ ዕረፍት ነጻነት ሰጠ ግብር አቀለለ ማለት ነው

ኅድጋን ኅድገት -ፍች ልቅ፤ የባልና የሚስት መለያየት፤ የጋብቻቸው ውል መፍረስ መጽሐፍ ግን ኅድጋን ገት በማለት ፈንታ ኅዳጋት ይላል፤ የተሳሳተ ነው መጽሐፈ ኅዳጋት -(ዘዳ፳፬ -፩። ኢሳ፶ -፩። ማቴ፭ -፴፩። ማር፲ -) ፍልጣንን እይ የዚህ ጎር ነው

ኅጠት [1]-(ታት። ኆጻ፤ ኆጻት) ቅንጣት ናሽ ፍሬ ያሸዋ የእኽል የሌላውም ኹሉ ኅጠተ ኆጻ ጠተ ጼው ኅጠተ ዘርዕ እኩይ ጠተ  ስናፔ ኅጠተ ሥርናይ -(ሢራ፲፰ - ንክ -ሐም፯ ሱቱ -ዕዝ፪ -፴፰። ማቴ፲፫ -፴፩። ዮሐ፲፪ -፳፬) ኅጠታተ ዕጣን ንኳር ቈቀር ኅጠታተ ዛጐል -(ቅዳ - -፵፮)

 [2]-ቅንጣትኀጢጥ ኀጠ ኀጠጠ

ኅጥሜ -(ዐረ ኂጥሚይ) ሰላጣ ሥንቆ የወፍ ዘረር ማናቸውም ቅጠላ ቅጠል በጨው የሚጣፍጥ ባለብሉዮች ግን የጐመን ዘር ጥማቂ ይሉታል -(ኢዮ፮ -)

ኅጥእና -ኃጥእነት አይቶ ዐጣነት -(ፈላስ -ገ፹፪)

ኅጸር ኅጽረት -ማጠር ዕጥረት ዐጭርነት -(ሔኖ፸፪ -፳፫ - -፴፯) በእንተ ኀጽረተ እደዊሆሙ ወበአንተ ዘአልቦሙ ክሂል ይትዔረይ ሌሊት ምስለ መዓልት በኑኀት ወበኅጽረት -(ዮሴፍ አቡሻ -፲፬)

ኅጹር -(ራን ራት ጽርት) ያጠረ ዐጭር፤ ታናሽ ጥቂት ዘመን ኅጹር ነገር ኅጹር እስመ ኅጹር ዕለትየ በኅጹር ዘዝኩክሙ ኅጹረ እነግረከ -( - - ፪ቆሮ - - ዕብ፲፩ -፴፪። ግብ፳፬ -)

ኅፁብ -(ባን ፅብት) የታጠበ ጠራ ንጹሕ ጥሩ ወኅፁብ ሥጋነ በማይ ንጹሕ ልባስ ኅፁብ -(ዕብ፲ -፳፪ ንክ -መጋ፫)

ኅፃብ -(ባት) ዕጣቢ እድፍ። ማየ ኅፃቤሁ ኮኖን በቍዔተ ለአዋልደ ዮሴፍ በኅፃበ እግሩ -(አረጋ -ድ፳፬ ስንክ -ግን፰)

ኅፅበት -ማጠብ፤ መታጠብ፤ አስተጣጠብ ዐጠባ ዕጥበት ስርየት ጥምቀት ኅፅበተ ሥጋ ኅፅበተ እግር ኅፅበተ ኀጢአት። ኅፅበት ዘዳግም ልደት -(፩ጴጥ - -፳፩። ፊልክ -፻፲፬ ኪዳ ቅዳ -ኤጲ)

ኅጽወት -መስለብ መሰለብ፤ ጃን ደረባ መኾን ማድረግ ፈቀደ ጽወት -(ፊልክ -፪፻፴)

ኅጽው -(ዋን) የተሰለበ ስልብ ጐማዳ ጃን ደረባ። ከመ ኅጽው ሶበ የሐቅፋ ድንግል በእንተ ኅጽዋን ወግዙራን እስመ ጽዋን -(ሢራ፴ - - -፴፫ ማቴ፲፱ -፲፪። ግብ፰ -፳፯)

ኅፉር -(ራን ራት ፍርት) የታፈረ የተፈራ፤ ፋሪ ተፈሪ። ያፈረ የፈራ፤ ኀፍረት የያዘው እስመ ኅፉራን እሙንቱ ሖሩ ፉራኒሆሙ ዘኅፉር ገጻ -(፪ነገ - - አፈ -ተ፲፫ )

ኅፍጠት -የማኅተም ቅርጽ፤ ጥፈት ልክ ልቦ ፍልጠት ውስተ ኅፍጠት ዘአርኣያ ንጉሣዊ ማእከለ ዘተኀትመ በማኅተመ ወርቅ ወማእከለ ዘተኀትመ በማኅተመ ኀጺን ወኢይትዐወቅ እምኔሆሙ ዘኅቱም በወርቅ እምዘኅቱም በኀጺን -( - -)

ኆኄ -ስመ ፊደልሆሄ -

ኆኅ -( ኃት ዐረ ኀውኅ ሱር ሓውሓ ዕብ ሖዋሕ፤ሦክ) የባሕር እሾኻም ፍሬው ጥቍር፤ ዘይቶንና ዘቢብ የሚመስል፤ ተምር የሚያካክል። ቈጽለ ኃት። ጽለ ኃት -(ቀሌ ግንዘ)

ኆኅት -( ኃት ኀዋኅው ዐረ ኀውኀት ታናሽ ጠባብ መስኮት ፉካ፤ ዐይን የሚያስልክ እጅ የሚያሾልክ፤ ነፋስና ብርሃን የሚያገባ ደጃፍ በር፤ የቤት የቅጥር መውጫ መግቢያ ባዶው ክፍቱ ሳንቃ የሚከድነው መዝጊያ የሚደፍነው። ንቀጽን እይ የዚህ ጎር ነው ነቅጾ ኅተ አንቀጽ ለኵ ዘመጽአ ርኅው ኅትየ ባእ ቤተከ ወዕጹ ኅተከ ይትረኀዋ ኃት እለ እምፍጥረት። ርኀወ ኆኃተ ሰማይ ስመ ሰበረ ኃተ ብርት -(ኪዳ ኢዮ፴፩ -፴፪። ኢሳ፳፮ - መዝ -፳፫ ፸፯ ፻፮)

ኆሠ -ነቀነቀሐዊስ ሖሰ።

ኆር -(ዕብ ሖር) ብስ ነዳላ፤ ታናሽ ጠባ መስኮት -(ሕዝ፰ -)

ኆኖፌ -መናፍቅ፤ ገበር ጓጕ ሕዝብ ይማኖቱ የተበላሸ፤ እንደ ቅማንት እንደ ተንባላት ያለ ወደጐጾሙ በኅቡእ ፍኖት ለእለ ኆኖፌ -(አፈ -ድ፪ ተግ፬)

ኆጻ [1]--አሸዋኀጠ ሐጸ ኀወጸ

 [2]-(ኀጢጥ ኀጠ፤ ሐጸ። ዐረ ሐጸን ሱር ሕጻጻ ዕብ ሓጻጽ) ጠጠር አሸዋ ድቡሽት ታናናሽ ጥቃቅን የደንጊያ ቅንጣት እንደ ጤፍ ምርት እንደ ርት ዶቄት ያለ በወንዝ ዳር በባሕር ጠረፍ በምድረ በዳ የሚገኝ ጥሬነቱ ከኀጢጥና ከሐጺጽ የተዴቀለ ነው፤ ኀጠንና ሐጸን ረመለን እይ። በዓለ ስፈሬዳት ወኆ ደራቅ። ኮነ ይወዲ ኆጻ ንስቲተ ውስተ አፉሁ። ከመ አህ፣እቲ ኅጠተ ኆጻ እምውስተ ኆጻ ባሕር ወደፈኖ ውስተ ኆጻ ሐነጸ ቤቶ -(ፊልክ -፴። ፷፱። ራ፲፰ -፲። ፵፬ -፳፩። ዘፀ፪ - ማቴ፯ -፳፮)


No comments:

Post a Comment

ማውጫ

ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ