~ደ~

                                 

-አራተኛ ፊደል በግእዝ አልፍ ቤት በአበገደ፤ ስሙ ድል() ት፤ ቍጥሩ አራት፤ አኃዝ ኾን አርባዕት ይባላል ዕብራውያን ግን አራትን መደብ አድርገው በራሱ ላይ ነቍጣ እየጨመሩ አራት እልፍ ይሉታል። ምስጢሩ ረቡንና የረቡን ፍጥረት መደብ አድርጎ ምስጢረ ሥጋዌን ያሳያል። -(ዘፍ፩ -፲፬ ዮሐ፩ -)

ደሀለ -ሸሸደሐለ።

ደሐሰ -ዳሰ ፈጨ ረገጠፅሒስ ፀሐሰ

ደሐረ -መረቀ ድኂር ደኀረ።

ደሓሪ -(ሪት ርያን ያት ሐርት) የሚድር፤ የሚፈታ፤ የሚሰድ የሚያባርር።

ደኃሪ -(ሪት ርያን ያት፤ ኀርት) ኋላኛ የኋላ መጨረሻ፤ ታናሽ ተከታይ። አግሪጳስ ውእቱ ደኃሪ እምእለ ነገሡ በይሁዳ ደኃሪ ጸላኢ ደኃሪተ ገመስ እሙንቱ ደኃርያን ቀደምት ወደኀርት -(ዮሴፍ። ፩ቆሮ -፲፭ -፳፮። ማቴ፭ -፳፮ ዘኍ፪ -፴፩። ዜና -፳፮ -፳፪)

ደኃራዊ -ዝኒ ከማሁ፤ ህርቃኖስ ደኃራዊ ያቅም ደኃራየ -(ዮሴፍ። ዕብ፲ -)

ደሐየ -ፈረደኀየ ደኅኀ።

ደኀየ -(ደኅኀ) ፈረ ማሰ አወለቀ የጕድጓድ ረየ ወደኀየ ጸናሒ ዘይድኂ ወይድኅይዎሙ -(መዝ - ደራሲ። ዲድ -፲፯)

ደሓዪ መድሐዪ ሕይ -የሚፈጭ ፈጭታ፤ ባለወፍጮ።

ደኃፂ ድኁፅ -(ፃን ፃት ኅፅት) የዳጠ፤ የተሰናከለ። የተዳጠ የተደፈጠጠ። የሚድጥ ዳጭ -(ገቢር)

ደለወ -(ዐጕል) ኾነ ተገባ ደላ ተመቸ ተስማማ። -(ገበዘ ተገበዘ ግብዝ ኾነ) ዘይደሉ መልእክተ ኵሉ ለከ ይደሉ ስብሐት። ወደለዎ ብሔር -(ጥበ፲፭ -፯። መዝ -፷፬። ሉቃ፲፪ -፲፮)

ደለው -(ዐረ እደለው) ኮከብ ደላዌ ማይ ሐያቢ በዓለ ማሕየብ ማለት ነው መልኩ በሥዕል ሲያዩት ውሃ ቀጅ ይመስሳል ኮከብነቱም የጥር ነው፤ ፀሓይ ጋራ ፳፱ ዕለት ኬክሮስ ይመግባል -(አቡሻ -)

ደሊላ -(ዕብ ድሊላ) -(350) -(ዕብ ድሊላ) ቀጭነን መድ ፈትል፤ ወይም ሥሥ ረቂቅ መንዲል የጠጕር ማሰሪያ መሸፈኛ የሶምሶን ሚስት -(መሳ፲፮ -) ስሟ እንደ ትንቢት ኹኖ ተነግሯል

ደሊቅ ቆት -(ደለቀ ይደልቅ ይድልቅ ዐረ ደሊቀ። ዕብ ዳላቅ፤ ነደ) መታወክ መናወጥ፤ መጋለብ መውለብለብ የባሕር የእሳት በቁሙ፤ መደለቅ መምታት፤ የከበሮና የርግጫ

ደሊው ዎት -(ደለወ ይደሉ ይድሉ ዐረ ደላ ሱር ድላ ዕብ -ዳላህ ሔበ) መጥለቅ መቅዳት፤ መሳብ መጐተት ከጕድጓድ ከጥልቅ ከዐዘቅት ማውጣት ማንሣት መስቀል ማንጠልጠል፤ መመዘን መለካት ማስተካከል -(ማዘጋጀት፤ ማሰናዳት) ወደለዉ፤ ዐስብየ። ደለውኩ ሎቱ ወርቆ። ወደለውኩ ሎሙ ወርቀ ወብሩረ። ደለውከ ቃለከ በመዳልው ወትደልዎ -(ዘካ፲፩ -፲፪ ኤር፴፱ - ዕዝ፰ -፳፭። ራ፳፰ -፳፭ ሕዝ፭ -) ዳግመኛም በቀደሰ ቤት ደልዎ፤ ደለወ ይዴሉ እያለ በ፪ መንገድ ይኼዳል ተደለወና መደልው የዚህ አንጻር ናቸው

ደላዊ -(ዊት ውያን ያት) የሚመዝን መዛኝ ውሃ ቀጅ ባለማሕየብ

ደልሎ ሎት -(ደለለ ይዴልል ይደልል። ዕብ ዳላል ታላል) መመየድ፤ መከፍከፍ፤ ጠጕርን በሚዶ ማበጠር ማጐፈር፤ መበተን ማጐተን መንቀስ መከናከን፤ ለቤት ክዳንም ይኾናል ወይም መሥራት መጣስ፤ መሸረብ መጐንጐን፤ መፍተል መቈንደል። በቁሙ መደለል ማታለል፤ መሸንገል። -(ተረት) ዶሮን ሲደልሏት በመጫኛ ጣሏት። ደላል ደላላ፤ ድላል ደለል ማለት ዚህ ወጥቷል።

ደልጎ ጎት -(ደለገ ይዴልግ ይደልግ ዕብ ዳላግ ዳላቅ) መዝለል -(ጥወ) መወርወር፤ ዘሎ ተራምዶ ማለፍ፤ መፍጠን መቀልጠፍ መናር መጓን ላም እንዳየ አንበሳ መኾን ያርበኛ። ማዘለል መወርወር አርቆ መጣል፤ የፍላጻ የጦር ንኅረይ ርእስነ ኅሩያነ ሰብአ እለ ይዴልጉ ውስተ ቀትል ወንሑር ዕሌሁ ወንትቃተል ምስሌሁ -(ኩፋ -፴፯)

ደመ ሰማዕት -ስለ ሃይማኖት በግፈኞች እጅ የሚፈስ የምእመናን ደም 

ደመ ትክቶ -የሴቶች ግዳጅ፤ ባሕርያዊ ምንጭ አበባ በየወሩ ቀን የሚታይ።

ደመ ነፍስ -የሰው የንስሳ ደም፤ ከዕፀዋት ደም የተለየ በደም የሚሣል እንስሳዊ አእምሮ

ደመ ኪዳን -የግዝረት የመሧዕት ደም ኪዳን ስለ ማጥናት የሚፈስ

()          ደመመ -(ይዴምም ይደምም ደምሞ ዐማርኛ) ዘጋ መረገ ደፈነ መላ ቈለለ አስተካከለ፤ ደመደመ። የመቃብርና ያቀባበር ደምመው እንዲሉ ድፈነው አስተካክለው ሲሉ -(ሙሾ መነኵሲት በወሊድ ሙቃ ስትቀበር እኅቷና አክሥቷ) አንቺ ሞኝ አንቺ ሞኝ አንቺ ሞኝ ተላላ፤ የኋላዉን በፊት የፊቱን በኋላ ያማወቷን ነገር ምን አጠያይቋችኹ እንዲያው ቅበሩ እንጂ እየደመማችኹ።

ደመራ ድምር -(ዐማርኛ) ቁሙ የበዓለ መስቀል ዋዜማ ዕንጨቶች የሚደመሩበት።

ደመቅ -ድቃቂ ስባሪ እንክትካች። ወትገብር ደቃቀ ወደመቀ -(ኢሳ፴ -፳፪)

ደመና -(ናት) በቁሙ ከርጥብ ምድር የሚወጣ ጢስ በት ተሰብስቦ ከጠፈር በታች ኅዋ የሚታይ፤ ጠፈርን የሚሸፍንና የሚጋርድ። ደመና ዐቢይ ደመና ሰማይ ደመና ዝናም ደመናት ያውሐዙ ጠላተ -(ሕዝ - -፬። ዳን፯ -፲፫ ራ፴፪ -፳፮ ምሳ፫ -)

-ብዙ ብዛት መዐት። ደመና ቋዓት። ደመና ዘናቢር ወትንንያ -(ኩፋ -፲፩ ስንክ -ጥር፲፰)

ደመንሚን -ጨለማ ድግዝታ ምሼት ማታ የጉም ያፈና ጊዜ ቦታ፤ የማይታይ ነገር ደመንሚነ ይመስል ብዙኃን -(ተረ -ቄር፲፱)

ደሚሕ ሖት -(ደምሐ ይደምሕ ይድማሕ ዕብ ዳማህ፤መሰለ) መጥለቅ መስመጥ ወደ ውስጥ መግባት ልቆ ማወቅ መመርመር። መቅዳት መጨለፍ። ኢታአምርኑ እግዚኦ ልባበ ሰበ ዘእንተ ትደምሕ ኅሊናነ -(ተረ ቄር፲) ደምዐን ተመልከት፤ የዚህ መንቲያ ነው

ደሚም ሞት -(ደመ ደመመ ይደምም ይድምም ዕብ ዳማም) መድመም -(ጥደ) መደመም፤ መደነቅ መገረም፤ መደንገጥ መፍራት ዝም ዕክም ጸጥ ማለት መፍዘዝ አፍን መያዝ፤ የክፋ የበጎ -(ድም ማለት፤ መጮኽ መፈንዳት) መጽሐፍ ግን በደመ ፈንታ ተደመ ይላል ያማርኛ ነው። አንክረ ወተደመ ታነክር ወትዴመም ተደሙ እምነ ሥና ንዘ ይዴመሙ ጥቀ -(ዮሴፍ። አፈ -ተ፳፰ ዮዲ፲ - ጥበ፲፯ -)

ደሚስ ሶት -(ደምሰ ይደምስ ይድምስ። ዐረ -ደመሰ። የደመነ ሞክሼ) መጥቈር፤ መጨለም መክበድ

ደሚቅ ቆት -(ደመቀ ይደምቅ ይድምቅ ዐረ ደመከ ) መጨፍለቅ፤ መስበር ማድቀቅ ቀጥቀጥ መፍጨት፤ መምታት መግጨት -(ማቴ፳፩ -፵፬። ኢሳ፵፩ -፲፮) ደመቀቶ መልታሕቶ ውግረተ እብን ደመቁ ሥጋሁ ብን ለእብን ሶበ ይደምቆ ይወፅእ እሳት -(መሳ፭ -፳፮ ስንክ -ጥቅ፬። አፈ -ድ፲፱) በቁሙ፤ መድመቅ ማማር የልብስ የግምጃ -(ተረት) ማቅ ይሞቃል ሻሽ ይደምቃል ገቢውን ባለቤት ያውቃል

ደሚፅ ፆት -(ደምፀ ይደምፅ ይድምፅ ዕብ ሻሜጽ፤ ሰደበ አሽሟጠጠ)  መድመፅ መጮኽ ድምፅ መስጠት፤ መሰማት መደመጥ፤ ድምጣም መኾን -(መዳመጥ መርገጥ መደፍጠጥ መራመም መፈግፈግ) ደደምፅ ማዕበሉ ዘእንበለ ይድምፅ ነጐድጓድ። በቃለ አሚ ወበትፍሥሕት ደምፁ። ደምፀ ወተሰብከ ውስት ዓለም -(ኤር፭ -፳፪ ሱቱ -ዕዝ፬ -፭። መዝ ፵፩ ድጓ)

ደማሊ -(ጽር ዳማሊስ) ጥጃ እንቦሳ በጥጃ አምሳል የተሠራ ጣዖት። ባለብሉዮች ግን የእንቦሳ ምስል በማለት ፈንታ የአንበሳ ምስል ይሉታል ወኵሉ ሕዝብ እለ ክሕዱ ሦዑ በዓል ወለደማሊ -(ጦቢ፩ -)

ደማሚት -(ደማሚ ምያን ያት) በቁሙ የሚደም የሚጮኽ ድም የሚል ባሩድ ደማሚት የሴት አንቀጽ ነው፤ ስዱስ ብሎ ስድስት እንደ ማለት -(ዐማርኛ)

ደማስቆ -(ዕብ ዳሜሴቅ) ሀገር የአራም መዲና ደማስ ግምጃ የሚሠራበት የሐርና የፀምር የልብስ የፈትል አገር ምሳለ ሠቅ በዓለ ማለት ነው ማየ ደም ምሳለ ፍሕም የሚሉም አሉ -(፩ነገ -፲፩ -፳፬)

ደማሪ መደምር -(ዊት ውያን ያት) በቁሙ፤ የሚደምር የሚጨምር አዋሓጅ ቀላቃይ።

ደማዊ -የደም ደማም ደመ ነፍስ ያለው ደም የሚወጣው፤ ደሙ ያልቅና ሲደርቅ የሚሞት በባሕርና በየብስ የሚኖር ሕያው ሥግው ተላዋሽ ተንቀሳቃሽ ያሙስና ያርብ ፍጥረት ለማግሰኞም ፍጥረት ይነገራል ደመ አስካል። ደሙ በለስ። ደመ ዕጕሥታር -(ዘፍ፵፱ -፲፩ መጽ -ምስ)

ደም -(ማት ዕብ ዳም ሱር ድማ ዐረ ደም) ቁሙ፤ ቀይ ፈሳሽ ከሕያው ከሥግው የሚገኝ -(ዝፍ፱ -) ሥጋ ወደም እምነ ዘደም። ደማቲሆሙ ወደምየ በእንተ ክዒወ ደማቲሆሙ ርቱዕ ንክዐው ደማቲነ በአንተ ክርስቶስ አምሳለ ማይ -(ሢራ፲፬ -፲፰ ዮሐ፩ -፲፫ ዮሴፍ ልክ -፻፴ አፈ -ተ፭) ወገን ተደምሮ በደም። ዘተርፈ እምነ ደሞሙ ለእለ ያርብሕ -( - - -፩። ኢያ፲፫ -፲፪)

ደምኀ -(ዐረ ደመኀ ኖኀ) አደገ ላቀ፤ ረዘመ። አነሣ አቀና፤ የጠጕር የራስ

ደምሮ ሮት -(ደመረ ይዴምር ይደምር ፀመረ ዐረ ደመረ ገባ) መደመር፤ መጨመር ማግባት መግጠም ማገናኘት፤ማዋሐድ አንድ ማድረግ መቀላቀል መደባለቅ። ትዴምር ኆጻዳተ ውስተ መማሥጥ። ትደምሩ ጣነ ዘካልእ ቅታሬሁ ደምር አዕጻደ አሐተ ምስለ ካልእታ። ደመረ ሥጋነ ምስለ መለኮቱ። ይዴምሩ ደመ ምስለ ደም። ኢትደምር ንዋየከ ምስለ ዘይኄይለከ ሠላሳ ወአሐዱ ወዕሥራ ወተስዐቱ ለእመ ደመርከ ክልኤሆሙ ይከውኑ ስሳ -(ዘፀ፳፮ -፲፩ -፱። ፳፮ -፮። ድጓ ሆሴ፬ -፪። ራ፲፫ -፪። አቡሻ -፲፩)

ደምሰሰ -(ተቀ -) በቁሙ ደመሰሰ አጠፋ፤ አበላሸ ፋቀ ሠረዘ ይቅር አለ የጥፈት የሥዕል የማኅተም። ወደምሰሰ ዘጽሑፍ ውስቴታ ለይእቲ ክርታስ። አነ ዘእደመስሶን ለኀጣውኢከ ወደምሰሰ መጽሐፈ ዕዳነ። ደምሰሰ አሠርየ -(ስንክ -ኔ፲፪ ኢሳ፵፫ -፳፭ ቆላ፪ -፲፬። ኢዮ፴ -፲፫)

ደምሳሲ መደምስስ -ሚደመስስ፤ ደምሳሽ አጥፊ ግዚ ደምሳሴ አበሳየ መል መደምስስ -(ቄድር። ፩ዜና -፳፩ ፲፭)

ደምኖ ኖት -(ደመነ ይዴምን ይደምን ደምሰ ዕብ ዳሜን ዘበለ) መዳመን መጥቈር መጨለም ደመና መምሰል ደመና መልበስ፤ በጉም መታፈን መሸፈን እምከመ ቦአ ውስተ ዝኑ ለሰብእ ገረ ሕሠም ይዴምን ገጽ ፀሓየ ጽድቅ ዘኢይዴምን ጸዳል ዘኢይዴምን መጽሔት እንተ ትዴምን -(ቀሌ ቄር አፈ -ተ፱ ጥበ፯ -፳፮)

ደምዐ -(ደምዐ፤ ትግ በጨበጣ ወጋ ዕብ ዳማዕ አነባ) ቶሎ አገኘ በቶሎ ወቀ የሰውን ልብ ምስጢርና ሐሳብ ደምዐና ደምሐ አንድ ዘር ናቸው መጽሐፍ ግን በደምዐ ፈንታ አድምዐ ይላል፤ ስሕተት ነው ሲወጉና ሲያዝኑ ደምና እንባ በቶሎ እንዲገኝ ይህም እንደዚያ ነው። ኢያደምዕ ፍትወቶ ደኃሪ ያደምዑ ኀይለ ምጸጋ። እመሰ አድምዐተከ ኢታወፅአከ ጽዕልት ብእሲት ለእመ አድምዐት ብእሴ ኄረ -(ኢዮ፳ -፳። ፊልክ -፹፫። ራ፳፩ -፪። ምሳ፳፬ -፶፰)

ደምዎ ዎት -(ደመወ ይዴሙ ይደሙ) መድማት ደም መኾን ደም መልበስ መምሰል

ደሲስ ሶት -(ደሰ ደሰሰ ይደስስ ይድስስ። ዐረ ደሰ) መሰወር መደበቅ መከለል መጋረድ መዳሰስ መዳበስ በእጅ

-መንዳሰስ ድስስ ማለት፤ ማጐንበስ፤ ደሳሳ መኾን፤ የቤት የጐዦ ለፈስም ይኾናል

ደሳ -ዳውዣ ምንጣፍ የሱማሌ ሥራ፤ ጭገራም።

ደሴት -( ደስያት) ቁሙ፤ በባሕር ውስጥ ያለ ባሕር የከበበው የብስ ሀገር ምድር ራራ እንደ ደቅ እንደ ሐይቅ እንደ ዟይ ያለ እለ ይነብሩ ውስተ ዛቲ ደሴት ደሴተ ኬጥኤም አድለቅለቃ ደስያት። ደስያት ዐበይት -(ኢሳ፳ -፮። ኤር፪ - ሕዝ፳፮ -፲፭ ኩፋ -)

ደስከን -( ደሳክን ዕብ ዲሾን ሬማእ ዐረ ሪእም) የዱር የበረሓ እንስሳ፤ ቀንዳም ቀንደ ታላላቅ ባለብዙ ዐጽቅ እንደ ርኤም ያለ የዋሊያና የፌቆ ወገን፤ ባለብሉዮች ግን ጐሽ ይሉታል ቶራ ወደስከን -(ዘዳ፲፬ -)

ደስክ -ደስክ፤ ደባስ ጋኔን የሚጫን የሚጨቍን የሚደብት፤ ድራሞን ተመልከት

ደስዮ ዮት -(ደሰየ ይደሲ ይድሲ ዳሽ ዐረ ዳሰ) መዳስ መርገጥ መደፍጠጥ፤ ማበራየት፤ ኬደን እይ። ማስደሰት፤ ደስ ማሰኘት መጣድ ማስረር ደስታ ድስት ከዚህ ወጥቷል።

ደስጴዳ -(ጽር ዳሲፑስ ዳሲፖዳ) ጥንቸል የሽኮኮ ይነት -(ዘሌ፲፩ -፭። ዘዳ፲፬ -)

ደረመን -ከክ ፎከት ፈረሳቤት -(ዐማርኛ)

ደረት -(ዐማርኛ) ቁሙ እንግድዓ ደርግሐ ብሎ ደረተ ማለት ከዚህ ወጥቷል።

ደሪስ ሶት -(ደረሰ ይደርስ ይድርስ። ዕብ ዳራሽ ሱር ድራሽ ዐረ ረሰ) መድረስ በቁሙ፤ በጽሐንና ለጸቀን ተመልከት ድርዳን መድረስ እየደረሱ መጻፍ ደረሱ በእንተ ወጸሐፉ ደሪሰ ድርሳን። ዘደረሰ ሕርያቀቆስ -(ቄር። ስንክ -ታኅ፰ ቅዳ)

ደሪር ሮት -(ደረ ደረረ ይደርር ይድርር) ማረት፤ እራት ማብላት መጋበዝ መወዘም፤ ዋዜማ መቆም። የደረረ ምስጢር መደበኛው፤ ውን እንዳሞሌና እንደ ኵልኵል በሰደቃው ዙሪያ ሰድሮ ደርድሮ ማስቀመጥ ነው፤ ዶርን እይ

ደሪብ ቦት -(ደረበ ይደርብ ይድርብ። ከዐበ፤ ደበለ) መደረብ መደራረብ። ደርብ ደረባ ድርብ እንዲሉ -(ዐማርኛ)

ደሪክ ኮት -(ደረከ ይደርክ ይድርክ ዕብ ዳራኽ ሱር ድራኽ ኬደ ረገፀ) መጥናት መጠንከር፤ መድረቅ መሻከር መክፋት መጨከን ደረቅ ማለት ቅሉ ከዚህ ወጥቷል ትፀወግ እምሕምዘ ፍዖት ወትደርክ ምተኵላ -(መጽ -ምስ)

-መንደርከክ መብሰል መቅላት፤ የፍሬ የፍሕም

ደሪዞን -(ጽር ዲዎርዞን) ንድቀ የግንብ ሥራ -(ሕዝ፵፩ -፲፪) ጠቀመን እይ።

ደሪግ ጎት -(ደረገ ይደርግ ይድርግ ሱር ዳራግ) ማድረግ ማደራጀት ደረጃ መሥራት፤ በደረጃ መውጣት፤ መግጠም ማዛወግ አንድ ማድረግ። መጽሐፍ ግን በደረገ ፈንታ አድረገ ይላል፤ አያሰኝም። ኅቡረ ኢታድርግ ድሪጎ በአልጓሚሁ -(ሢራ፯ -፰። ቄር)

ደራሲ -(ሲት ስያን ያት) የሚደርስ ደራሽ፤ ባለድርሳን ተርጓሚ ስባኪ፤ ፍጹም ሊቅ ጎርጎርዮስ በዓለ መንክራት ወደራሴ ቅዳስያት ቤተ ደራስያን -(አቡሻ -፶። ስንክ -ሚያ፳፩)

ደራጎን -የየብስና የባሕር ዘንዶ እግርና ክንፍ ዦሮና ቀንድ ያለው፤ ጓጕል ከኹሉ አለኹ የሚል ምስጢሩ ድርገትና ባለድርጎነት ነው ድሩግ እንደ ማለት -(ገድ -ጊዮ)

ደርሰኔ -(ዐረ ዳርሲን ) የሽቱ ዛፍ ስም ንጨቱ ብዙ ዐይነት ያለው፤ ቅመምና መድኀኒት የሚኾን፤ ቀናንሞን እይ። ምቱረ ልሳኖ ኀበ ህላዌሁ አግብአ ሶበ ደርሰኔ ወመዓረ ቀብዐ -(ስንክ -ጥር፭)

ደርቀ -(ትግ ገፋ ገፈተረ) ደረቀ ከረረ ደረቅ ኾነ ዘሩ ደረከ ነው -(ዐማርኛ)

ደርበየ -(ተቀ ) ዕብ ዳርቤን) ወረወረ፤ ወጋ መታ ደራርቦ መላልሶ። ደርበያ ኵናቱ ውስተ አረፍት። ደርብዮ ያንው። ከመ ብእሲ ዘይደረቢ ናት ይወግዖ ለዘተፈነወ ኀቤሁ ደርብዮቱ ይደረቢ በኵያንዊሁ -(፩ነገ -፲፱ - መቃ -ገ፲፬ አፈ -ተ፳፪ ስንክ -ኅዳ፯ ሕዝ፳፮ -) አንደርቢ ማለት ከዚህ ወጥቷል ዘረበን እይ የዚህ ጎር ነው

()          ደርዐ -ተጠረረ ጥሩር ለበሰ ጨከነ፤ ታገሠ ሰማዕት ረከቡ ተስፋሆሙ ደሪዖሙ ወተዐጊሦሙ -(ድጓ)

ደርከኖ :-ኀምራዊደሪክ ደረከ

ደርዝ -(ዐማርኛ) ድርብ ስፌት እንደ መኪና ስፍ ያለ ወይም የባብ ጥርስ የጥልፍና የጥራዝ ዐይነት።

ደርጉ -( ደራግው) ወረንጦ፤ መቈንጠጫና ማጣበቂያ። ሚደርጉ፤ ወረንጦው ሹሉ ደርጉ መቈንጠጫው።

ደርግ -አንድነት፤ አንድጋ መጋጠሚያ። ሐውጹ ማኅበረነ ወባርኩነ ደርግ በደርገ አንቀጸ ዐጸድ -(ስንክ -ታኅ፲፮ ዘፀ፴፯ -፲፫)

ደርግሐ -(ተቀ ) ደረተ፤ ጠቀመ አማገ ድርና ማጊን ኣዛወገ አንድ አደረገ

ደቀ መዝሙር -(መዛሙርት) ቁሙ፤ ተማሪ ዳዊት ደጋሚ

ደቀ ጽርሕ -ዙፋን ጠባቆች፤ የልፍኝ አሽከሮች -(ኢሳ -፴፱ -)

ደቂቃ -( ደቃይቅ ዐረ ደቂቀት) በቁሙ ታናሽ የጊዜ ክፍል፤ የሰዓት ወይም የኬክሮስ ኛ፤ ከሥልሳው አንዱ ክፍል -(አቡሻ -፶፬)

ደቂቅ -(ቅት ቃት ደቃቅ ቃት) ቅጽልና ጥሬ። በቁሙ የደቀቀ ደቃቅ፤ አሸዋ እብቅ ዶቄት ውግጥ የሚበን የሚተን የሚበተን ጣን ዘቅታሬ ደቂቅ። ትገብር ደቃቀ ጼው ደቃቅ -(ዘፀ፴ -፯። ኢሳ፴ -፳፪ ስንክ -ኅዳ፩)

-ታናናሽ ጥቃቅን ቀጫጫ ቀጫጭን ክንፍ ደቃቅ አስናኒሁ ደቃቅ ወበሊኃት ከመ አስናነ ከልብ። ይሣርር ዲበ ማይ ወየሐንጽ በደቃቅ አንስሳ ዐበይት ምስለ ደቃቅ። ራዊት ደቃቅ ብትር ደቃቅ እለ ቅዐቶሙ። እለ ይፌጽሙ ?ሕጻጺ ደቂቃት ጣውእ ሕባለ ሥርው -(ሱቱ -ዕዝ፲፩ -፬። ዮሴፍ። ቅዳ መዝ -፻፫ ስንክ የካ፭ ሄርማ። ቀሌ መቃ -ገ፳)

-ልጅ ዕጓል፤ ሕፃን ደቦል አሽከር ብል ውስጠ ብዙነት ስላለው እንደ ሰብእ ላንድም ለብዙም ይኾናል። ወልድየ ዓዲሁ ደቂቅ። ደቂቅት ድንግል ደቂቅ ድኩማን አዳም ወደቂቁወርእየ ኢዮብ ደቂቆ ወደቂቀ ደቂቁ -(፩ዜና -፳፪ -፭። ፊልክ -፶፰። ዘፍ፴፫ -፲፫ አርጋ ኢዮ፵፪ -፲፮)

-ሕዝብ ቤተ ሰብ፤ ሻክርት አርድእት ደቀ መዛሙርት ምስጢሩ ታናሽነት ነው። ደቂቀ እስራኤል። ደቂቁ ለንጉሥ ደቂቀ ቤሴሎም ደቂቁ ለአቡነ ተክለ ይማኖት። ደቂቀ ቢያት ደቂቀ ጥበብ -(ዘፀ፩ -፩። አስቴ፪ -፪። ፪ነገ -፲፫ -፳፱ ገድ -ተክ ነገ - -፫። ማቴ፲፩ -፲፱)

ደቂቅ ቆት -(ደቀ ደቀቀ ይደቅቅ ይድቅቅ ዕብ ዳቃቅ) መድቀቅ መላም ዶቄት መኾን መርቀቅ መቅጠን ማነስ መኰሰስ ናሽ መኾን ደግደገን እይ፤ የዚህ ጎር ነው

ደቂቅና -ልጅነት፤ ታናሽነት። በደቂቅናሁ ኢከልኣ ደቂቅናሃ -(ፊልክ -፴፭። ፶፬)

ደቃውቅ -(ቃት) ልጆች፤ ታናናሾች ዕቀብ ንስቲያሆሙ ወትማሕፀን ቃውቂሆሙ ደቃውቃት -(ቅዳ -ያዕ ኪዳ)

ደቅ -(ዝኒ ከማሁ) ልጆች አሽከሮች ወሸከሮች አንስት ወደቅ ምጽኡ ሎቱ  ደቀ ወረከበ ደቀ ንኡሳነ -(ማቴ፲፬ -፳፩ ፲፱ -፲፫ ፬ነገ - -፳፫)

-ኀያላን ጐበዛዝት ወጣቶች ወጸውዐ ዊት ሐደ ምውስተ ደቁ ወይቤሎ ሑር ቅትሎ ይትነሥኡ ደቅነ ደቀ ብንያም ወደቀ ዳዊት -(፪ነገ - -፲፭ -፲፬ -፲፭)

- ሀገር በጣና ስጥ ያለ ታላቅ ደሴት ስመ ልሕኵት የደቅ ዎች የሚሠሩት ጥሩ ሸክላ -(ግጥም ያጤ ገረድ ብልላ ደቅ ስትገባ ያያት አዝማሪ ላጤ ሲያወራ) እጇን ተሰብራ በሙሉ ኂሩት ደቃለች አሉ

ደቅሐ -ደቅሐ፤ -(ቀድሐ) በቁሙ፤ ደቃ ደሰቀ መታ ቸነከረ በሳ ደለ ሰረሰረ ደሰ ባረከ መረቀ ቀደሰ በመድቅሑ ደቅሖሙ ወበኀይለ መዝራዕቱ አጽንዖሙ -(ኢሳ፵፬ -፲፪)

ደቅሶ ሶት -(ደቀሰ ይዴቅስ ይደቅስ ዐረ ዱከስ) ማንቀላፋት፤ በእንቅልፍ መያዝ መድቀስቀስ፤ እንደ ሬሳ መኾን። ደቀሰ ወኖመ ደቀሱ ኖሎትኪ። ወኢይዴቅስ ዘየዐቅበከ -(ግብ፳ -፱። ናሖ፪ -፲፰ መዝ -፻፳)

-መተኛት መጋደም፤ መጣመር ደቀሱ ውስተ ምድር ዘይዴቅስ ምስለ ብእሲቱ ወላዕሌሃ ትክቶ -(አዋል -ሲኖዶ) መደቈስ መደቋቈስ፤ ገቢር ወይም ዐጕ ተገብሮ -(ጥደ) መደቈስ፤ ተደቋሽ መኾን

ደቅደቀ -(ተቀ ) በቁሙ፤ ደቀደቀ -(ዐማርኛ)

ደበራ -የብልግና ሥራ ዝሙት ሴሰን ቅንዝር ምንዝር

ደበርቢር -(ዐረ ዱብር ዘባን ድኅር) ታናሽ ድንኳን አጐበር ማረፊያ መጠጊያ ወይም እንደ ወንበርና እንዳትሮንስ ያለ፤ ሲጠጉት ርባ የሚጐንጥ፤ የሚጐረብጥ፤ መነኮሳት በርሱ ዐርፈው ርሱን ተደግፈው እንቅልፋቸውን የሚያሳልፉበት ይኑሙ እንዘ ኢይሰክቡ አላ ከመ እንተ አትራኖስ ዘንድቅ ይግበሩ ደበርቢረ ወቦቱ ይንጽፉ አልባሲሆሙ ወይስክቡ ንቡረ -(ሥር -ጳኵ)

ደቡብ -የማእዝ ም፤ ዐቢ ማእዝን የሰሜን ትይዩና አንጻር ፊት ለፊት በሊባና በአዜብ መካክል ያለ የምዕራብ ቀኝ የምሥራቅ ግራ ሜንን ተመልከት ኵሉ ገጽ እምደቡብ እስከ ሜን -(ሕዝ፳ -፵፰) ደቡብ የምሥራቅ ግራ እንደ ኾነ ሰሜንም የምዕራብ ግራ ነውና በዚህ ምክንያት ተሳስቶ በደቡብ ፈንታ ሜን በሰሜን ፈንታ ደቡብ እያለ በብዙ ቦታ ተጥፎ ይገኛል -(ኢሳ፲፬ -፲፫ -፴፩። ፵፩ -፳፭ ፵፱ -፲፪)

ደቢል ሎት -(ደበለ ይደብል ይድብል) መደበል ማዳበል  መሸረብ መደረብ የሐብል የፊደል። መሰካት ማሳካት በፈትል ወይም ርስ በርሱ የድባ የበለስ የዋንጫ

- መሰብሰብ ማከማቸት፤ የሸንጎ። መጽሐፍ ግን በደበለና በተደብለ ፈንታ አመድበለ መድበለ ይላል፤ የተሳሳተ ነው። ሰላም ሰላም እንድራኒቆስ እብሎ ውሒዘ መንፈስ ዘሰትየ ምስለ ሐዋርያት በአመድብሎ። በቍስጥንጥን መድበሉ -(ስንክ -ግን፳፪። ጥር፲፭)

ደቢር ሮት -(ደበረ ይደብር ይድብር) መደበር መገደም፤ ደብር ገዳም መሥራት ማዘጋጀት፤ ለንግድ ዕቃም ሳይቀር ለታሪክ ለመጽሐፍ ይኾናል

ደቢቅ ቆት -(ደበቀ ይደብቅ ይድብቅ ዕብ ዳባቅ ለጠቀ ተጠጋ) መደበቅ መደባበቅ፤ መሸጐጥ ማስጠጋት -(ዐማርኛ)

ደቢብ ቦት -(ደበቀ ይደብቅ ይድብቅ ዕብ ዳባቅ ለጠቀ ተጠጋ) መደበቅ መደባበቅ፤ መሸጐጥ ማስጠጋት -(ዐማርኛ)

ደቢው -(ደበወ፤ ይደቡ ይድቡ ደበየ ዴፐ) ማድባት መሸመቅ፤ ቀስ ዝግ ማለት መደበት መጫን መጨቈን መደቋቈስ ያውሬ የጠላት የንቅልፍ።

ደባሪ መደብር -ሠራዒ መጋቢ፤ ባለቤት። ዮሐንስ መደብር ዘውእቱ ሠራዒ ብሂል

ደባዪ -(ዪት ይያን  ያት፤ በይት) ወራሪ ዘራፊ ቀማኛ ደባዬ አባግዕ -(አዋል)

ደብረወ -(ተቀ ) ዳበረ አደገ ላቀ፤ ባለቀ ለዘር በቃ ባለ ማገጠ

ደብራን -(ዐረ እደበራን። ክሲል) ጉቡኣን ከዋክብት ባንድነት የተደበሩ በጐሽ ስም የሚጠሩ፤ ፈላስፎች ጐሽ የሚሏቸው እነኀምስቶ ወይም ካምስቱ አንዱ ታላቁ በጣም የሚያበራው። ባለብሉዮች ዳተኛ ይሉታል። ወአስተጋብኦሙ ለደብራን ርኢከኑ ፍኖቶ ለደብራን ወሙፃኦ -(ኢዮ፱ -፱። ፴፰ -፴፩)

ደብር -( አድባር፤ ራት) ተራራ ጋራ ገመገም፤ የምድር ዕንብርት ጕብር ታላቅ ረዥም፤ ወግር የሚበልጥ። ደብረ ሲና ደብረ ዘይት ደብረ ታቦር አድባረ እስራኤል -(ሕዝ፮ -)

የተራራ ተራራ፤ ተራራ ኹሉ የሚበልጥ በረዶ የሚፈላበት ሰው የማይደርስበት፤ እንደ ዳሸን እንደ ሄርሞን ያለ የሰማይ ጎረ ቤት። አድባረ አራራት ድባር ዋኃት ዘመትሕተ ሰማይ -(ኩፋ -፰። ዘፍ፯ -፲፱ -)

-ወሰን ደንበር፤ መዲና ከተማ ታላቅ አገር። ወኮነ ድባሪሆሙ ለከነዓን ምነ ሲዶን እስከ ጌራራ። ደብረ አህጉር ዲበ አድባሪከ ድባረ ግብጽ -(ዘፍ፲ -፲፬። ኢያ፲፬ -፲፭። ዘፀ፲ -፲፬ ኢሳ፩ -፳፮)

-ገዳም ቤተ ክሲያን ታላቁም ታናሹም ደብረ ባኖስ ደብረ ዐስቦ ድባራት ወገዳማት። መቃርስ ዘደብረ አስቄጥስ መዳልወ አልባብ ተሰምየት እስከ ዮም ደብሩ -(ገድ -ተክ ስንክ -መጋ፳፯) ደብር ማለት በተራራ ላይ የሚሠራ፤ተራራ የሚያኽል ታላቅ ማለት ነው፤ የምኵራብን ፍች ተመልከት -(ሙሾ ስለ ድምፀ መልካም ደብተራ) ካህን ሞተ ብሎ አይነግሩም ዐዋጅ እንዲያው በየደብሩ መላክ ነበረ እንጅ።

ደብተረ -ደበተረ፤ ዘረጋ ነጠለ ወጠረ ገተረ፤ በደብተረ ፈንታ አደብተረ ይላል -(ገድ -አዳ)

ደብተራ -(ጽር ዲፍቴራ) የምሧ የሠረገላ ተድባብ፤ የመንበረ ታቦት አጐበር፤ በስተላይ እንደ ድባብ እንደ ጃን ጥላ እንደ ባጥና እንደ ጣራ ኹኖ የሚሠራ ድንኳን መላጃን በዲፍቴራ አምሳል የተሠራ፤ እንደ ብራና የሚወጠርና የሚገተር፤ ቤተ መቅደስ ጸሓፊ ባለደብተር ባለብራና። -(ተረት) አይጥፍ ደብተራ፤ ክንፍ የለው አሞራ ተክለ ብራም ደብተራሁ

መትሕተ ደብተራ ሠቅ በውስተ ደብተራሁ ቅዱስ ከመ ትትሐነጽ ደብተራሁ -(ኩፋ -፲፫ ዜና -፲፯ -፩። ራ፳፬ - ጦቢ፲፫ -)

ደብተራት ደባትር -ደብተሮች መዝገቦች የሚጣፍባቸው ወይም የሚጥፉ ጣፎች ባለደብተሮች። ድንኳኖች አጐበሮች። ኅተ ደባትሪሆሙ ደባትር ዘነደ እሳት ደብተራት -(ዘፀ፴፫ - ቅዳ -ሕር መቃ -ገ፩)

ደብተራዊ -ድንኳን ተካይ የድንኳን አገልጋይ፤ ባለድንኳን ሌዋዊ -(አፈ ተ፲፮) መዘምርን ደብተራ ማለት ከሌዋውያን ስም የመጣ ነው

ደብተር -(ዕብ ዲፍታር ዐረ ደፍተር) በቁሙ መጣፊያ መክተቢያ፤ የብራና የወረቀት መዝገብ፤ ነጋዶች ጠርዘው አፍፈው መጣፍ አስመስለው ለየጸሓፊው የሚሼጡት የገንዘብ ጥር ወፅአ ዘገባ የሚጣፍበት። ደብተር ማለት ቃሉ የፋርስ ቋንቋ ነው ይባላል

ደብይ ዮት -(ደበየ ይደቢ ይድቢ ደበወ) ማደባየት፤ ካፈር ድቤ ላይ መጣል ማንባለል ደባ መሥራት ሳይታሰቡ ወደ ሰው ቤት መግባት ጥልቅ ዠቅ ማለት መውረር መዝረፍ መቀማት መመንተፍ ደበዩኒ እለ ልቦሙ ምሕረት። ሮዱኒ ወደበዩኒ ይደ አብያተ ሰብእ  ከመ ኢይድብያ ለቤተ ርስቲያን -(ኢዮ፴ -፳፩ መዝ -፴፯። ግብ፰ -፫። መጽ -ምስ)

ደብደበ -(ደበ ዐረ -ዘበ ዘብዘበ) ፈራ ዐሰበ ተጨነቀ የሚመጣበትን ስላወቀ የሐዝን ወይደበድብ -(ፊልክ -፻፷፭ ቀሌ)

-ፈዘዘ ተነፋ ዱባ መሰለ የሆድ የሰውነት አብዝቶ መብላት የተነሣ። ወሶበ ይነቅህ ኢይደበድብ ነፍስቱ -(ሢራ፴፬ -)

-በቁሙ ደበደበ መላልሶ መታ ቀጠቀጠ፤ ደብዳቢ እንዲሉ። አረገዝ ድብድብ ኾነ፤ የሰብል ምስጢሩ ማበጥ መንዘርጠጥ ነውና ተነፋ ካለው ይገባል

ደነሳዊ -(ዊት ውያን ያት) ዘማዊ ሰኛ፤ ያመንዝሮች ሲሳ ትወደዩ ውስተ ኵነኔ ደነሳውያን በርኵሰ ዝሙት -( - -፳፬ -)

ደነስ -(ሳት) እድፍ አደፍ ትክቶ፤ ሙት ኀጢአት የዝሙት ሥራ ምኞት ዐስበ ዝሙት። መዋዕለ ደነስ በፍትወተ ደነስ ዘተፀነስኪ ንጽሐነ ምኵሉ ደነስ ወእምኵሉ ርኵስ ያነጽሕ ልቦ እምደነሳት -(አዋል። ቅዳ ፊልክ -፻፷፩) ሀበኒ ደነስየ ደነ ዘማ ደነሰ ዝሙት፤ዋጋ -(ኩፋ -፵፩። ዘዳ፳፫ -፲፱ ሚክ፩ -)

ደነክ -ዝልዝል ትልትል ቋንጣ ያልጋ ጠፍር

ደነፈ -(ትግ ደንፈ) ወውዐ ደነፋ ፈከረ፤ ተንደቀደቀ -(ዐማርኛ)

ደኒቅ ቆት -(ደነቀ ይደንቅ ይድንቅ ደደቀ) መድነቅ መደነቅ ድንቅ መኾን መደንገት ደደቀና ወገበን እይ

ደኒን ኖት -(ደነ ደነነ ይደንን ይድንን። ዐረ ደኒነ) መድነን መጐንበስ ራስን መቀለስ ዐንገትን መድፋት መስበር፤ ማቀርቀር ድንን ወእፍታሕ ደነነ ሥዕል ኦሆ ዘይብል ትደንኑ ወትሰግዱ ሎቱ ድንኒ ወንትዐዶኪ -(ማር፩ -፯። ድጓ ኢሳ፵፮ -፯። ፶፩ -፳፫)

-መጕበጥ መታጠፍ በጭራሽ እንደ ደጋን መኾን፤ የደዌ የርግና። ኮነ ነዊኀ በቆሙ አላ ውእቱ ይደንን በእንተ ርሥእናሁ -(ስንክ -ግን፲፫)

ደኒክ ኮት -(ደነከ ይደንክ ይድንክ) መዘልዘል መተልተል የሥጋ የቈርበት።

ደኒዝ ዞት -(ደንዘ ደነዘ ይደንዝ ይድንዝ። ፀሪስ ፀርሰ) መደነዝ መጥረስ፤ ደነዝ መኾን፤ የስለት። ደንገዘንና ደንጐዘን እይ የዚህ ስሯጽ ነው። ደንዘ ያማርኛ ፀርሰ የግእዝ

ደኒጽ ጾት -(ደነጸ ይደንጽ ይድንጽ) አጥብቆ መያዝ መጨበጥ መቀየም፤ የጠላት የገንዘብ።

ደናግል -ድንግሎች ደናግሎች የወንድ የሴት ጐበዛዝት ነዣዥት ያልተዳሰሱ ደናግል ወመነኮሳት በእንተ ደናግል ዕደው ደናግል ንጹሓን ወንዶች -(ቅዳ ስንክ -ጥቅ፲፮። አርጋ -) ደናግል አለፍቀራከ ዋልድ ደናግል ወራዙትኒ ወደናግል ዐሥሮን ደናግል -(ማሕ፩ -፫። መሳ፳፩ -፲፪ መዝ -፻፵፰ ማቴ፳፭ -)

ደን -() ደን -(ዐማርኛ) በቁሙ ዱር ጫካ ብዙ ዛፋም የዛፍ ቦታ ደን ጠባቂ የደን ሹም እንዲሉ፤ ሊባኖስን እይ።

ደንሶ ሶት -(ደነሰ ይዴንስ ይደንስ ዐረ ደኒሰ) ማደፍ መርከስ ማሳደፍ ማርከስ ማባበል መለመን፤ ዐስበ ዝሙት መስጠት እስመ ደነሱኪ ወኢደነሱኪ -(ሕዝ -፲፮ -፴፬) ደንሰ ፈንታ ተደነሰ ይላል፤ አያስኝም። ይረኵሱ ባቲ ወይዴነሱ እመ ዘአበሰ ወተደነሰ በዛቲ ኀጢአት። እመሂ በቃል አበሱ ወእመሂ በገቢር ረኵሱ ወእመሂ በክሡት ተደነሱ -(አፈ -ድ፴፩ - - -፪። ግንዘ)

ደንቀወ -(ተቀ ) ደነቈረ፤ ተደፈነ ልሰማ አለ የዦሮ ዘአሜሃ ትውልድ ደንቀዋ እዝዚሆሙ ከመ ኢይስምዕዎ -(ቅዳ -ግሩ) ደነቀረ በግድ አገባ፤ ቀረቀረ -(ዐማርኛ)

ደንቃዊ ድንቅው -(356) የደነቈረ ደንቈሮ የማይሰማ ወይም መካከለኛ ጥቂት ጥቂት የሚሰማ ነፍሳት ደንቃውያት ድንቅው፤ ድንቅዋነ ዝን -(ቄር - መጽ -ምስ)

ደንበር -(ትግ ክንፍ ላባ ንጮ) በቁሙ፤ ወሰን ዳርቻ ጽንፍ -(ዐማርኛ) ደነበረ ተደናበረ ደንባራ ማለት ከዚህ ወጥቷል

ደንዘዘ -(ተቀ ) በቁሙ፤ ፈዘዘ ዳተኛ ቸልተኛ ኾነ

ደንደስ -(ዐማርኛ) በቁሙ፤ ጫንቃ ትከሻ፤ ደንደሳም እንዲሉ።

ደንደር -(ዕብ ዳርዳር) እሾኻም ቅጠል የሱፍና የኰሸሽላ ዐይነት፤ ኹለንተናው እሾኽ ስለ ኾነ ሊያዝ ሲጨበጥ ማይቻል በቁሙ ደንደሮ እሾኽ ጋሬጣ፤ ወይም በደንደር አምሳል የሚሠራ የስልክና የብረት እሾኽ፤ የዱሮ ሰዎች እግረኛ ፈረሰኛ ጠላት በሚመጣበት መንገድ ወጥመድ አድርገው የሚቀብሩት የሚሰውሩት፤ አውሬ የሚያጠምዱበት። ይቤ እንጦንዮስ አን ርኢኩ መሣግረ ሰይጣን ትክልተ ዲበ ምድር .... በከመ ተጽሕፈ እስመ ኀብኡ በውስተ ፍኖተ ምሕዋርየ መሣግረ ወአሕባለ ወሶበ ርእየ ንከረ ምብዝኀ ሥዋክ ወደንደር እንተ ጽርት ውስቴታ፤ ወአራዊት እንተ ትወድቅ -(ፊልክ -፻፲፮)

 

ደንደነ -(ተቀ ) በቁሙ፤ ወፈረ ገዘፈ ዛፉ ለሰውም ይኾናል። ደንዳና ዚህ ወጥቷል

ደንዳና -(ዕብ ዳንዳና) የቅጠል ስም ንድ ዐይነት ቅጠል ጥሩ ሽታ ያለው መድኀኒት የሚኾን በቁሙ ወፍራም ግዙፍ -(ዐማርኛ) ደኒን ደነ ደንደነ።

ደንገለ -(ዐረ ደገለ ሸሸገ ደበቀ) ደነገለ አጥብቆ ጠበቀ ከለከለ ከሴት አራቀ ራሱን ወይም ሌላውን። የደንጐላ ምስጢር አብቦ አለማፍራት ነውና ደንገለም የደንጐላ ዘር ስለ ኾነ ይህን ያሳያል እምአይቴ ረከብከ ዘከመ ብሥራተ፤ እንበለ ዘርዕ እምድር እትወተ ወእንበለ ምት እም ድንግል ፅንሰተ -(ድጓ)

ደንገዘ -(ደነዘ፤ ደንዘዘ) አረጀ ደከመ መሸ ጨለመ -(ዐማርኛ)

ደንገገ -(ደገገ፤ ደግደገ) ደነገገ ወሰነ ዐገገ ገደበ ወደበ የሕግ የፈለግ

ደንገፀ -(ደጐጸ ደነጸደነገጠ ፈራ ተንቀጠቀጠ ምስጢሩ ልብን በፍርሀት መድጐጽ መነካት ነው፤ ከማየት መስማት የተነሣ ኵሉ ነፍስ ይደነግፅ ደንገፀኒ ነፍስየ ይደነግፅ ልብኪ ደንገፁ በበይነ ዘኮነ -(ኢሳ፲፫ -፯። ፳፩ -፬። -፭። ዮዲ፲፭ -)

-ጮኸ አስተጋባ፤ ተሠነጠቀ፤ የምድር የተራራ። ደንገፀት ምድር እምቃሎሙ። ወይደነግፁ ድባር ዋኃት -(፫ነገ - -፵። ነገ - -፭። ሔኖ፩ -)

ደንጐላ -(ላት። ዕብ ሐባጼሌት) የዱር የበረሓ ሽንኵርት በቈላ በደጋ የሚበቅል የዥብ ሽንኵርት ዐይነት መልካም አበባ የሚሰጥ አበባው መረዋ ቃጭል የሚመስል ጥሩ ሽታ ያለው ጽጌ ደንጐላት ዘውስተ ቈላት። ወከመ ጽጌ ደንጐላት በማእከለ ሥዋክ -(ማሕ፪ - -) ባለብሉዮች ግን ማእከለ አሥዋክን ሲያዩ ሱፍ ይሉታል፤ ፍችው አይዶለም

ደንጐዘ -ሠራ ቈነነ፤ ጐቸ ጐነጐነ ፈለ ፈተለ ቈነጣጠረ

ደንጸወ -(ተቀ ) ነፈገ ቤስ፤ ሣሣ ጠበ ጨባጭ ኾነ ቀና ተመቀኘ። ኢትደንጹ ዐይንከ ሶበ ትገብር ምጽዋተ ጋዊ ዘእንበለ ደንጽዎ ይደነጹ ባቲ ላዕለ ነዳያን። ይደነጹ በውስተ ማእድ ትደነጹ ዐይኑ በእኁሁ -(ጦቢ፬ -፯። ቅዳ -ኤጲ - - ራ፲፬ - ዘዳ፳፰ -፶፬ -፶፮)

ደንጻዊ ድንጽው -ንፉግ ጨባ ሥሥታም -(ሢራ፲፰ -፲፰ ፳፭ -) ለደንጻዊ ደረግምዎ በእከየ ግዕዙ ኢትትማከር ምስለ ደንጻዊ እንበይነ ውሂበ ምጽዋት -(፴፬ -፳፫ ፴፯ -፲፩) ድንቅው በማለት ፈንታ ድንጽው ይላል ስሕተት ነው ኢትኩኑ ድንጽዋነ ወድንዙዛነ ልብ ለአሚን -(መቃ -፲፰)

ደንጽ -ቂም በቀል ትግል ክርክር ፍጅት። ምንት ውእቱ ደንጽ። በደንጽ ሀለዉ አሐዱ ለአሐዱ ይትቃተሉ ደንጽ ዘበኅዳጥ -(ዕር -ኢሳ፯ -፲፩ -፳፬)

ደዐት -ማወቅ መታወቅ፤ ዕውቀት አነጋገር ንግግር

ደኵስበተሪ -(ጽር -ዶክሳ -ፓቴሪ) ስብሐት ለአብ ማለት ነው። ኦርቶዶክስን እይ ወትብል ደኵስበተሪ አርባዕተ ጊዜ -(ግንዘ)

ደኵዐ -(ይደኵዕ ይድኳዕ ደኩዕ) ወደቀ ተጣለ ተረሳ

ደኪም ሞት -(ደክመ ይደክም ይድክም) መድከም መታከት መዛል መስነፍ መላም መለስለስ፤ ማነስ መኰሰስ እገሪከ ይረውጻ ወይደክማከ ወደኪሞ ሐዊረ ፍኖት ነበረ ደክመት ነፍስየ -(ኤር፲፪ -፭። ዮሐ፬ -፮። ሱቱ -ዕዝ፲፪ -)

-መፍዘዝ፤ መስለል የዐይን የቃል ማርጀት መታመም  ምስጢሩ ያው ድካም ነው ደክማ ዕይንትየ በአንብዕ። ቃለ ወለተ ጽዮን ደክመ ደክመት እምኀይላ ደክመ አቡከ ዘእንበለ ትድክም -( -፲፩። ኤር፬ -፴፩። ኩፋ -፴፭ ፍ፵፰ -፩። ሢራ፲፰ -፳፩) ደክተመን እይ የዚህ ስሯጽ ነው።

ደክተመ -(ደክመ -ስሯጽ። ዕብ -ያቴም) ደኸየ፤ የሙት ልጅ ኾነ። አባት እናት ድኻ ማለት ቅሉ ከዚህ ወጥቷል ዕብራይስጥም ድኻ ሲል ዳኽ ይላል ደክተመት ቤተ ርስቲያን ለእለ ተርፉ ድኅሬሁ ርድኦሙ ወለእለሂ ደክተሙ ሕፅኖሙ -(አቡሻ -፶። ግንዘ)

ደክታም -( ደካትም) ድኻ አደግ ድኻ የሙት ልጅ እፎ ኢይፈደፍድ ሐዘንየ ንዘ እኔጽር አንስቲያሆሙ ከዊኖን ደክታመ ወውሉዶሙ ዕጓለ ማውታ ደክታም ነፍስየ ምእማ ወአባ ንዋየ ደካትም -(ዮሴፍ። ስንክ -ታኅ፳፬ - -፴፫ -)

ደወል [1]-( አድዋል) ዙሪያ ዳርቻ ወሰን ደንበር ቀበሌ አውራጃ። ኢታፍልስ ወለ ገራህት ዘአንበሩ አበው። ኵሉ ደወሉ ዘዐውዱ። ደወለ ጢሮስ ደወለ ርስ ተጋብኡ ምአድዋለ ብሔሮሙ -(ምሳ፳፫ - ሕዝ፵፭ -፩። ዘካ፱ -፪። ኢሳ፯ -፲፰ ነሐ፲፪ -፳፰)

[2]-ደወል -(ላት) ቁሙ መጥቅ መረዋ ቃጭል የደንጊያ የንጨት የብረት፤ ሲደወል በዙሪያው ባውራጃው የሚሰማ። ከመ ድምፀ ብርት ዘይነቁ ባለው ደወል እንዲል -(፩ቆሮ -፲፫ -)

ደዊል ሎት -ደዊል፤ ሎት፤ -(ዶለ ደወለ፤ ይደውል ይዱል። ዕብ ዳዌል አኮበ ደወረ ጠመጠመ የፈትል) መወሰን መከለል የቦታ መደወል፤ ማቃጨል። መዶል ማግባት፤ መክተት ዱላ ዳውላ ዶልዷላ ዱለት ማለት የዚህ ዘር ነው

ደዊር ሮት -(ዶረ ይደውር ይዱር ዕብ ዳር) መማገድ መረብረብ፤ ማንደድ መቈስቈስ እሳት መለኰስ።

ደዋ -(ትግ ወዐረ) መድኀኒት የሚያም የሚገድል ደዌ የሚኾን፤ ወይም የሚያድን

ደዌ -(ያት) በቁሙ በሽታ ሕማም የቈየ የዘገየ ብሮ የሚኖር ወይም ዐልፎ ኻያጅ ኀጢአት ፍትወት ደዌ ነፍስ። ደዌ መሪር ወእኩይ ደዌ ከርሥ ለእ አሐዩ ምዛቲ ደዌ ሐይወ እምደዌሁ ደዌ ሲሕ። ነበረት ይእቲ ደዌ ውስተ ልብ -(፪ዜና - -፲፭ ነገ - -፪። ኢሳ፴፰ -፱። ራ፴ -፲፯ ሱቱ -ዕዝ፩ -፳፪)

ደውርሀ -(ይደወርህ ይደውርህ ደውርሆ አው ዶርሀወ ይዶርሁ ዶርህዎ ተቀ -) ተባዛ፤ ረባ ተንሻሻ።

ደውይ ዮት -(ደወየ ይደዊ ይድወይ ዐረ ደዊየ ዕብ ዳዋህ ሱር ድዊይ) መደወይ መታመም መበሸት ድውይ መኾን ጤና ማጣት፤ በደዌ ዳኛ ባልጋ ቍራኛ መያዝ። እመሂ ደወየ ኢይሴፎ ሐዪወ። ደወዩ ከመ ባግዕ። ደወየ ልብነ ደወይኩ ወሐወጽክሙኒ -(ኢዮ፳፬ -፳፫ ዘካ፲ -፪። ሰቈ፭ -፲፯ ማቴ፳፭ -፴፯)

ደያኒ መደይን -የሚዳኝ ዳኛ ፈራጅ ቀጭ ደያኔ ጽድቅ -(ፊልክ -፻፷፬)

ደይቦ ቦት -(ደየበ ይዴይብ ይደይብ ትግሬ) ማረግ ወደ ላይ መውጣት ከፍ ማለት፤ በላይ መኾን። መመደብ፤ መደብ ዕር መሥራት። ዐርገንና ለዐለን እይ የዚህ አግዋር ናቸው

ደይን -(ናት) ቍርጥ ፍርድ፤ የማይላጥ የማይለወጥ፤ የማይመለስ ቃል፤ ንዑ ኀቤየ ሑሩ እምኔየ ይህን የመሰለ ኢትግበር ዘንተ ደይነ ትንሣኤ ዘለደይን ዕለተ ደይን -(ዘፍ፲፰ -፳፭ ዮሐ፭ -፳፱ ማቴ፲ -፲፭)

-ፍጹም ቅጣት መከራ ሥቃይ፤ የሥቃይ ቦታ መካነ ደይን ጢሰ ደይኖሙ ዐዘቅተ ይን ይጼዐሩ ውስተ ደይን አንቀጸ ደይን -(ኩፋ -፯። ራእ፲፬ -፲፩። -ዕዝ፮ - -፱። አርጋ -) ዲን ድኝ ማለት ደይን ከማለት ወጥቷል ክብሪትን እይ

ደይኖ ኖት -(ደየነ ይዴይን ይደይን ዳነየ ዕብ ወሱር ዳን ዐረ ዳነ) መዳኘት፤ መፍረድ መቅጣት መገሠጽ መቈጣት ወይዴይኖሙ በዐቢይ -(ሱቱ -ዕዝ፲፫ -፵፩)

ደደክ -(ደገ ደግደገ) ደጋ ጮቄ፤ ጉማም ብርዳም ውርጫም ነፋሳም ወምድረ ሴምሰ ኢመርቄ ወኢደደክ  ይባርክዎ ደክ ወመርቄ ገነት ዘኢያየብሳ ነፋሰ መርቄ ወደደክ -(ኩፋ - ዳን፫ -፵፰። ስንክ -ጥቅ፳፩)

-ቀቅ፤ ሪር ነፋስ፤ በደጋ የሚወርድ የብርድ ዐይነት ኹሉ አስሐትያ ወቍር ወሐመዳ ወደደክ። ዘየዐርግ ምኔሁ ከመ ጢስ ውአቱ ወስሙ ደደክ -(ሔኖ፸፮ -፲፪ -፲፰)

ደዲቅ ቆት -(ደደቀ ይደድቅ ይደድቅ። ወድቀ ወገበ) መደንገት፤ ድንገት መኾን መደረግ፤ የሥራ። ሳይታሰቡ መድረስ መምጣት ከተፍ ማለት፤ በድንገት ማግኘት መገኘት ግጭት መግጠም። ደደቀ በውእቱ አዝማን ባእስ ማእከለ ይሁድ ወማእከለ ርማንያ ደደቀ ብጽሐተ ነግድ። ካህን ዘደደቆ በንዋም ዝንየት ጽኑ ልብ ኢይደድቅ ሠናየ ወደደቆ ለአብ መምህረ -(ዮሴፍ። ፊልክ -፸፬። ቄድር ምሳ፲፯ ተረ -)

-መደደቅ መውጋት፤ መደንጐር፤ መፈንቀል መገልበጥ፤ መቈፈር መመንቀር -(ዐማርኛ) አንዳንድ መጽሐፍ ግን በደደቀ ፈንታ ተዳደቀ ይላል አያሰኝም። እንተ ኢኀለይኩ ተዳደቀተእኒ በከመ ይዳደቆ ለአብድ ከማሁ ሊተኒ ይዳደቀኒ። ለአብዳን ይዳደቆሙ ሞት አል ዘይዳደቃ። ወተዳደቆ አሐዱ ካህን ከመ ይዳደቅዋ ለሀገር -(ኢዮ፫ -፳፭ መክ፪ -፲፭ ምሳ፳፬ -፰። ጥበ፯ -፳፭ ሉቃ፲ -፴፩። ዮሴፍ)

ደጊም ሞት -(ደገመ ይደግም ይድግም) መድገም መደጋገም፤ ቀድሞ የሠሩትን ፪ኛ መሥራት። ገሥጾ ለዐርክከ ዮጊ ገብረ ወእመኒ ገብረ ከመ ይድግም ለእ ዘአበስከ ትድግም ደገሙ ዓዲ ወአበሱ ይደግሙ በሳ -(ሢራ፲፱ -፲፫።፳፩ -፩። መዝ -፸፯። ሔኖ፭ -)

-ማንበብ፤ ማነብነብ መጸለይ መድገም፤ መናገር መለፍለፍነሥአ መጻሕፍተ በዊሁ ወደገሞን። ወትደግም ምእተ ወኀምሳ መዝሙረ ዳዊት ይደግሙ ነገረ በዲበ ነገርየ -(ኩፉ -፲፪። ግንዘ። ኢዮ፳፱ -፳፪)

-(ትግሬ) ዳጕሳ የድግስ እኸል የጤፍ ዐይነት፤ ዐረቂና ጠላ እንጀራ የሚኾን።

ሮት -(ደጐረ ይደጕር ይድጕር ዕብ ዳጋር) ማሞቅ መታቀፍ፤ ማመስ መቀፍቀፍ የንቍላል። መዘርጋት ማርገብገብ፤ የክንፍ፤ ለመብረር። ኹሉም የወፍ ሥራ ነው። መለካት ከልክ ማግባት፤ መስፈር መመዘን ማስተካከል

ደጕር ድጕር (ዐረ ደጅር) ድግር የሞፈር ክንፍ በግራና በቀኝ የሚቀጠል ረረን እይ በአንጻረ ድጕር ዕርፈ ወበአንጻረ ዕርፍ ድጕረ። አርዑተ ብዕራ ወጸሪበ ድጕር (ኩፉ ፲፩ አዋል) ደንጐራ አዳጕራ ማለት ዚህ ወጥቷል

ዓሌ ደጓዕሌ -(ዕብ ዴቄል ሱር ዴቅላ። ዐረ ደቀል) የሰሌን ዐይነት ዛፍ ተምር፤ ግንዱ ቁመቱ የበቀልት ቅጠሉ ሌላ ዐይነት እንደ ውስጥ እጅና እንደ ጣት ያለ፤ ዲቃላ ማለት ከዚህ ወጥቷል

-ሌን የሰሌን ቅጠል ዘንባባውና ዝንጣፊው ፀመርቱ ሙሽራው የተሠራ ወይም ያልተሠራ ወአንበረ በውሳጢታ ታቦት አንጦሊዖ ደጕዓሌ ነጸፈ ውስተ ግብ ቈጽለ ደጕዓሌ ሥአ ኅዳጠ ደጓዕሌ ወሠጠቆ ወበዕለት ካልእ አርሐቦ ፅፍረት ዘደጓዕሌ ፀፊረ ደጓዕሌ -(ገድ -ተክ ገድ -ዮሐ። ፊልክ -፵፰። ፻፫ ስንክ -ኅዳ፲፮)

ደጊግ ጎት -(ደገ ይደግግ ይድግግ ዕብ ዳጋህ በዛ ረባ) መደገግ መኵራት፤ ማደግ መመንደግ፤ ደግ ደገኛ፤ ታላቅ ምጡቅ መኾን ደጋ -(ማድጋ) ደደክ ማለት ከዚህ ወጥቷል አዳጋ ቍሊልታ ተራራ ኰረብታ ከፍ ያለ ቦታ ማለት ነው፤ ልናውን መደብ አድርጎ ደግነቱን ጤናማነቱን ያሳያል ደንገገን ተመልከት የዚህ ስሯጽ ነው። በጋልኛም ዝኆንን ደጋጋ ማለት ከዚህ የወጣ ነው ነጌን እይ

ጾት -(ደጐጸ ይደጕጽ ይድጕጽ። ዕብ ዳጋሽ፤ አጠበቀ የማጥበቅ ምልክት አደረገ፤ የፊደል) መውጋት መጠቈም ጠቅ ማድረግ መጓጐጥ መንካት መጐነጥ፤ መጐሰም መደሰቅ መምታት። መጐጸን እይ የዚህ መንቲያ ነው። ሜከላ እመ ኀዝኮ በእዴከ ይደጕጽ ሕጻከ ደጐጻኒ ዘደጐጸ ዐይኖ ያወርድ አንብዐ ዘይደጕጸኒ ሥጋየ ደጐጸ ንግድዓሁ። ወገረ አሐዱ እምኔሆሙ አሐደ ዐጽቀ ወደጐጸ ገጸ ንጉሥ -(አፈ -ድ፲ መዝ -፴፯። ራ፳፪ -፲፱ ፪ቆሮ -፲፪ - ገድ - ተክ ዮሴፍ)

-መደጐስ፤ መደገስ ማስናዳት፤ ማሥመር ማሳመር፤ ማሰንበር ማስመጥ ማሳበጥ፤ መሸለም ማስጌጥ መልክ ማውጣት፤ ያንቀልባ የብራና ገለደን እይ

-መዳጐስ፤ ደጓሳ መኾን ወይም ማድረግ ምስጢሩ ማሳበጥ ካለው ይገባል። ደንገፀን ተመልከት፤ የዚህ ዲቃላ ነው።

ደጊፍ ፎት -(ደገፈ ይደግፍ ይድግፍ። ትግ ደግፈ) መደገፍ መደጋገፍ፤ ማጽናት ማበርታት፤ እንዳይወድቅ ማድረግ አይዞኽ ማለት። ገደፈ ማለት ከዚህ ወጥቷል፤ የዚህ ግልባጭ ነው ሶቀንና ዐመደን ተመልከት ደገፈ ያማርኛና የትግሬ ነው አንዳንድ ሰዎች ግን ብርዕ ሲሉ ብዕር እንደሚሉት፤ ደገፈ ሲሉ ገደፈ ይላሉ፤ ኹሉም ስሕተት ነው

ደጋሚ -(ሚት ምያን ያት) በቁሙ የሚደግም የሚያነብ አንባቢ ዳዊት ደጋሚ እንዲሉ

ደጋን -በቁሙዴግኖ ዴገነ

ደግደገ -(ዲቃ ዕብ ዳግዴግ፤ ነካ ዳሰሰ) ከሳ ቀጠነ ደቀቀ ረቀቀ ሣሣ ማለደ ገሠገሠ ማለዳ ተነሣ ታጠቀ ተጣጠቀ፤ ለበሰ ተላበሰ አደገደገ

ደግደግ ደግዲግ - ነግህ ጧት ማለዳ ነገታ ሳኒታ ማግስት እፎ ወድቀ እምሰማይ ኮከበ ጽባሕ ዘቢደግዲግ ይሠርቅ ወኢታትርፉ እምኔሁ ለደግደግ -(ተረ -ር፯ ዘፀ፲፪ -)

ደጐብያ -( ጎባይ ዐረ ጃቢእ) ደጐባ አንበጣ ያነበጣ ወገን ኵብኵባ ፌንጣ ሌላውም ኹሉ አናኵዕን እይ ለሰው ሲኾን ጐበዝ ወጣት ሦታ ደቦል ረድ ማለት ነው መሓዝን ተመ -(ዮኤ፩ -፬። -፳፭ ናሖ፫ -፲፭ -፲፮) ዘበልዐ አንበጣ ወደጐብያ አው ገመለ -(ቀሌ)

ደጓጺ -(ጺት ጽያን ያት) የሚወጋ የሚጐንጥ፤ ደጓሽ አሥማሪ

ደፈር -ተራራ ኰረብታ ገመገም።

ደፊር ሮት -(ደፈረ ይደፍር ይድፍር ዐረ ደፈረ ገፋ አራቀ ወዲያ አለ) መድፈር መጨከን አለመፍራት አለማፈር፤ መናቅ ማቃለል ማዋረድ ደፈርከ ትስተይ በንዋየ ቅድሳትኢኮኑ አይሁድ ይደፍሩ ይስዐሩ ካህነ ምሢመቱ እስከ ይመውት ወኢክህለ ሐዱሂ ደድፍር ላዕሌሁ -(ዮሴፍ) ይድፍር ወኢይትናገር መኑሂ ይደፍር ለምህሮ ዘንተ ደፈርከ በትዕቢትከ ሐሰወ ወደፈረ መሐላ ደፈሮ እግዚእ -(ስንክ -ጥር፰ ፊልክ -፻፱፳። መቃ -ገ፮። ቀሌ ድር)

ደፊን ኖት -(ደፈነ ይደፍን ይድፍን ዐረ ደፈነ ዳፋን ገፋ ደፋ) መድፈን፤ መምረግ መዝጋት። ዘይደፍን ዐዘቅተ ዘዞሙ ይድፍኑ ውእተ መቃብረ ዘዘ ይድፍኑ ግበባተ -(ምሳ፳፭ -፳፮ ጦቢ፰ -፲፰ ዮሴፍ)

-መቅበር፤ መሸሸግ መሰወር፤ ካፈር ከመሬት ውስጥ ማግባት መክተት፤ ከእሳት ከፍሕም መረመጥ መሸጐጥ ድፍኑ ደመ ይደፍንኑ ምሕረተ በመዐቱ ቀተሎ ወደፈኖ ውስተ ደፈንኩ ወርቅየ ውስተ መሬት። ደፈነቶ ውስተ ሐሪጽ ደፈነት ናእተ -(ኩፋ -፯። ዘፀ፪ -፲፪ ኢዮ፴፩ -፳፬ ሉቃ፲፫ -፳፩ ነገ -፳፰ -፳፬)

-መሸፈን ማልበስ መክደን። ደፈነኒ ባር ይደፍነኪ ጸበል ደፈኖሙ ማዕበል። ደፈነነ ጽላሎተ ሞት -(ኢዮ፳፫ -፲፯ ሕዝ፳፮ -፲። ዘፀ፲፭ - መዝ -፵፫) ማስታጐል ማስቀረት፤ የግብር የጸሎት ምስጢሩ ከመዝጋት ይገባል።

ደፊዕ ዖት -(ደፍዐ ይደፍዕ ይድፋዕ ዐረ ደፈዐ። ዕብ ዳፋህ) መድፋት መከንበል መግፋት መጣል መገልበጥ ደፍዐ ገባሬ ብርሃናት ዘደፍዖ ጽልመት። ታድራ ወአባ አዝለፉ ኀምሳ ዓመተ እንዘ ይደፍዑ ኅሊናቲሆሙ ስመ ኮኑ ይፈቅዱ ፈሊሰ እመካኖሙ ወኮኑ ይብሉ ስከ ረምት ነሐውር ወሶበ ይበጽሕ ክረምት ይብሉ እስከ ሐጋይ ሐውር -(ገድ -ተክ ቅዳ ያዕ ፊልክ -፷፫)

ደፋሪ -(ሪት ርያን ያት) በቁሙ፤ የሚደፍር ደፋር ጨካኝ ትቢተኛ። ጽኑዕ ወደፋሪ እምን ደፋሪ ወኢኀፋሪ ደፍርያን -(ዮሴፍ ግንዘ። ፊልክ -፪፻፫)

ደፋኒ -(ኒት ንያን ያት) የሚደፍን ደፋኝ ቀባሪ ሸሻጊ። ገብር ደፋኔ ወርቀ እግዚኡ -( - -)

ደፍተር -በቁሙ፤ደብተር

ደፍዕ -የመዝጊያ ደፍ ጕበ በመቃኖች ላይ የሚኾን።

ደፍደፈ -አጋደመ ረበረበ ደፈደፈ፤ መረገ አለበሰ ደመደመ ኹሉም የእድሞ ሥራ ነው እድሞን እይ ይደፈድፉ ናሕሰ -(ታሪ -አኵ)

ደፍደፍ [1]-ክርክራ፤ደፊዕ ደፍዐ

[2]-ክርክራ የእድሞ ቤት ጣራ፤ ሉሕ ጠርብ መረባርብ ደፍደፈ ናሕስ

ዱር -በቁሙ ደን ዎማ ብዙ ዛፍና ዕንጨት ያለበት። ታሕተ ዱር ተኀባእኩ -(አዋል)

ዱብል -(ላቲን) ደባል፤ ዕጥፍ ድርብ መንታ ፊደል፤ ደጊመ ቃል። የበበ በበ ደለለ ከለለ፤ ሐተተ ፈተተ ይህን የመሰለ ደበሎ ዐጐዛ ለምድ በላይ የሚደረብ። -(ተረት) ሀብታም ይኼዳል በበቅሎ፤ ድኻ ይለብሳል ደበሎ።

ዱድ -ስመ ነገድደዊድ ዶደ ዶድ

ዲሎሳን -(ጽር -ዲሎሲስ። ዕብ ኡሪም) የበዓል መብራቶች ለደስታና ለክብር የሚበሩ። ቃላት ነገራት ሊቀ ካህናት ልብስ የሚስሙ አልባስ ተኳህኖ ሊቀ ካህናት ቃለ እግዚ ሲጠይቅ የሚለብላቸው። ካህን ዘይለብስ ዲሎሳነ ልብሰ ዲሎሳን -(ዕዝ፪ -፰። -)

ዲቁና -ቁሙ፤ ዲያቆንነት ዲያቆን መኾን የዲያቆን ሹመት ማዕርግ። ሢመተ ዲቁና መልእክተ ዲቁና ግብረ ዲቁና -( - - -፭። - - - ስንክ -ጥቅ፱)

ዲበ -ላይ ወይዶ  ደየበ  ዲብ -ዲበላይ ወደደይቦ ደየበ ዲብ

ዲባግ -(ጋት ዐረ -ዲባጅ) ልብሰ ሐር ዝንጕርጕር ባለብዙ ሕብር ወርቀ ዘቦ ግምጃ ራያት ወዲባጋት አልባሰ ዲባጋት ቀጠንት ወኢዲባጋት። ጸውዖ ብእሲ ባዕል ለዲዮጋንስ ጠቢብ ውስተ ቤቱ ወኮነ ስርግወ በዲባጋት ወብእሲሁሰ ኮነ ግሡጸ -(መቃ። ስንክ -መስ፲፮ አፈ -ተ፳፰ ፈላስ)

ዲብ ዲበ -(ደቂቅ አገባብ) ላይ በላይ ወደ ስለ ይኾናል ሳይናበብ ሳይዘረዘር እንደ ላዕለ ብቻውን አይነገርም። ዘሐነጸ ቤቶ ዲበ ኰኵሕ ይትኀደግ ብን ዲበ እብን ሀሎ ዲቤሁ ልብስ ጥቁብ። ከልብ ይገብእ ዲበ ቅያኡ ዲበ ሀጕ ውሉዶሙ ይግ -(ማቴ፯ -፳፬ ፳፬ - ፊልክ -፻፴፮ ምሳ፳፮ -፲፩ ሔኖ፲፪ -) ኀበና ዲበ ይወራረሳሉ፤ ስለዚህ በኀበ ፈንታ ዲበ ይላል በረ ዲበ ዐዘቅት -(ዘፀ፪ -፲፭) የወዲያኛው ትግሬም ወደ ሲል ዲብ ይላል ባማርኛ ግን ጕባ ጐባታ ታናሽ ቍሊልታ አዳጋ ቦታ እንዳርባጫ ያለ ማለት ነው -(ተረት) የወዳጅ ዥብ፤ ልጄን ከዲብ ድብኝትም የዚሁ ዘር ነው

ዲብዲቆን -(ጽር ዲፕቲኮን) ሰሌዳ፤ መጽሐፈ ተዝካር የሙታን ወይም የሕያዋን፤ የማኅበርና የመምህራን የጳጳሳትና የቅዱሳን ስም በተራ የሚጣፍበት፤ የባስልዮስን ቅዳሴና ወዕቀቦሙን በእንተ ብፁዕን የመሰለ መዝገበ አስማት። መጽሐፈ ዲብዲቆን ዘቅዱሳን ኀበ ተለክአ ዲብዲቆን ዘማኅበረ ነቢያት -(መጽ -ምስ። አርጋ -)

ዲና -(ዕብራ) ስመ ብእሲት ወለተ ያዕቆብ ፍርዷ ፍርዲቱ ማለት ነው ወንድሞቿ ስምዖንና ሌዊ በርሷ ምክንያት የሴኬምን ሰዎች ስለ ዘረፋና ስለ ፈጁ ሽፍታ ኹሉ በነዚህ አምሳል ዲና ይባላል፤ የዲና ወንድም ማለት ነው ኬም ህየ በዲና ተሀጕለ ወበሳራ አቤሜሌክ ቈስለ -(ቅኔ። ዘፍ፴ -፳፩ -፳፩ ፴፬ - -፳፬)

ዲናር -(ራት። ጽር ዲናሪዮን) የገንዘብ ስም፤ ጽርኣዊ ሮማዊ ታናሽ የብር ገንዘብ የሰቅል እኩሌታ የዲድርክም አላድ ወርቅም ይኾናል -(ማቴ፲፰ -፳፰ - ፳፪ -፲፱) ዲናረ ብሩር ዲናረ ወርቅ ዲናራተ ብሩር ወወርቅ ዲናራት ወጠፋልሐ ብሩር። ዲናር ግብጻዊ፤ ዲናር ጢሮሳዊ -(፪ዜና - -፲፯ ንክ -ጥቅ፲፮ ጥር፲፩ - -፳፰ -፴፫) ደናራ ማለት ዐማርኛው ከዚህ ይሰማማል

ዲኖ -(ትግሬ) ዐጐዛ ሌጦ ደበሎ ፍርድ ልበስ ማለት ከዚህ ጥቷል ዐድልን ተመልከት። ባማርኛ ግን ጅን ጅናም የባሕር ጐሽ የጋኔን በሬ ማለት ነው ይኸውም ከባሕር እየወጣ ሣር ይበላል፤ ከየብስ እንስሳትም ይወልዳል ርሱ የሚወለድ ላም ኹሉ በጣም ብርቱ በገር አይያዝም አይጠመድም፤ ብሄሞትን እይ።

ዲያቆናይ -(ይያን -ውያን) ዝኒ ከማሁ። አስጢፋኖስ ዲያቆናይ ምእመን በሰማይ -(ድጓ)

ዲያቆናይት -(ዊት ይያት -ውያት) ዲያቆን የ፰ ዓመት ባልቴት በሴቶች ወገን እንደ ዲያቆን ኹና የምትላክ የምታገለግል ወዲያቆናዊት ትገሥጾን ለአንስት ወታዕርፎን ወትርድኦን። እለ ያወስቡ መነኮሳይያተ ወዲያቆናይያተ -(፩ጢሞ - -፱። - - ፵፰)

ዲያቆን -(ናት። ጽር -ዲያኮኖስ) ቁሙ፤ አገልጋይ የቄስ ተወራጅ በአንብሮተ እድ የሚሾም ሶበ ትሰይሞ ለዲያቆም አንብር ዴከ ዕሌሁ። ሊቀ ዲያቆናት። ንፍቀ ዲያቆን፤ የዲያቆን ተወራጅ ምክትል -( - -፯። )

ዲያብሎስ -(ጽር -ዲያቦሎስ ዐረ -ኢብሊስ) በቁሙ ሰይጣን ጋኔን ክፉ መልአክ፤ የሰይጣንን ፍች ተመልከት፤ ክዚህ ጋራ አንድ ነው። ባለመጣፎች ግን ዐማፂ ገፋዒ ጸናኒ ፈታዊ ኀሣሤ አምላክና ነድ ውዑይ ዖፍ ሰራሪ ይሉታል፤ ዘይቤው ከደየበና ከደበወ፤ ምስጢሩ ከሰይጣን ይሰማማል -(ጥበ፪ -፳፬ ማቴ፬ -፩። ፲፫ -፴፱)

ዲዮስቆሪዶስ -(ጽር -ዲዎስኩሮን) መንታ ጣዖት ወንድማማች የድያስ ልጆች የሚባሉ ባለሐዲሶች ግን መስቀል ይሉታል -(ግብ፳፰ -፲፩)

ዲዮስቆሮስ -(ጽር -ወቅብጥ) የሰው ስም፤ በዳኬዎስና በመርቅያን ዘመን የነበረ ሰማዕት ያምላክ ወገን ቤተ ሰብ ልደ ቤት አገልጋይ -(ቅዳ ሃይ -አበ)

ዲዮስጶራ (ጽር ዲያስፖራ) ዝርዋን በዝርወት ዘበስደት ዘበፍልሰት (ያዕ፩ )

ዲዲሞስ [1]-መንቲያዴደየ

[2]-(ጽርእ። ዕብ ቶማእ) መንታዊ፤ መንቲያ ማለት ነው፤ ቶማስን እይ -(ዮሐ፲፩ -፲፮)

ዲድስቅልያ [1]-የመጣፍ ስምደይደስ

[2]-(ጽር -ዲዳስካሊያ) የመጽሐፍ ስም ኛው የሐዋርያት መጽሐፍ፤ ትምርት ማለት ነው። ወሣልስ መጽሐፍ ዲድስቅልያ ዘውእቱ ትምህርት፤ ወኍላቌሁ አርብዓ ወሠለስቱ አንቀጽ -( - -መቅ)

ዲድርክም [1]-የገንዘብ ስምደይደር

[2]-ዲድርክም ሜ፤ -(ጽር፤ ዲድራኽሞን ) የገንዘብ ስም እንደ ሩብና እንደ ፈረንክ ያለ አንዱ ዲድርክም ኻያ አቦሊ ነው። የአቦሊን ፍች ተመልከት -(ዘሌ፳፯ -)

ዲፍራን -(ሱር ዳፍራና) ጥድ የጥድ ይነት ዛፍ። ባለብሉዮች ግን ቀረጥ ይሉታል -(ኩፋ -፳፩)

ዲፓ -(ዲባ) (347) ሸመቃ ሽመቃ ደበቅ ጦር ደባ ተንኰል። ነበረ ዲፓ። ቆመ ዲፖ ጸንሐቶ ዲፓ ንጉሥ። ወይጸንሕዎ ሎቱ በዲፓ -(፩ነገ -፲፭ -፭። መሳ፱ -፵፬። ዮሴፍ)

ዳሕል -ድል ሽሽት ኵብለላ።

ዳሕመመ -ቈፈረዳህምሞ ዳህመመ።

ዳህምሞ ሞት -(ዳህመመ ይዳሀምም ይዳህምም። ዕብ ዳሀም ብህመ) መቈፈር መኰትኰት ዐፈር ማስታቀፍ መቈለል መደመም፤ መመደብ፤ መደብ መሥራት ላታክልት ደመመን እይ፤ የዚህ ጎር ነው።

ዳኅነ ድኁነ -ይኅና ደኅና ወደ ደኅና ድኖ ደኅና ኹኖ ዳኅነ ሀሉ ዳኅነ ይትናገሩ ቢጾሙ። ትነብር ዳኅነ ለእመ ዳኅነ አቶክ ይሬኢ ዳኅነ ወርእየ ዳኅነ መጽአ ድኁነ -(ግብ፳፫ -፴። ኤር፱ -፰። ኢዮ፲፩ -፲፰ ጦቢ፭ -፲፮። ፲፩ -፯። ማር፰ -፳፭ ዘረፋ)

ዳኅና -ደኅንነት፤ ጤና ላም፤ ትንሣኤ ሕይወት። አልቦ ዘይስእል ዳኅናኪ። ተስእሎ በእንተ ዳኅናሁ ይዜንዉከ ዳኅና ብሔር እነግር ጽድቀከ በዳኅናየ በእንተ መንክር ዳኅናሁ -(ኤር፲፭ - ነገ -፲፩ -፯። ፩ነገ - -፬። ኢሳ፴፰ -፳። ጥበ፭ -) በዳኅን ፈንታ ዳኅና ይላል ስሕተት ነው። ነበረት ሀገር ዳኅና -(፬ነገ -፲፩ -)

ዳኅን -(ንት ናን ናት) የዳነ፤ የሚድን ደኅና ባለጤና፤ ንጹሕ ጽሩይ ዳኅንኑ ዳኅን ዳኅንኑ ማኅተምርኢ ለእመ ዳኅናንኑ አኀዊከ ወአባግዒሆሙኒ -(ገድ -ተክ። ዳን፲፫ -፲፯ ዘፍ፴፯ -፲፬ ፵፫ -፳፯ ማቴ፳፫ -፲፮ -፲፰) በዳኅና ፈንታ ዳኅን ይላል ወኮነ ሰላም ወዳኅን ላዕለ ኵሉ በሓውርት። ዳኅን ወሰላም -(ገድ -ተክ። -ተሰ - -፫። ቀሌ)

ዳኅፅ -(ፃት) ዳጥ ድጥ መሰናክል ዕንቅፋት ኀጢአት ሕገ ሥራ። ጭንጋፍ ውርጃ ዳኅፅ ወጽልመት ያመጽኡ ዳኅፀ ሕዝብ በሳነ ስረይ፤ ወዳኅፃቲነ እምሕግ ይኄይስ እምኔሁ ዳኅፅ -(መዝ -፴፬። ዳን፲፩ - መክ፮ -)

ዳሕፍ -ዳፋ ግፍ ግፊ፤ ድቀት ፍዳ ጡር የክፉ ብድር።(ተረት) የኃጥኡ ዳፋ ጻድቁን አዳፋ ያመሥጥ ኃጥእ እምነ ዳሕፍ -(ሢራ ፲፮ -፲፫)

ዳሌጥ -(ዕብ ዳሌት ጽር ዴልታ ግእ ድልት) ስመ ፊደል ብዕ መዝጊያ ሳንቃ ማለት ነው -(መዝ -፻፲፰ -፳፭ ሰቈ፩ -፬። -፬። -፱። -)

ዳልጋ -(ዐማርኛ) የባሕር በሬ ጅን የበሬ ዐንገት ርፉ እንጥልጥሉ ቈርበት ደላጎ የጤፍ ዛላ ማናቸውም ትርፍ ነገር ኹሉ።

ዳስ -ቁሙ፤ ጥላ ከለላ፤ የሣር የቅጠል ጐዦ ግርዶ ከሐሩር ከቍር የሚሰውር ዳሰ ዐቃቤ ወይን ከመ ትግበር ዳሰ ኀበ ትነብር -(ኢሳ፩ -፰። ፲፮ -)

ዳራጊ -(ጊት ግያን ያት) በቁሙ የሚዳርግ ሰጭ አሰጭ፤ ድርጎ አውጭ ባለገንዘብ።

ዳርባን -(ዕብራ) መድጐጸ ላሕም፤ አርቃሾ መውጊያ መጓጐጫ ህየንተ ጅራፍ

ዳርጎ ጎት -(ዳረገ ይዳርግ ይዳረግ) መዳረግ ማስተላለፍ፤ ሰጭን ከተቀባይ መግጠም፤ የገንዘብ የቀለብ። ለእመ ዳረገ ሠያጢ ዕለ ተሣያጢ ብእሴ በንዋይ -( - -፴፫ -)

ዳሮም -(ዕብራ) ደቡብ፤ የሰሜን አንጻር -(ሕዝ፳ -፵፮)

ዳባር -(ዕብራ) ነገር ቃል ባህል ብሂል አንዳች ዳይ መፍቅድ

ዳቤላ -(ላት) ደቦል፤ ታላቅ የፍየል አውራ፤ የሚደረብና የሚታዘል የሚንጠላጠል፤ የላም ውራ ኰርማ ወይፈን። ዳቤላ ዘጠሊ ሰብዐቱ ዳቤላት። ንስሐቦ ለዳቤላ ዘላሕም -(ዳን፰ -፭። ኩፋ -፲፮ መጽ -ምስ)

ዳቤላም -(ዕብ ድቤሊም) የበለስ ቋንጦች ቍጥራቶች እንደ መቍጠሪያ የተሰኩ። አንዱን ስክ ድቤላ ይለዋል፤ እኄላን ተመልከት ዚህ ጋራ አንድ ነው። ባለብሉዮች ግን ዕፅቦ ጕርዶ የወጣለት ዶቄ ይሉታል -(፩ዜና -፲፪ -)

ዳቤር -(ጽር ዳቢር ድቢር) መቅደስ ቅድስተ ቅዱሳን፤ ባርባው ክንድ ፊት ያለ ኻያው ክንድ፤ መካነ ታቦት ቃለ እግዚ የሚሰማበት፤ የሚነገርበት -(፫ነገ - -፲፮ -፲፱፳፫ - -፰። ፀ፳፭ -፳፪)

-ስመ ሀገር ታናሽ ከተማ በይሁዳ ክፍል ያለች፤ ካሌብ የወረሳት እለ ይነብሩ ውስተ ዳቤር ወስማ ለዳቤር ሀገረ መጽሐፍ -(ኢያ፲፭ -፲፭) ዳቤር ያለውን ነገር እንደ ማለት መጽሐፍ ብሎ ፈታው፤ መጽሐፍን ዳቤር ድቢር ማለት በፋርስ ቋንቋ ነው ይላሉ -(ረበናት)

ዳታን -የሰው ስም ሥርዐት ማለት ነው ፪ኛም ነቅዓዊ ይሉታል -(ዘኍ፲፮ -፳፬)

ዳነተ -(ዐማርኛ) ቁሙ፤ ጮኸ ተቈጣ ኀይለ ቃል አወጣ ነገሩ ችንካር ነው እንዲሉ

ዳነየ -(ደየነ) (ደየነ) ዳኘ፤ ፈረደ። ኢይዳንየነ ንጉሥ -(ታሪ -ነገ ኢያ)

ዳናት - ቀኖት ሣልስ የግራ እጅ ዳናት ዘበትርጓሜሁ ሣልስ -(መጽ -ምስ)

ዳናዪ ዳኒ -ደያኒ፤ የሚዳኝ ዳኚ ዳኛ፤ እውነተኛ መካከለኛ የፍርድ ሚዛን። -(ተረት) ዳኛ የወል፤ ምሰሶ የመካከል። ዳኛ ቢያደላ በዳኛ፤ አህያ ቢያጋድል በመጫኛ። ዳኒና ደኃኒ ባማርኛ ይተባበራሉ። -(ግጥም -በቴዎ ጊዜ) ይልማናና ዴንሳ ቁሞ ይሟገታል ይህን በጌምድርን ማን ዳኛ() አድርጎታል። ዳነየ ያማርኛ እንጂ የግእዝ አይዶለም።

ዳን -የዲና ወንድም፤ ስመ ነገድ ስመ ገር ፈረደ ማለት ነው ሰመየእቶ ስሞ ዳን ተለዎሙ እስከ ዳን። እምዳን እስከ ቤርሳቤሕ -(ዘፍ፴ -፮። ፲፬ -፲፬ ፪ነገ -፲፯ -፲፩)

-ስመ ገድደይኖ ደየነ

ዳንስ -(ሮማይ) ዘፈን እስክታ፤ የዝሙት ዋዜማ። እንስሳውን ገራም ጭምት ሲሉ ደንሴ ማለት ዐማርኛው ከዚህ ይሰማማል

ዳንኤል -(ዕብ ዳኒኤል) ሰብእ ጻድቅ ነቢይ ፈላስፋ። አምላክ ደያኒየ መደይንየ የሚፈርድል() ፈራጄ ዳኛ ማለት ነው -(ዳን፩ -፮።  ሕዝ፲፬ -፲፬። ፳፰ -) ደየነን እይ

ዳንዮት -መዳኘት፤ ዳኝነት፤ የዳኝነት ሥራ።

ዳዒ -(ዕብ ዴዒ፤ ዴዓ ዳዐት) ዕውቀት ዕውቂያ፤ ማስተዋል።

ዳዕሙ -እንጂድኢም ደአመ ዳእሙ

ዳእሙ -(ትግ ደአም) ዐቢይና ንኡስ አገባብ እንጂ ግን ብቻ ይልቅ ይኾናል፤ እንጂና ግን ብቻና ይልቅ አንዳንድ ወገን ናቸው፤ ሲገባም እንደ ባሕቱ በፊት በኋላ ይገባል አላንና ባሕቱን ተመልከት ኃጥኣንሰ አኮ ከመ ዳእሙ ከመ መሬት እንጂ። ኵሎ ዘቦ መጠውኩከ ዳእሙ ኪያሁ ኢትግስስ ግን። እሉኑ ዳእሙ ደቂቅከ ብቻ ወይቤሎ አልቦ ዳእሙ ፈንወኒ፤ ይልቅ ብቻም ይኾናል -(መዝ -፩። ኢዮ፩ -፲፪ ነገ -፲፮ -፲፩ ጦቢ፲ -) -(ዕር፲፱ -ቍ፹፩)

ዳዕሮ -የዛፍ ስም፤ ወርካ ዋርካ የሾላ የባንባ ይነት፤ ወፍራም ደንዳና ታላቅ ግዙፍ ጽቁ ግድም የሚኼድ ወደ ምድር የሚወርድ የሚሰፋ የሚንሰራፋ እንደ ወርካ ያስፋኽ እንዲሉ። -(ግጥም ስደተኛ ላቱ ሹም ስለ ተሻረና ስለ ሞተ) ወርካ ምድር ደረሰ ንግሪ፤ እንግዴህ ልመለስ ልግባ ወዳገሬ። ወይጼድሎ ዖመ ዳዕሮ -(ኢዮ፵ -፲፯) ዕብራይስጡ ግን አርዘ ሊባኖስ ይላል 

ዳዊት [1]-(ዕብ ዳዊድ) የሰው የእስራኤል ንጉሥ ፍቁር መፍቀሪ -(፩ነገ -፲፮ -፲፫)

[2]-(ዕብ ትሂሊም) የመጽሐፍ ስም መጽሐፈ መዝሙር ዳዊትና እንደ ዳዊት ያሉ እነአሳፍን የመሰሉ የግዜር መዘምራን የደረሱት ብዙው የዳዊት ስለ ኾነ በዳዊት ተጠርቷል እንጂ ፻፶ው ኹሉ የርሱ ይዶለም ይኸውም በያርእስቱ ይታወቃል ከምርኮም በኋላ የተደረሰ አለ ይልቁንም እግዚኦ ጻወነ ኮነከነ ካለው ምሮ ምሕረተ ወፍትሐ እስከሚለው ድረስ ፲፩ዱ መዝሙር የሙሴ ይባላል። ምእት ወኀምሳ ዳዊት ጸሎት ዘእምዳዊት በዜማ -(ግንዘ)

()          »ዳዋ -(ዐማርኛ) ዝኒ ዓዲ ማሁ በቁሙ ዱር ጥሻ ጣሻ። -(ተረት) ዐይጥ በበላ ዳዋ ተመታ።

ዳየር -አንባ ኰረብታ ዙሪያው ገደል የግሼና የግሸን ተራራ፤ ምስጢሩ ገዳምነት ነው።

ዳይቅ -(ዕብ ዳየቅ) መቃኰሻ ግንብ የውጭ ጠላት በቅጥር ዠርባ የሚሠራው ወይም በዚያ ላይ ኹኖ እንዳንደርቢ ወደ ከተማ የሚሰደው የሚወረውረው ደንጊያ። ከመ ይሕንጽ ዳይቀ -(ሕዝ፳፩ -፳፪)

ዳግመ -ደግሞ መልሶ ተመልሶ ዳግመኛ። እም ዳግመ ዓዲ ዳግመ። ወካዕበ የሐውር የአብስ ዳግመ ዳግመ ይመጽእ -(ኤር፫ -፩። መሳ -፲፫ -፱። ሢራ፴፩  -፴፩። ቅዳ)

ዳግማዊ  ዳግማይ -(ዊት ውያን ያት) (ዪት ሚት፤ ይያን ያት) በቁሙ ኹለተኛ ታናሽ ተከታ ምክትል። አባ ማርቆስ ዳግማዊ ወልደ ዳግማዊት ብእሲት። ዳግማይ ዳም ሰማይ ዳግሚት -(ስንክ -ጥቅ፳፫ መስ፬ ውዳ - ቅዳ ድጓ)

ዳግም -(ምት ማን ማት) ድጋሚ ዳግሞሽ ዳግመኛ ኹለተኛ። ዳግም ልደት ዳግም ዳግም ሪት ዳግም ብእሲ ዕቀጸኒ ወናሁ ዳግሙ ዮም ሰላም ለክልስትያኖስ ለዮናክንዲስ ዳግሙ -(ማቴ፲፱ -፳፰ ራእ፪ -፲፩ ዘዳ፲፯ -፲፰ ቆሮ -፲፭ -፵፯። ዘፍ፳፯ -፴፱። ስንክ -ም፫)

ዳጎን -(ዕብራ) ጣዖት የባሕር ዳር ዎች ኢሎፍላውያን የሚያመልኩት፤ ፊቱና ራሱ የሰው፤ ግንዱና ገላው መለመላው የደራጎን ያሣ፤ ዐይነቱ ሦርዞና ጐርዞ ወይም አንባዛና ዐዞ የሚመስል። ዳግ ዓሣ፤ ዳጎን ዓሣዊ ዓሥማ ዓሦ ማለት ነው፤ ዥቦ ነብሮ እንደ ማለት -(፩ነገ - -)

ዳፈን -(ዐማርኛ) ያዳፋኝ መቀጮ።

ዳፍን -(ጽር ዳፍኒ) የዛፍ ስም ሽቱነትና ቅመምነት ያለው ቅጠሉን ስለ ከበሬታ ቄሳሮች የሚቀዳጁት። ባለብሉዮች ግን ጥድ ይሉታል -(ኩፋ -፳፩)

ዳፍንት -ቁሙ የዐይን በሽታ ከማታ እስከ ጧት የሚያሳውር ዳፍንታም እንዲሉ

-ቂጣ ብርኵታ ርሚጠ፤ ንባሻ ሽልጦ በረመጥ በፍሕም ቀብረው አዳፍነው የሚያበስሉት የባላገር ኅብስት -(ዘፍ፲፰ -፮። ፲፱ -፫። ዘፀ፲፪ -፴፱) ግበሪ ዳፍንተ ወአምጽኢ ሊተ። ይግበራ ዳፍንተ -(፫ነገ -፲፯ -፲፫ ኤር፯ -፲፫)

ዴር -(ሱር -ዳይራ። ዐረ ደይር) ገዳም ዱር፤ የመነኮሳት ሰፈር ዘሩ ደዊር ነው ወና ተወራራሾች ስለ ኾኑ በየ ምክንያት ወደዚህ መጥቷል፤ ዱርና ዴር ስም ናቸው ተሐንጸ ተዝኪር ወኀበ ተሣረረ ዴር -(ስንክ -የካ፱)

ዴቆነ -(ይዴቁን ይዴቁን) ዲያቆነ ዛቆነ ዲያቆን ኾነ ዜቆነን ተመልከት፤ የዚህ ሞክሼና መንቲያ ነው።

ዴዳን [1]-ስመ ነገድደይዳን

[2]-(ዕብ ድዳን) ስመ ነገድ የኵሽ የልጅ ልጅ፤ የሽባእ ወንድም ዐደንን ያቀና ያረቦች አባት -(ዘፍ፲ -፯። ሕዝ፳፯ -፲፭) የአብርሃም ልጅ ከኬጡራ የተወለደ -(ዘፍ፳፭ -)

ዴዴ [1]-ደጅ፤ደይደየ፤ ዴደየ።

[2]-( ዴዴያት ዴዳያት ዴድያት) ደጃፍ በረንዳ ወልወል፤ የቤት መዠመሪያ ክፍል፤ ክበር ከቅጥር በውስጥ ያለ ቦታ ወይም ታላቅ የውጭ በር ደጀ ላም ዴዴሁ ለባዕል ውስተ ዴዴ ቤተ ክር በዴዴያተ አብያት። ዴድያተ አንቀጽ። ወዴዳያቲሃ -(ሉቃ፲፮ - ቀሌ ሕዝ፴፫ -፴። ኤር፩ -፲፭ ራእ፳፩ -፳፩)

ዴድዮ ዮት -(ዴደየ ይዴዲ ይዴዲ። ዕብ ዳዴህ፤ ሂዳዴ) መዝለል መፈንጨት፤ እንጥር ፍንጥር ድቅ ድቅ ማለት የግልገል የጥጃ። አካኼድ አረማመድ መማር፤ ማስተማር ዳዴ ዳዴ ወይም አቱ ሥግራ ታቱ ሥግራ ማለት የሕፃን የሞግዚት።

ዴጋኒ -(ኒት ንያን ያት ዴገንት) ደጋኝ አጥማጅ ዐዳኝ። የሚከተል ተከታይ ፈላጊ አባራሪ ዠግና፤ ሯጭ ገሥጋሽ። ኤዎስጣቴዎስ አሠረ ቶማስ ዴጋኒ ዴጋኔ ፀሩ -(ድጓ ስንክ -ሚያ፳፰)

ዴጋን ደጋን -(ናት) በቁሙ ቀስት የንጨት የብረት ጐባባ ጐባጣ ጠማማ ደጋን ያማርኛ ቀስት የግእዝ ነው። እለ ፍናዊሆሙ መብእስ ወደጋን መንኰራኵሮሙ -(ምሳ፪ -፲፭)

ዴግሬ -(ላቲን ግራዱስ) ደረጃ ዕርከን ልክ ሚዛን እንደ ድግር የተካከለ።

ዴግኖ ኖት -(ዴገነ ይዴግን ይዴግን። ትግ ዳገነ። ዕብ ዳዮግ አሥግሮ ዓሣ) ተል ማባረር፤ መሻት ማደን ማጥመድ ማለብ መደገን ለመያዝ ለመግደል ለመማረክ ዴግንየ እአኅዞሙ። ዴግንዎ ወትእኅዝዎ። ይዴግንዋ ለኦሪቶሙ። ለእመ ዴገንካ ለጽድቅ ትረክባ ይዴግን ሐመልማል -(ዘፀ፲፭ -፱። መዝ -፸። ሮሜ፱ -፴፩። ሢራ፳፯ -፰። ኢዮ፴፱ -)

ዴፐ ደየፕ [1]-(ደበወ ደበየ) ሸመቀ አሸመቀ፤ አደባ ደፈጠ ተደበቀ ለመግደል አደጋ ለመጣል ዘዴፐ ለከ ይቅትልከ። ዴፑ ፍኖት -(ዮሴፍ)

-ጦር ወጥመድ፤ ኖረ፤ ደበቀ ሸሽገ። ዴፐ ሎቱ ዕደወ ከመ የኀይል ቦቱ -(ዮሴፍ)

ዴፐ ዲፓ -ሸመቀ፤ ሽመቃ፤ደየፐ

ድኁኅ -(ኃን ኃት ኅኅት) የተፋረ የተጠረበ የተወቀረ ጥርብ ውቅር ድባር ድኁኃን -(ድጓ። ማሕ፪ -፲፯ -፲፬) ዋሻ ፍርኵታ አንባነት ዕርድነት ያላቸው፤ ደንጊያ የመላባቸው ማለት ነው ባለብሉዮች ግን ጽኑዓን ይሉታል፤ ባለቅኔዎችም ደኅኀ ጸና ይላሉ

ድሑር -(ራን ራት ሕርት) የተዳረ፤ የተፈታ ገለሞታ። ውሰበ ድሕርተ አርኰሰ ሥጋሁ -(ዲድ -፴፫)

ድኁር [1]-(ራን ራት ርት) የተመረቀ ምሩቅ። የቈየ የዘገየ

[2]-(ዐማርኛ) ጭር ግጭር ድንክ ጐባጣ፤ ሕጹጽ ታናሽ። ግናይን ተመል

ድኁን -(ናን ናት ኅንት) የዳነ ያመለጠ ደኅና የኾነ የተፈወሰ ጥዑይ፤ ንጹሕ ጽሩይ ያልተነካ ኢድኁን አንተ በሞተ ኢየሱስ። ይረስዮ ምስለ ድኁናን ድኁነ ምስማዕ ወንጻሬ ድኁን እምነውር ድኁን አነ እምሐሜት ክርስቶስ ድኁን ውእቱ አምኀንጣውእ። ነፍስ ድኅንት -(መጽ -ምስ ግንዘ - -፵፫ -፩። አፈ -ድ፬ ፲፭ ድጓ)

ድሑክ -የዳኸ የሚድኽ ታናሽ እግረ ንትሽ ደካማ እንዳሽኮኮና እንደ ላጽቂት ያለ ማናቸውም ፍጥረት

ድኁይ -የተቈፈረ የተማሰ ጥልቅ። ተገድፈ ሥጋከ ውስተ ክርየት ግብ ድኁይ -(ደራሲ)

ድኂኅ ኆት -(ደኅኀ ይድኅኅ ይድኀኅ) መፋር መፈርፈር፤ መጥረብ መውቀር፤ የዋሻ የጐሬ

ድሒል ሎት -(ድሕለ ይድሕል ይድሐል ዐረ ደሐለ) ድል መኾን መሸሽ መኰብለል፤ ማምለጥ መራቅ መደበቅ መጽሐፍ ግን በድሕለ ፈንታ ተድሕለ ይላል። አመ ተድሕሉ ወጐዩ እምገጸ ሮድስ ዘተድሕለ እመንግሥተ ዓለም ዘተድሕለ -(አዋል። ስንክ ሚያ፰ መስ፱)

ድሒር ሮት -(ደሐረ ይድሕር ይድሐር ዐረ ደሐረ) ማባረር መስደድ፤ መፍታት መልቀቅ፤ ከቤት ማሶጣት ማሰናበት -(ማቴ፲፱ -፱። ማር፬ - -፲፩። ሉቃ፲፮ -፲፰) ዘይድሕር ብአሲቶ ዘእንበለ ትዘሙ። ኢይድሐር ብእሲ ብእሲቶ -(ቀሌ። ዲድ -፴፫)

-መዳር ማጋባት ሴት ልጅን በሕግ በሥርዐት ለጮኛዋ መስጠት ምስጢሩ ያው ማሶጣት ነው ለወንድ ልጅም ይነገራል። -(ግጥም ልጃገረድ ስላባቷ ስርግ) እንዲህ ያለ ዘመን የተበላልጨ፤ ባቴ ተዳሩ እኔ ተቀምጨ።

-ማዘዝ መፍቀድ አድርግ ማለት ምስጢሩ ከማሰናበት ይገባል ሙሴሰ እከየ ልብክሙ ደሐረክሙ ትኅድጉ አንስቲያክሙ -(ማቴ ፲፬ -)

ድኂር ሮት -(ደኀረ ይድኅር ይድኀር አኀረ ዐረ ደኀረ እሰ) መቈየት መዘግየት፤ ማፈግፈግ ወደ ኋላ ማለት በኋላ መቅረት ኋለኛ መጨረሻ መኾን፤ በግብር በነገር በማናቸውም ከመ ይትመየጥ ወኢይድኀር ለእመ ነበረ ሕዝባዊ ሠለስተ ሰንበት ድኂሮ እምቤተ ክርስቲያን ይክልእዎ ትድምርተ -(ዮሴፍ ቀኖና -ግንር) ብዙ መጽሐፍ በደኀረ ፈንታ ተድኅረ ይላል፤ ስሕተት ነው። ተድኂሮ መጽአ ኢይበድሩ ወኢይዴኀሩ አሐደ ዕለተ። በእንተ እለ ተድኅሩ። መሂ ኤጲስቆጶስ ተድኅረ እምስብሐተ ነግ ወኢተድኅረ አሐዱ እምኔሆሙ ገቢረ ዝንቱ ንበለ ተድኅሮ -(ኪዳ። ሔኖ፸፬ -፲፪ ቅዳ። ቀሌ ዮሴፍ ስንክ -ኅዳ፲)

-መመረቅ፤ መባረክ፤ ማመስገን። ሶበ አሐዱ ይድኅር ወካልኡ ይረግም። ጸጋዊ ይድኅርዎ በሥነ ምግባሩ ደኀረኒ ዘይመውት ይድኅሩኒ ስኡናን ይድኅሩኒ አራዊተ ገዳም ይረግሙነ ወንሕነ ድኅሮሙ። በአፉሆሙ ይድኅሩ ወበልቦሙ ይረግሙ -(ሢራ፴፩ -፳፱። ፴፬ -፳፫ ኢዮ፳፱ -፲፫ ፴፩ -፲፱ ኢሳ፵፫ - ቆሮ - -፲፪ መዝ -፷፩። ፸፩)

ድኂን ኖት -(ድኅነ ይድኅን ይድኀን ዕብ ያሾዕ ሂዋሼዕ) መዳን ማምለጥ መውጣት፤ ተያዙ በኋላ፤ ወይም ሳይያዙ መቅረት መትረፍ፤ እንዳይያዙ መኾን መጠንቀቅ መጠበቅ በሕይወት መኖር መታደስ መለምለም። -(ዐጋዥ ረዳት ጠበቃ ወባት ዋስና መድን ተያዥ ማግኘት) እንደ አዳም ሐይወን ተመ የዚህ መንቲያ ነው ሐይወ የግእዝ ድኅነ ያማርኛ። አልቦ ድኂን። መዋዕለ ድኂን ድኂኖ እምባሕር ወድኅነ ጢጦስ በይእቲ ዕለት እምቀትል ሠለስተ ጊዜያተ ወልደተ ዓለም ለድኂን ይእቲ ድኅነት -(ኩፋ - አስቴ፱ -፳፱ ግብ፳፰ -፬። ዮሴፍ ጥበ፩ -፲፬ ሄርማ)

ድሒክ ኮት -(ድሕከ ደሐከ ይድሕክ ይድሐክ) መዳኽአጐንብሶ እጅና በእግር መኼድ፤ ወይም እጅን ተይዞ በእግር ብቻ መወናከር፤ አካኼድና አረማመድ መማር ለፊደልም ይኾናል። በድሒክ ውስተ መርሕብ። ሐንካስ ድሕከ እስከ ይበጽሕ ኀበ አባ ሳሙኤል ይድሕክ ወይስእል። ወድሕከ ዲበ ምድር ይድሕክ በነቢበ ፊደላት -(መጽ -ምስ። ገድ -ሙ። ስንክ -ሐም፲። አፈ -ተ፳፮) ድኳ ዳክዬ ድኻ ድኰት ማለት ዚህ ወጥቷል

ድኂፅ ፆት -(ድኅፀ ይድኅፅ ይድኀፅ ዐረ ደሐፀ) መዳጥ መሰናከል፤ መውደቅ የእግር የቃል ከመ ኢይድኀፅ ሰኰናየ ይኄይስ ትድኀፅ ወትደቅ ውስተ ምድር እምትድኀፅ በአፉከ ትድኅፅ ምክሩ ኢንድኀፅ በኀጢአት ከመ ኢንድኀፅ እምርትዕት ሃይማኖት -(መዝ፲፮ ሢራ፳ -፲፰ ኢዮ፲፰ -፯። ዲድ - ፳፭) -(ጥጨ) መጨንገፍ መውረድ ጭንጋፍ መኾን የፅንስ የሽል። መዳጥ መደፍጠጥ፤ መርገጥ መዠለጥ -(ዐማርኛ)

ድሒፍ ፎት -ድሒፍ፤ ት፤ -(ደሐፈ ይድሕፍ ይድሐፍ። ዕብ ዳሐፍ) መግፋት ማዳፋት መገፍተር፤ ማጣደፍ ማባረር።

ድኅረ -(ዐቢይና ደቂቅ አገባብ) ኋላ በኋላ፤ ወደ ኋላ ምስጢሩ ጊዜ ነው እም እንተ ይሰማሙታል ዐቢይ ሲኾን አምድኅረ ተደሩ ወእምድኅረ መስሑ እያለ በቀዳማይ ይገባል። ደቂቅ ሲኾን በቦታ በጊዜ ይገባል። ሰማዕኩ በድኅሬየ ቆመት እንተ ድኅሬሁ ድኅረ ማዕጾ ፈረሱ ለፈርዖን ይቤ ድኅረ ድኅረ ስመ እግሩ ኢለመደ ባሕረ፤ ቦታ -(ሕዝ፫ -፲፪። ሉቃ፰ -፵፬። ኢሳ፶፯ -፰። ቅኔ) እምድኅረ ሕቅ። ምድኅረ ፍልሰተ ባቢሎን። ወድኅረ ኵሎሙ ስተርአየኒ ሊተ ቅድመ ጠይቅ ወድኅረ ትጌሥጽ ጊዜ -(ማር፲፬ - ማቴ፩ -፲፪። ፩ቆሮ -፲፭ -፰። ሢራ፲፩ -) -(ዕር፲፱ -ቍ፸፱)

ድኅሪት -ኋሊት የኋሊት ኋላ እንግሊላ። የሐርስ ድኅሪተ እሱራን ድኅሪተ። ገብኡ ድኅሪተ ይደቁ ድኅሪተ -(ሉቃ፱ - መዋሥ ስንክ -ሐም፳፭ ኢሳ፳፰ -፲፫)

ድሕር -ኋላድኅር

ድኅር -(ራት) ኋላ ርባ፤ ማዥራት እስ ተረክዝ በዠርባ አንጻር ያለ ቦታ የኋላ ኋላ፤ ጓሮ። ድኅሬሆሙ ለእልክ አልሕምት ይኔጽር ውስጠ። ገቦሃ ዘድኅር። ዘባን እን ድኅር -(፪ዜና - -፬። ግብ፳፯ -፵፩። ቅዳ -ሕር)

ድኅርና -ደኃራዊ ኋለኛ መጨረሻ መኾን። ለቅድምና ወለድኅርና -( - -መቅ)

ድሕነ -ዳነድኂን ድኅነ።

ድኅነት -መዳን መፈወስ ደኅንነት ጤና ወአንከሩ እምድኅነቱ ምአይቴ ተሰፈዉ እሉ ድኅነት ሕፃን ድኅነተ ልብ ወአባል ድኅነት እምደዌያት። ጾመ ድኅነት ምሕላ ድኅነት -(ስንክ -ሐም፳፬ አፈ -ድ፳፮ - -፬። መር - ድጓ)

ድሕንጻ -( ሕንጻ) በቁሙ እደ ሕንጻ፤ የክራርና የበገና የመሰንቆ መምቻ፤ እድ ልጁ ሕንጻ እናቱ። ንባቡ ሐነጸን ምስጢሩ ደጐጸንና ደነጸን ይመስላል ጥሬነቱ ግን የሐነጸ ነው። እድ ውእድ ተብሎ ወደ እንደ ኼደ ሕንጻም ድሕንጻ ተብሎ ወደ መጥቷል። በድሕንጻ መንፈስ ዝብጢ አውታረ መሰንቆሁ ለልብየ እብል ሰላመ በልሳንየ ድሕንጻ። ፎጢኖስ ኮገከ ንዚራሁ ለመንፈሰ ሰይጣን ወመሰንቆሁ ለመንፈሰ ሐሰት ወደጐጸከ ድሕንጻሁ -(ሳታት ንክ -ጥቅ፳፯ መጽ -ምስ)

ድኅንጻ -በቁሙድሕንጻ

ድሕይ ዮት -(ደሐየ ይድሒ ይድሐይ ዐረ ደሐ ሱር ዳሒሓ) መፍጨት ማድቀቅ፤ መገርደፍ መሰለቅ፤ ማዞር ማሽከርከር መግፋት መመለስ የመጅ

ድሕጸ -ዳጠድኂፅ ድኅፀ።

ድኅፀት -መዳጥ -(ጥዳ) መዳጥ አዳዳጥ ድጦሽ መሰናክል -(ፊልክ -፻ሮ፩። ፈላስ)

ድሉል -(ላን ላት  ልልት) የተመየደ የተከፈከፈ ክፍክፍ ወይም ወደ ታች፤ የተጣሰ የተዝረፈረፈ፤ ግልስልስ ያለ የተቈናዘለ፤ የተጋመደ የተመሳቀለ ድምድማሁ ድሉል ሥዕርት ርእስኪ ድሉላት ሕይት ይእቲ ብእሲት ድምድማሃ ድሉል -(ማሕ፭ -፲፩ አርጋ -፮። -ተክ)

ድላሌ -( -ጥ። ) መከፍከፍ አከፋከፍ ፍከፋ ክፍክፋት፤ የጠጕር ሥራ ዐይነቱ መልኩ፤ ጠባዩ ኣኳዃኑርእሱ ወርቀ ቄፋዝ ወድላሌሁ ጸሊም ከመ ቋዕ ለሥዕርትኪ ሰላም ዘድላሌሁ ጸሊም -(መጽ -ምስ። ደራሲ)  

ድላግ -ዝላይ ውርወራ መከታ፤ የሰልፍ ሥራ ከመ ያእትት እምላዕሌየ ዘቀትለ ፀራዊ ድላገ ውሒዘ ረድኤትከ ይኩን በዐውድየ ዐይገ -(ደራሲ)

ድልማኑታ - ሀገር፤ የገሊላ ምዕራብ -(ማር - -)

ድልቅልቅ (ቃት) - ሁከት ውጽውጽታ ብር ድብልቅልቅ አድለቅለቀ ዐቢይ ድልቅልቅ። ወናሁ ኮነ ዐቢይ ድልቅልቅ ወይከውን ዐቢይ ድልቅልቅ ወረኀብ በበ ብሔሩ -(ግብ፲፮ -፳፮ ማቴ፳፰ - ሉቃ፳፩ -፲፩)

ድልት -(ድንት) ስመ ፊደል ራብዕ የግእዝ አራተኛ ፊደል ፍችውን በዳሌጥና በድንት ተመልከት።

ድልወት -(ታት) መመዘን -(ጥመ) መመዘን መዛኝና ተመዛኝ መኾን፤ አመዛዘን ምዘና ሚዛን፤ ልክ መጠን -(ዘፍ፳፬ -፳፪ ዘፀ፴ -፴፬። መሳ፰ -፳፮) ወድልወቱ ለኵሉ ብርት ወኀጺን ዘላዕሌሁ ምሳ ምእት ሰቅሎን -(፩ነገ -፲፯ -፭። ፪ነገ -፲፬ -፳፮)

-አገባብ ርትዕ፤ -(እውነት፤ የተገባ የሚገባ። በጽድቅ ተኰነኑ ዘከመ ድልወተ እከዮሙ እንዘ ድልወት ሊተ ድኀንከኒ ድልወት ኣንቃዕዱ በብ ድልወታት። ነበብከ ድልወተ -(ጥበ፲፱ -፲፪ ዲድ -፯። - - -፪። ቄር -ጰላ)

()           ድልው [1]-(ዋን ዋት ሉት) የተመዘነ የተካከለ ልከኛ ነሰ በዛ የማይባል ቃሎሙ -ጠቢባን ድልው በመዳልው ድልወ ዕርየት -(ሢራ፳፩ -፲፭ ልክ -)

[2]-() ድልው፤ የተገባ የተዘጋጀ የተሰናዳ ግጁ። ዘድልው ክብር። ድልው መንበርከ በዓልየ ድልው ድልዋኒክሙ ሀልዉ እልኩ እለ ድልዋት ወድሉት ይእቲ -(ሢራ፵፱ -፲፪ መዝ -፺፪ ማቴ፳፪ -፰። ፳፬ -፵፬። ፳፭ - ራእ፳፩ -) ድልኽ ማለት ከዚህ ወጥቷል

ድል -(ዐረ ዱምሉጅ) የእጅ የጣት ጌጥ ጥምዝ የወርቅ አንባር ኀቲም ቀለበት ወይም ባለዕንቍ ፈርጥ። ወከመ ድልጕማ ውስተ እደ የማን። ሕልቀትየ ዘአጽባዕትየ ወድልጕማየ፤ አንባር -(ሢራ፳፩ -፳፩ ኩፋ -፵፩) ከመ ባዝግና ወርቅ ውስተ ክሣድ ወከመ ድልጕማ ዘውስተ አጻብዕ -(ፈላስ -ገ፲፰ ደልገን ማለት ከዚህ ይሰማማል

ድመት [1]-መደመም መደነቅ ደናነቅ፤ ድንቂያ ኸት ድምታ ድም ማለት።

[2]-(ታት። ዐረ -ዲመት ጽር -ኤሉሪ) ቁሙ፤ ብስ ብሴ ውር ውሮ የሚባል ታናሽ የቤት አውሬ ያይጦች ደመኛ ግርማው የሚደም የሚያስደምም ያንበሳ ወገን ዐዳኝ ወሮ በላ። የዱር የባሕር ድመት ጸጕረ ድመት አናብስት ኮኑ ከመ ድመታት ወረውዎ ውስተ ማዕበለ ባሕር ከመ ይብልዕዎ ዓሣት ወዐናብርት ድመታት -( - ስንክ -መጋ፳፫ ጥቅ፯)

[3]-በቁሙደሚም ደመመ

ድሙስ -ጥቍር ጠቋራ ጽዕዳዌና ቅላት የሌለው በድሙስ ሰማይ በብሩህ ሰማይ -(ቄድር)

ድሙር -(ራን ራት ምርት) ቁሙ፤ የተደመረ ድምር፤  ጭምር ቅልቅል ኀጺን ድሙር ምስለ ሕኵት ኢኮኑ ድሙራነ ዝንቱ ምስለ ዝንቱ ባሕር ድምርት በእሳት -(ዳን፪ -፵፩ -፵፫። ራእ፲፭ -)

-የቍጥር ስም፤ አንድነት ጅምላ ወኮነ ኵሉ ድሙር ወድሙር ኵሉ ንዋዮሙ -(ነሐ፯ -፷፮። ግብ፪ -፵፬)

ድሙቅ -የደመቀ ደማቅ፤ ቀለሙ ዕዳያቱ ጽዕዳዌው ቅላቱ ሩቅ የሚቃይ። ወይትኀጣእ ቅድው ወድሙቅ አልባስ -(ፍካሬ እየስ)

ድሙን -(ናን ናት ምንት) የዳመነ፤ የጨለመ የጠቈረ ጥቍር ያቅየሐይሕ ሰማይ ድሙነ። ኮነ ገጹ ድሙነ ወሕብሩ ጽምሑየ -(ማቴ፲፮ -፫። ፊልክ -፻፰፬)

ድሙፅ -(ፃን ፃት ምፅት) የተሰማ የተደመጠ፤ ጧኺ ድምጣም -(ስንክ -ሐም፲፭)

ድማኅ -(ኃት) ራስ ጭንቅላት፤ የራስ ቅል ቸብቸቦ ካንገት በላይ ያለው። -(ግጥም) ዋርሳ አታግቡ ብሎ የገዘተ ማነው፤ ዮሐንስ እንደኾን ካንገቱ በላይ ነው -(መዝ -፯። ኩፋ -፳፪) በከመ ሰካሪ እምሐሩረ ወይን እንተ ተዐርግ ዲበ ድማኁ ይሬኢ ወኢየአምራ -(ፊልክ -፻፮)

-ዐናት ማኽል ራስ፤ የናላ ርግብግቢት ሜዳው ስጡሑ በስተላይ ያለው፤ ለተራራና ለዛፍም ይኾናል -(ሔኖ፮ -፮። ፲፰ -) ሥዕርተ ድማኅ፤ ንጮ ብርንጎ ክብሶ በማኽል ራስ ላይ የሚበቅል የሚከበስ -(ሕዝ - -፫። ዳን፲፫ -፴፮። ኢዮ፲፮ -፲፪)

ድማም -ድንቅ፤ ድንቂያ ዝምታ፤ ንክሮ ወተደመ ይሥሐቅ ቢየ ድማመ -(ኩፋ -፳፮)

ድማሬ -(ርያት) መደመር፤ -(ጥደ) መደመር አደማመር ድመራ ደመራ። ኅብረት አንድነት ተዋሕዶ ሀበነ ለኵልን ድማሬ። እን ኢይዘሮ ምድማሬሁ። ድማሬ ዘህላዌ ጽድቅ -(ኪዳ። ቅዳ -ዮሐ ቄር)

-1 መቀላቀል፤(ጥቀ) መቀላቀል አቀላቀል ቅልቀላ ድብለቃ፤ ቅልቅልነት ኢድማሬ ህላውያት፤ የባሕርያት አለመቀላቀል -(ሃይ -አበ)

ድማኔ -መደመን፤ አደማመን፤ ድመና ረት ጨለማ። ሰማይ ንጽሕት ይእቲ ወኢይረክባ ርስሐት ወኢድማኔ -(አፈ -ተ፲፮)

ድምሱስ -(ሳን ሳት ስስት) የጠፋ የተደመሰሰ ድምስስ ያለ ይን የሌለው።

ድምሳሴ -ማጥፋት መደምሰስ ጥፋት መደምሰስ አጠፋፍ ጥፋት ደመ ክርስቶስ ዘይትከዐው ለድምሳሴ ጣው ዓለም ድምሳሴ እደመስሶሙ ድምሳሴ ኃጥኣን ሰብእ ማየ ድምሳሴ -(መጽ -ምስ ዘፀ፲፯ -፲፬ ጴጥ - -)

ድምቀት -መድመቅ አደማመቅ፤ የማሕሌት የዘፈን። ምስጢሩ ልብስን አይለቅም ሲዘምሩና ሲዘፍኑ ለብሰው አጊጠው ነውና

ድምድማ [1]:-ተናደሚኅ ደምኀ።

[2]-ድምድማ፤ -(ማት) ጕተና ጐፈሬ የራስ ጠጕ -(ማሕ፭ - ፲፩። ፩ቆሮ -፲፩ -፲፬) ቈናዝዕ ወድምድማተ ርእስ -(አዋል) መጨረሻ መደምደሚያ፤ ክዳን ክፍክፋት፤ ቍንጮ ልላት ድምድማት እንዲሉ -(ዐማርኛ)

ድምፅ -(ፃት) ቁሙ፤ ድምጥ ጓታ ጩኸት አጧጯኽ የጩኸት ቃል ድምፅ ተሰሚው፤ ቃል ፍሬው። ሰማዕኩ ድምፀ ክነፊሆሙ ከመ ድምፀ ማይ ብዙኅ። ድምፀ አራዊት። ድምፀ ጸሎት ሐዋዝ ድምፀ ንባቦሙ። ድምፃት መደንግፃት -(ሕዝ፩ -፳፬ ስንክ -ሚያ፲፯ ጥቅ5 ጥበ፩ -፱። ፊልክ -፻፲፮)

ድስቅን -(ጽር ዲስኮስ) ታናሽ ክብ ጻሕል የቍርባን መሥሪያ መቀደሻ። ያቅርብ ቢድስቅን ወኢያቅርብ በጽዋዕ ዲያቆኑ ለቄስ ማለት ነው -(ቀኖ -ኒቅ፲፫)

ድስቡጣ -(ጽር ዴስፖታ ) ሊቅ እግዚእ፤ ደግ ገዥ። ድስቡጣ ናይናን። ምንስቲቲሙ ድስቡጣ -(ግብ -ሕማ)

ድሩስ -(ሳን ሳት ርስት) የደረሰ የተደረሰ፤ ድርስ ፍጹም።

ድሩክ -(ካን ርክት) የጠና ጥኑ ብርቱ ንካራ ደረቅ ሸካራ ክፋ ጨካኝ። -(የተንደረከከ ብስል ቀይ) ማእሰር ድሩክ ልሳን ድሩክ። ቃል ድሩክ። ወዔሳውሰ ውእቱ ብእሲ ድሩክ ወሐቃላዊ ወጸጓር ወኵሉ ብሩ ድሩክ። ድርክት ከመ ሲኦል ቅንአት -(ስንክ -ጥቅ፳፩ ኅዳ፭ ኩፋ -፲፱ ማሕ፰ -)

ድሩግ [1]-(ጋን ጋት ርግት) የተደረገ ድርግ ድርጁ ዝግጁ፤ ቅንጁ።

[2]-የተዳረገ ገንዘብ ሰው ንዋየ ድሩግ ዋይ ድሩግ -( -)

ድሪቆን ድርቲቆን -(ዕብ ርቂዕ) የሰማይ ስም ማይ ኤረር፤ ኛነቱ ለጠፈር ው፤ ለላይኞቹ ግን ለሰባቱ አንደኛ ይባላል -(አዋል ቀሌ)

ድራሞ -ደስክ የንቅልፍ ጋኔን የሚጫን የሚደብት ይልቁንም በጸሎትና በጉባኤ ጊዜ የመነኮሳት ደረሞኛ ጋኔነ ዝሙት፤ የሚያሳክክ የሚያስፎክት ዕከካም ያስሕኮ ለሥጋ ወይሬስዮ ለብእሲ ይዝሐቅ ሥጋሁ ዘእንበለ ፅርዖ -(አረጋ -ድ፯)

ድራር -(ራት) እራት የማታ ምግብ ምሳሕ አው ድራር መሂ በድራር ወእመሂ በምሳሕ ዘአሕጸጸ ድራሮ ይበይት ጥዑየ ሥጋሁ ይጸውም ድራረ -(ሉቃ፲፬ -፲፪። ኪዳ ፈላስ ስንክ መስ፴)

-ድሮ ዋዜማ፤ ቅበላ ጾመ ድራረ ልደት ወጾመ ድራረ ጥምቀት። ማኅትው ዘድራረ ጾም -( - -፲፭ ድጓ) ዲቃላውን ደርደረ አንደርደረ ብሎ፤ ደረደረ አንደረደረ ተንደረደረ ማለት ከዚህ ይወጣል -(ዐማርኛ)

ድርህማት ደራህም -ድሪሞች መጠነ ዐሠርቱ ድርህማት ደራህም ዘሕልያን -( - -፴፱። - -፳፭ -)

ድርህም -(ጽር ድራኽሚ ዐረ ዲርሀም) የገንዘብ ስም፤ ድሪም እንደ ዲናር ያለ የፋርስ ገንዘብ። ዲናርና ድርህም ትክክል ናቸው -(ስንክ -የካ፭ ግብ፲፱ -፲፱። ቀሌ)

ድርሙስ -(ጽር ድሪሙ) ዱር ደን ሐቅል ብዙ ዛፍና ዕንጨት ያለበት። ሐነጸ ቤተ ድርሙስ -(፫ነገ - -) ድርሙስ ባለው ደግሞ በገዳም ይላል

ድርማንቅ -(ቃት) የውስጥ የገላ ልብስ ሱሪ ቀሚስ ልብ አልባ ጥብቆ ዐጭር ምጣ ወይም ረዥም ጠባብ የወንድ የሴት። ድርማንቅ ዘዐጌ ድርማንቃቲሆሙ -(ሕዝ፵፬ -፲፰ ዳን፫ -፳፩ ዘፀ፳፰ -)

-የመግነዝ ስም የቄስ የመነኵሴ ግንዛት አስተሳሰሩ እንዳስኬማ ያለ ትእምርተ መስቀል ያለበት ድርማንቅ ቃል ነው ድርማ ንቅ ወይም ድር ማንቅ ድርማ ንቅ ሲኾን ድርማ ድራሞ ከነቅሀ የወጣ ይመስላ የሚለበስ ሌት ተቀን ነውና። ድር ማንቅ ሲኾን ግን አለጥርጥር ድር ከድርዕ ማንቅ ከዐነቀ መጥቷል ያሰኛል የመግነዙም ስም በቁሙ ድርን ማሰሪያን ያሳያል። -(ተረት) ድር ቢያብር አንበሳ ያስር

ድርሰት -(ታት) መድረስ መደረስ አደራረስ ደረሳ ድርሻ በቁሙ የምስጋና ቃል ቅኔ መልከ ሰላምታ ግጥም። ነባቤ  ዝንቱ ድርሰት ርብዓ ወክልኤ። ድርሰታተ ማሕሌት -(ደራሲ ርጋ)

ድርሳን -(ናት) በቁሙ የተደረሰ የተጣፈ ቃል ነገር ንባብ ረዥም ስብከት ትርጓሜ አፈታት፤ ጕሥዐተ ልብ -(ዲዝኩር) መዝሙር ምስጢሩ የሚያጠግብ ቃሉ የሚያረካ፤ አነጋገሩ የተሳካ፤ ጣዕመ ቃሉና ኀይለ ቃሉ ደስ የሚያሰኝ ልብ የሚነካ። ድርሳን በእንተ ሰንበት ዘደረሰ ርቱዐ ሃይማኖት። ድርሳን ዘአባ ያዕቆብ ዘስሩግ ዘደረሰ በእንተ እለ ኖሙ ካህናት ወዲያቆናት ኤፍሬም ሶርያዊ ደረሰ ድርሳናተ ብዙኃተ  ፈድፋደ -(አዋል። ግንዘ ንክ -ሐም፲፭) ድርሳነ ማርያም ድርሳነ ሚካኤል ቢል ወግ ታሪክ ዜና ማለት ነው። ምስጢሩ ነገር ከማለት ይገባል።

ድርስ -(ዐማርኛ) ልክ እውነት ርግጥ ድርሱን አገኘኹት እንዲሉ። የምልክት ስም የዜማ ምልክት ፍጹም ማለት ነው

ድርስ ድራይ -(ጽር ድሪስ ድሪይ ድሪዮስ) የዛፍ ስም  በሉጥ። ባለብሉዮች ግን ወይራ ይሉታል -(ኩፋ -፲፫ ፲፬ ፴፩) ለአብርሃም ቀዳሚ ዘአስተርአይኮ ክርስቶስ፤ ቀትረ ታሐተ ዕፀ ድርስ ተሰቀልከ ከመ እቡስ -(ደራሲ)

ድርቲቆን -፪ኛ ሰማይድሪቆን

ድርንቅ -(ዕብ ስላው) የባሕር ቆቅ ድርጭት ፍርፍርት በወንዝ ዳር በባሕር ጠረፍ የሚኖር፤ የሠባ ያፈረጠመ ንገቱ ክንፋ የገጠመ ድርንቅ ማለት ቃሉ ከዶቄት ስፍር ወጥቷል ምቆ ደርንቆ እንዲሉ። ያንገቱን ማጠር የሥጋውን መጥበቅ ያሳያል። ወሶበ ሰአሉ መብልዐ ፍግዓ ወተድላ ዐርገ እምውስተ ባሕር ብዙኅ ድርንቅ -(ጥበ፲፱ -፲፪) ፍርፍርትን እይ

 

ድርዕ -( አድራዕ ዐረ ዲርዕ) ጥሩር የብረት ቀሚስ ሴደርያ በሰልፍ ጊዜ የሚለበስ። ወልታ ወድርዐ እንግድዓ። ዘቦ ድርዕ ይለብስ ድርዐ ጽድቅ አልባሰ ድርዖሙ። ድራዕ ወአቅስስት -(ሔኖ፰ -፩። ነሐ፬ -፲፮ ጥበ፭ -፲፱ ነገ - -፬። ዜና -፳፮ -፲፰) በምስጢር፤ ጥብዐት ትዕግሥት ይኾናል ድርዐ እንግድዓ ወበጽንዐ ሃይማኖት ወረሰ መን ሰማ -(ድጓ)

ድርኵኵት -(ታት) የመዝጊያ ቍላ ወንዴ፤ በመድረኩ ላይ የሚቆም የሚተከል ወይም ሴቴው የመድረኩ ፍልፍል መቋሚያውና መተከያው ከመ ማዕጾ እንተ ዐውድ ውስተ ድርኵኵታ -(ምሳ፳፮ -፲፬ ዘካ፲፪ -፪። ነገ - -፴፩)

ድርክሜ -(ጽር ድራኽሚ ዕብ ቤቃዕ) ድሪም ድርህም፤ የዲድርክም አላድ ድርክሜ አሐቲ ድርክሜኑ ለለ ዕለት -(ዘፀ፴፱ -፫። ቢ፭ -፲፬)

ድርያሚን ድብርያሚን -(ዕብ ዲብሬይ ሀያሚም) የብሉይ መጽሐፍ ስም እንደ ነገሥት ያለ ዜና መዋዕል ማለት ነው ሕጹጻንን እይ፤ ከዚህ ጋራ አንድ ነው -(አቡሻ)

ድርድር -በቁሙ ዐማርኛደሪር ደረ ደርደረ

ድርገት -(ታት) [1]-ማድረግ፤ መደረግ፤ አድርጎት አደራረግ፤ ድርጊያ ድርጊት። አንድነት አንድ መኾን ማኅበር ሸንጎ ጉባኤ ከመ ያውርሶ መንግሥተ ወድርገተ ምስለ እለ ይነሥኡ ክሊለ ድርገት ምስለ መላእክት ድርገተ አኀ ድርገቶሙ ለቅዱሳን። ኀፍረት ሰቈቃወ ብካይ ማእከለ ድርገተ ማሕሌት -(ቀሌ ቄር ፊልክ -፵፬። ተረ -ቄር መጽ -ምስ)

[2]-(ታት ዐረ ደረጀት ሱር ዳርጋ) ደረጃ ዕርከን ማዕርግ የቤት የሹመት። ዘይሴብሕዎ ድርገታተ ሐራ ወኵሉ  ድርገታት -(ድጓ ቅዳ -ሕር)

ድርጋሕ -ድሪቶ ደባደቦ ሦስቲዮና አራቲዮ ኹኖ የተሰፋ የተጠቃቀመ ቆብ አሮጌ ጋቢ ዐዲስ ልብስ ዐርበ ወጥ ገና ያልተሰፋ። አልቦ ዘይጠቅብ ምደ ድርጋሐ ልብስ ውስተ ሥጠተ ልብስ ብሉይ -(ማቴ፱ -፲፮ ማር፪ -፳፩ ሉቃ፭ -፴፮)

ድርጎ -በቁሙ ርሻ ዳረጎት ተዳራጊ የሚቀበለው በእንተ ድርጎ ዘይዳረግዎ ትከውን ማነ ተዳርጎ ዘእንበለ በሥምረተ ዳራጊ ወተዳራጊ -( - -፴፫ -)

»ድቀት -(ታት) መውደቅ መሰናከል፤ አወዳደቅ ውድቂያ መከራ ሞት ኀጢአት እለ ይትፌሥሑ በድቀቱ ለጻድቅ ድቀት ትጸንሖ ይከውኑ ለድቀት ኅሱር ታጎሥኦ ምነ ድቀቱ ኢይማስን። እስመ መተረ ግብራተ ድቀታት እለ ያርሕቅዎ እምእግዚ -(ሢራ፳፯ -፳፱ ኢዮ፲፭ -፳፫ ጥበ፬ -፲፱ ዲድ -፮። ፊልክ -) በድቀት ፈንታ ውድቀት ይላል ፍችው አንድ ነው በእንተ ውድቀቱ ለሳዶቅ ካህን -(ክብ -ነገ) ፪ኛም በፃእፃእ ፈንታ ድቀት ይላል። ለእመ ድቀት ይወርስ ባሁ -(ፊልክ)

ድቁስ -(ሳን ሳት ቅስት) ያንቀላፋ፤ እንቅልፍ የወስደው የደበተው ዘይነግሮ ድቁስ ድቁስ ወኢንዉም -(ሢራ፳፪ -፰። መጽ -ምስ) በቁሙ ድቍስ ብትን ድልኽ -(ዐማርኛ)

ድቁቅ -(ቃን ቃት ቅቅት) የደቀቀ ደቃቅ የተወገጠ የተቀጠቀጠ፤ የተደቈሰ የተፈጨ ታናናሽ ቅንጣት ዕጣን ዘድቁቅ ተሐርጽ ድቁቀ ወይከውኑ ድቁቀ አግልዕተ -(ዘሌ፲፮ -፲፪። ዘፀ፴ -፴፮። ኢሳ፴ -፲፬) ድቁቅ ቃሉ የደከመ የሰለለ ቀጭን -(ስንክ -ነሐ፲፭)

ድቍንዱቅ -ምድቃሕ ፋስ ምሣር መጥረቢያ። መፍጽሕ ወድቍንዱቅ -(፫ነገ - -)

ድቃል -( ደቃልው። ዴቄል ሱር ዴቅላ ዐረ ደቀል ተምር) ዲቃላ የዝሙት ልጅ ከሚመሳሰል ከማይመሳሰል የተወለደ። በቅልን ተመልከት

ድቃስ -ክቡድ እንቅልፍ እንደ ሞት ያለ ስልምታ ሽልብታእንጕልቻ ወፈነወ እግ ድቃለ ዕለ ዳም -(ዘፍ፪ -፳፩ መዝ -፻፴፩። ምሳ፮ -፬። ሉቃ፱ -፴፪)

ድቡስ ድንቡስ -ድንቡስ -(ሳት። ዐረ ደቡስ ደባቢስ) ራሳም ችነካር የበረት በሎታ ወይም ዘንግ ወፍራም ሽቦ ቋራም ስለታም ዘዘ ይዝብጥዎ በድቡሳት ዘኀጺን -(ስንክ -ታኅ፰ ጥር፩ ሐም፰ ሠኔ፳፯) ቀሠፍዎ በድንቡሳት በሊኃት እስከ ተሰብሩ ገበዋቲሁ ወቦኡ ውስተ ከርሡ ድንቡስ ክቡድ ድንቡሳት ዘብርት፤ -(ስንክ -ሚያ፲፪ ፳፮)

ድቡብ -(ባን ባት ብብት) የተደበበ የተዘረጋ ዝርግ። ደባባ መዳብማ

ድቡተ - ብሎ በቀስታ በሹልክታ ይታይ ሳይሰማ። ዐርገ ድቡተ እንተ ካልዕ ገጽ። ወፅአ ድቡተ። ወሶበ ስእነ ሠጊረ ድቡተ ሖረ -(ገድ -ተክ። ድጓ)

ድቡት -ሽመቃ፤ ቀስታ ዝግታ ድበታ አደባበት። ርቱዕ ድቡት ንገበሮ ለዝ። ከመ ዘበድቡት ወበቀሊል ያሐምመ -(ግብ፲፱ -፴፮። ሄርማ ፪ጢሞ - -)

-() ድቡትሽመቃ ቀስታደቢው ደበወ

ድባብ -በቁሙ፤ ጃን ጥላ፤ የሚደበብ የሚዘረጋ የሚታጠፍ የሚጠቀለል ጌጥና ሽልማት መረሻ ያለው ወይም ሌጣ ጸዋሬ ድባብ -(ታሪ -)

()          ድባን -(ዐረ) ዝንብ፤ ደበነ አደበነ ድብን አለ ማለት ከዚህ ወጥቷል

ድቤ -(ዐማርኛ) ፈር መሬት፤ ትቢያ ቧራ። ደባ ደቦ ደባይ ደባያት ማለት የዚህ ዘር ነው

ድብ [1]-በቁሙደቢው ደበወ

[2]-ድብ፤ -(ባት ዕብ ዶብ ሱር ዴባ ዐረ ዱብ ዱበት) ቁሙ አውሬ የዥብ ወገን፤ የሚያደባና የሚያሸምቅ፤ አድብቶ የሚይዝ የሚነጥቅ፤ ጥላው የሚያፈዝ የሚደብት ጠጕራም መድማ፤ -(ወና ) ድብ ኀራስ። ድብ ርኁብ ድብ እንተ ትንዑ ቤተ አናብስት ወድባት ከመ ትፈኑ ድባተ ብዙኀ -(፪ነገ -፲፯ -፰። ሆሴ፲፫ -፰። ስቈ፫ - ስንክ -መስ፳፯ ጥበ፲፩ -፲፰)

- ዋክብት እነሰባቶ፤ መንፈቀ ሰማይ ወዲያ ወደ ሜን ወገን ጅብ ብለው ታፍገውና ተመስገው ድርገት ኹነው የሚታዩ፤ ባለመርከቦች የሚመሩባቸው ኖትያዊ ይኔጽር ኀበ ዋክብት አመ የሐውር ውስተ ባሕር ዘከመ ይመርሓ ወያይዳ ለሐመሩ -(ማር -ይሥ፳፰)

ድብል -(ትግሬ) ልብሰ ዔሊ፤ የደንጊያና የቀንድ ያጥንት ይነት ራራ ጠንካራ ጥኑ ባድ ሸክም ጭነት ውድን ወዴላ በቁሙ ድበላ ያበባ እኽል ሲከኩት ፪ነት ያለው -(ዐማርኛ)

ድብቱር -የተዘረጋ የተተከለ። ኀበ ድብቱር ደባትረ እሳት -(መጽ -ምስ)

ድብታሬ -መተከል መዘርጋት፤ ድብትርና ደብተርነት።

ድብዕንኵል -(ላት) ያንበሳ ወጥመድ እንደ ቀፎ ያለ -(ሕዝ፲፱ ገድ -ተክ)

ድኑስ -(ሳን ሳት ንስት) ያደፈ የረከስ እድፋም። ኢበላዕኩ አነ ሙራ ርኩሰ ወድኑስ። ንሕነሰ ንሬሲ ኵሎ ርኩሰ ወድኑሰ ዘማዊ ወድኑስ ኅሊ ድንስት -( - -፳፫ -ድ፳፮ ፴፫ ፊልክ -፻፷፩)

ድኑን -(ናን ናት ንንት) የደነነ ያደነነ፤ የተጐነበሰ ጕንብስ ጐንባሳ ተርካሳ። ይጣን በኀፍረት ወበኀሳር ድኑነ ወርእየ ኵሎ ይላተ ሰማይ ድኑናነ በዐውደ መስቀል ቅዱስ -(ስንክ -የካ፬ መቅ -ወን)

ድናኔ -ድናኔ መጐንበስ አጐነባበስ፤ ጐንባሳነት፤ መቅለስለስ -(ገድ -አዳ) ውሥኦ ወድናኔ -(ማር -ይሥ፮ -)

ድንቀተ -(ግብተ) ድንገት ድንገት፤ ይታሰብ። ድንቀተ ብተ እንዘ ኢተአምር። በጽሑ ኀበ ሰራዊተ ዳራ እምቅድመ ጽባሕ ድንቀተ እለ ይነግሩ እምአፉሆሙ ድንቀተ ወኢቀደሙ ጽሒፈ -(ቀሌ። ዮሴፍ ተረ -ቄር)

ድንቀት [1]-ዝኒ ከማሁ፤ አደናንቅ ድንቂያ፤ ድንቅነት። ድንቅ ብርቅ፤ የሚያስደንቅ እምአይቴ አምጽአት ዛቲ ብእሲት ዘከመ ድንቀተ -(ገድ -ተክ)

[2]-(ድድቀት) ድንገት፤ ቆሎ ወዲያው ምስጢሩ ድንቂያን አይለቅም።

ድንቃዌ -መደንቈር፤ ድንቍርና ደንቈሮነት ጸወ እዝና ድንቃዌ -(መጽ -ምስ)

ድንቡስ -ችንካር ሽቦድቡስ

ድንባዝ -(ዛት ንባዝ ነበዘ) መጾር ምዝላል መሎጊያ ወፍራም ደጓሳ ደልዳላ፤ እንደ ዕርፍና እንዳልጋ ዘንግ እንደ ሸማኔ መጠቅለያ ያለ የወሰካ ዕንጨት የሳንሳ የሚይዙበት የታቦተ ጽዮን መሸከሚያ -(ዘፀ፳፭ -፲፫፲፭) የመሰንቆና የበገና የክራር ንጨት -(፪ዜና - -፲፩) ዘሩ ነበዘ ነው ሕንጻ ድሕንጻ እንደ ተባለ ባዝም ድንባዝ ተብሎ ወደዚህ መጥቷል፤ ባለቅኔዎች ግን ደንበዘ ደገፈ ብለው ይገሱና ድንባዝ ባላ ድጋፍ ወጋግራ ይላሉ

ድንብዕኵል -ያንበሳ ቀፎድብዕኵል።

ድንታር ዲንታሮ -የሱሪ መሽቀቅ ጥብጣብ። ማነቆ ሸምቀቆ -(ጥሬ ) ምስጢሩ ዘልፋዊ ማለት ነው። ወከመ ቅናት ዘይቀንት ዘልፈ -(መዝ -፻፰)

ድንት [1]-(ድልት) ስመ ፊደል ራብዕ ለዓለም ዘለዓለም። ድንት ያኑርኽ እንዲሉ እውነተኛ ድልት ነው እንጂ ድንት አይዶለም በን ተለውጧል ዳሌጥንና ድልትን እይ

[2]-ድንት፤ -(ታት) ድንች ነዋሪ የምድር ፍሬ ከተዘራበት የማይጠፋ የማይታጣ።

ድንክ -ቁሙ፤ ታናሽ ጭር ዐልጋ። ለሰውም ይኾናል።

ድንዙዝ -(ዛን ዛት ዝዝት) የፈዘዘ ፈዛዛ ደንዛዛ ደብዛዛ እንቅልፋም ነፍ ታካታ ደካማ ወሀቦሙ መንፈሰ ድንዙዘ -(ሮሜ፲፩ -፰። ብ፭ -፲፩ -፲፪) ትኩኑ ድንጉፃነ ወድንዙዛነ ድምዙዛነ ልብ። ፍካሬሁ ኢኮነ ቀሊለ ወፈድፋደሰ ለእለ ይሌብዉ ወኮኑ ድንኩዙዛነ ሰሚዕ -(ኪዳ። መቃ። ተረ -ር፳፩)

ድንዛዜ -መደንዘዝ መፍዘዝ፤ ፈዛዝነት ድንዛዜ ወሀኬት እምሰሚዕ ሀኬት ወድንዛዜ -(አፈ -ድ፲ -ቀሌ)

ድንገት -(ዐማርኛ) በቁሙ ድንቀትደኒቅ ደነቀ።

ድንጉል -(ላን ላት ግልት) የደነገለ የተደነገለ፤ ድንግል ጥብቅ የማያውቅ ቅድስት ወብፅዕት ወድንግልት ኢዮጰራቅስያ ነበርኪ ድንግልተ ደቂቅት ድንግልት -(ስንክ -መጋ፳፮ አርጋ -፬። ፊልክ -፶፰) ባማርኛ ግን ድንጉል የንብ ውሃ ቀጅ ያልተሰነጋ ፈረስ ማለት ነው። ከበገና አውታርም አንዱ ድንጉል ይባላል።

ድንጉግ -(ጋን ጋት ግግት) የተወሰነ የተደነገገ ውሱን ኢድንጉግ መለኮቱ በግብረተ ዓለም -(መጽ -ምስ)

ድንጉፅ -(ፃን ፃት ግፅት) የደነገጠ ድንጉጥ ፈሪ፤ ፍራት የያዘው ያፈዘዘው ሀሎኩ ድንጉፅየ ኀለ ድንጉፃኒሆሙ ህጉር ድንጉፃት በሪ ድንግፅተኪ -(ሱቱ -ዕዝ፩ ኤር፱ -፲። ኢሳ፲፬ -፴፩ ፵፯ -)

ድንጕዝ -(ዛት) የጭራ የጠጕር ሥራ፤ ንናት ያሠራሩ ዐይነት፤ የሥራው ስም ጕቾ ብርንጎ ቍንጥርጥር፤ እንደ ሣህለ ሥላሴ ጠጕር -(ግጥም መጥፎ ተነሳሒ ጠጠቱ ይሁዳን ጠጠት የመሰለ) የወንድሜ ራሱ ተናው አማረ እኔም ባልተሠራኹ ይሻለኝ ነበረ ድንጕዛት -( - -፶፩)

ድንጋሌ -መደንገል፤ ድንገላ ጥበቃ፤ ድንግልና። ድንጋሌ ሥጋ ይለ ድንጋሌሁ መሀሮሙ ደናግል ለእለ ያውስቡ ከመ ይዕቀቡ ድንጋሌሆሙ ብንተ ዐይን -(አፈ -ተ፳፰ ስንክ -መጋ፲፪ ቀሌ)

ድንጋጌ -ውሳኔ አወሳስን ውስና። ወሰን ደንበር ሸዋ ደንጊያ ባሕረ ውቅያኖስ ውሱን በድንጋጌሁ -(አርጋ -)

ድንጋግ -ዳርቻ ዳር፤ ወሰን ደንበር ወደብ ገደብ፤ አፋፍ ረፍ ኆጻ ዘድንጋገ ባሕር። ልቦ ድንጋግ ባሕረ ጥበቡ ወሜጠኒ ኀበ ድንጋገ ፈለግ። ድንጋገ ማይ -(ዘፍ፳፪ -፲፯ ቅዳ ኤጲ ሕዝ፵፯ -፮። ራ፳፬ -፲፬)

ድንጋፄ -በቁሙ መደንገጥ አደነጋገጥ ድንጋጤ ፍራት። ድንጋፄ የልብ የልቡና ፍራት ያንጎል የናላ ያመጽእ ድንጋፄ ዕለ ሕዛብ። ዐቢይ ድንጋፄ አኀዞሙ። ድንጋፄ ልብ -(ኤር፵፩ - ዳን፲ -፯። ናሖ፪ -)

-እንቅልፍ ራእይ አንክሮ ተደሞ ተመሥጦ ወድቀ ድንጋፄ ዕለ ብራም። መጽኦ ድንጋፄ ላዕሌሁ ወርእየ -(ኩፉ -፲፬። ግብ፲ -)

ድንግል -( ደናግል) በቁሙ፤ ጥሬ ቅጽል ፍችው እንደ ድንጉል ነው። ዮሐንስ ድንግል ሞንዮስ ድንግል። ኖብ ድንግል -(ድጓ ፊልክ ቅዳ) ቅጽልነቱና ስምነቱ የወንድ ብቻ ነበረ መጽሐፍ ግን በጣፎች ስሕተት ለወንድም ለሴትም ያደርገዋል። ብእሲት ድንግል ወለት ድንግል ወስማ ይእቲ ድንግል ማርያም -(ዘሌ፳፩ -፲፫ ዘዳ፳፪ -፳፫ ሉቃ፩ -፳፯) አንዳንድ ጊዜም ብእሲ ድንግል ወብእሲት ድንግልት ብሎ ይለያል -( - -፳፬ -)

ድንግልና -በቁሙ፤ ድንግልነት ድንግል መኾን፤ ክብርና ማኅተመ ሥጋ፤ ንጽሐ ሥጋ በእንተ ምታ ዘድንግልናሃ ርኰሰ ድገንልናሃ። ዮሐንስ ቅኑት በድንግልና። ዐቀበ ኖኅ ርእሶ በድንግልና ምስተ ምእተ ዓመተ -(ዮኤ፩ -፰። - - -፰። ድጓ ቀሌ)

ድንግልናዊ -ድንግላይነት ድንግላይ ባለድንግልና። በዓለ ልደት ድንግልናዊ ድንግልናዊት -(አቡሻ -፴፬ ርጋ -)

ድኢም ሞት -(ደአመ ይድእም ይድአም ዐረብ) መትከል ማቆም ማጥናት ማሸራሸት ማጥበቅ፤ እንዳይወድቅ እንዳይነቃነቅ ማድረግ መመሥረት፤ የግብር የነገር፤ ጥሬው በቀር አንቀጹ አይገኝም።

ድኩም -(ማን ማት ክምት) የደከመ ደካማ ኰሳሳ፤ ታናሽ ወራዳ፤ አሮጌ በሽተኛ ልም ልምሉም ርጥብ ለጋ ጨቅላ ድኩም ወጽኑስ መንግሥት ድኩም። ደትኪ አማሕፀነ ድክምት ሥጋ አዕይንቲሃ ድኩም። ልሳን ድክምት ድኩማን ደቂቅ -(ገላ፬ -፱። ሕዝ፲፯ -፲፬ ንክ -ግን፩ ኩፋ -፳፰ ምሳ፳፭ -፲፭ ዘፍ፴፫ -፲፫)

ድኵዕ -(ዕብ ዳክእ ዐፈር ትቢያ) ፍግ ፋንድያ በጠጥ ዐዛባ ይከይድዎሙ ከመ ድኵዕ ክዑ ድኵዐ ተግሣጽ ለሕፃን  ያሤንዮ በከመ ያሤንዮ ድኵዕ ለምድር -(ኤር፰ - ሉቃ፲፫ -፰። ፈላስ -ገ፰)

ድካም -(ማት) በቁሙ፤ ስንፍና ሀኬት ልፋት ጥረት አገልግሎት እንበለ ድካም ያእምር ድካሞ ድካመ ፍጥረቱ ወአእምሮቱ ሑጻጼ ወድካም። ዕሴተ ገድላቲሆሙ ወድካማቲሆሙ -(ስንክ -ጳግ፪ ኢዮ፴፯ -፮። ፊልክ -፻፸ዮሴፍ - - -)

ድክመት -መድከም፤ አደካከም፤ ድካም ደካምነት እምድኅረ ርሥኣኑ ወድክመቱ -(ፊልክ -)

ድክምና -ደካምነት ድካም እንዘ ሀለውክኒ አንቲ ድክምና መጽንዒ -(አዋል)

ድክቱም -(ማን ማት ትምት) የደኸየ የተጣለ፤ አባት እናቱ የሞቱበት። ድክትምት ይእቲ እምአቡሃ ወእማ ድክእቱማን -(ኦዋል - -፳፬ -)

ድክታሜ -ድክትምና ድኽነት አይቶ ጣነት፤ የሙት ልጅነት። በእንተ ዕጓለ ማውትናሆሙ ወድክትምናሆሙ -(ዮሴፍ - -፲፮)

ድዉይ -(ያን ያት ዱያን፤ ድውይት ዊት) በቁሙ፤ የተደወየ፤ ደዌ ያደረበት ታማሚ በሽተኛ። ትትሀከይ ሐውጾ ድዉይዘድዉይ ሥጋሁ በእን ድዉያን መጋቤ ዱያን ነፍስ ድውይት -(ሢራ፯ -፴፭። -፲፬ - -፳፩ ሲኖዶ)

ድዩን -(ናን ናት ይንት) የተዳኘ የተቀጣ፤ ፍርድ የለበሰ፤ የተፈረደበት።

ድያስ ድዮስ ድያ -(ጽር -ዲዎስ) ወፍራም ረዥም ጣዖት አምላክ ዐቢ ማለት ነው ዜዉስን እይ -(ግብ፲፬ -፲፪ -፲፫ ንክ -ኅዳ፲፬)

ድድ [1]-መሠረትወዲድ ወደ

[2]-»ድድ -(ዳት) በቁሙ፤ ማውድ መሠረት ምዕማድ ስክተት ድደ መሠረት። ዐምዳ ወድዳ ጽድቅ ይጸውር ድደ ወይነብር ጠፈረ -(ቆላ፩ -፳፫። ፩ጢ - -፲፭ ቅዳ)

ድድቅ -(ቃት) ድንገት፤ ድንገተኛ ያልታ አደጋ ሞት ጥፋት፤ ክፉ ነገር ኹሉ ሑዱ ድድቅ ይዳደቆሙ ክልኤሆሙ ተዳደቆ ድድቅ ለውእቱ ዋይ ምንዳቤያት ወድድቃት ምኵሉ ድድቅ ዘይጸንሖ ዕጓለ መሕያው። ምድድቅ ዘውስተ ማያት -(መክ፪ -፲፬ - -፵፩ -፭። መቃ -ገ፳፬ አርጋ - ደራሲ መዝ -)

ድጉም -(ማን ማት ግምት) የተደገመ፤ የተደጋገመ፤ ዕጥፍ ድርብ። የተደገመበት።

ድጉጽ -(ጻን ጻት ጽት) (ጻን ጻት ጽት) የተወጋ የተነካ የተደጐሰ -(ስንክ -ሠኔ፲፮)

ድጕዓ -(ሐማሴን) አልቃሽ አሟሽ ጣሚ። ቍዘማ የልቅሶ ዜማ ሙሾ ግጥም። ድጓን ተመልከት የዚህ ዘር ነው ድጕዓ ደግሞ ጐድዐ ጥቷል

ድጕጸት -መውጋት፤ መወጋት መነካት ንኪት ንበር ዕበጥ ድጕስ ድጐስት። እንበለ ሕማም ወእንበለ ድጕጸት -(መጽ -ምስ)

ድጋም -በቁሙ፤ መድገም መደገም ደጋገም ደገማ ድግሚያ ጸሎት

()          ድግ -በቁሙ፤ መቀነት፤ የሆድ ካሳ የወገብ ምሳ ወገብ የሚያጠና የሚደግፍ።

ድግዱግ -(ጋን ጋት ድግት) የከሳ ቀጠነ፤ ቀጭን ደግዳጋ ኰሳ ከሻዋ ድግዱግ ሥጋሆሙ ድግዱጋኒክሙ እስክንድር ድግዱግ መልክኡ ኮነ ብሶይ ድግዱገ -(ዘፍ፵፩ -፫። ዳን፩ - ዮሴፍ ስንክ ሐም፰)

ድግዳጌ -መክሳት መቅጠን፤ ከሳስ ክሳት ደግዳግነት -(ስንክ -የካ፳፭) መቃጥቅ መልበስ ለባበስ አስተጣጠቅ ትጥቅ ድግድጋት። ዱግ ዶግ ማለት ከዚህ ወጥቷል።

ድጓ [1]:-የዜማ መጽሐፍ፤ደጊግ ደገ ደግደገ

[2]-የዜማ መጽሐፍ ቅዱስ ያሬድ ባፄ ብረ መስቀል ዘመን ያዜመውና የገጠመው የኋላም ሰዎች በየጊዜው ጨምረውበታል፤ ፻፶ው መዝሙር የዳዊት ብቻ እንዳይዶለ ድጓም የያሬድ ብቻ አይዶለም። ድግዱግ ድግዱግ ጽሕፈት ጥፈቱ የከሳ የቀጠነ ደቂቅ ረቂቅ የኾነ አሸዋ እብቅ፤ ወይም ዜማ ቍዘማ፤ ግጥምና ዜማ ማለት ነው ድጕዓን ተመልከት በደጎ ዘይቤ ሲፈቱት ግን ደግ ደገኛ አሰኝቶ የመጽሐፉን መጠን ታላቅነቱን ያሳያል፤ በርቀቱ ላይ የመንፈቅ ስንክሳር ያኽላልና ፪ኛም ምእላድ መድበል እስትጉቡእ ብለው ይፈቱታል ቃሉ ገድል ከታምር ከአዋልድ ሳይቀር ብሉይ ከሐዲስ ሊቃውንት ተለቅሞ ተቀሥሞ የወጣ ድርሳን ኅዉሥ መዝሙር ሐዲስ ማለት ነው ኛም፤ በፊደል ቍጥር ፈቱት - - -፫፤ ድጓ - ይኾናል ስመ ኍልቈ ሳብዕ ፍጹም ውእቱ ይላልና -(ሃይ -አበ) ፍጹም ቍጥር ነው ድጓ ማለትም እንደ ስንክሳር ካመት እስካመት የተሠራ በየሱባዔው ሑድ እስከ ቀዳም ዕለት ዕለት ጧት ማታ የሚቀርብ ፍጹም ድርሰት መሧዕተ ስብሐት መኾኑን ያሳያል ዋዜማ ዘሠርክ ዕዝል ዘነግህ ስብሐተ ነግህ ይላልና። እየብቻውም ነጥሎ ቢፈቱት የክፍሉን ትርብዕት፤ እንደ ወንጌል ባ፬ ዐቢይ ክፍል ተከፍሎ ዮሐንስ አስተምሕሮ ፋሲካ መባሉን ምዕራፍን ዝማሬንና ዋሥዕትን ሦስቱን ያሳያል። ዳግመኛም ዋይ ዜማ ዘሰማዕኩ በሰማይ እመላእክት ይላልና ሰባትነትን ለዜማው ብቻ ቢሰጡት የስልቱን ትርብዕት ቁምን ዝማሜን መረግድን ጽፈትን ያሳያል እሊህ አራቱ የኪሩቤል አምሳል ናቸውና። ቁም ከመ ኪደተ ብእሲ፤ ዝማሜ ከመ ኪደተ አንበሳ መረግድ ከመ ኪደተ ላሕም፤ ጽፍዐት ከመ ኪደተ ንስር፤ወእሱ ይትሜሰሉ በአርባዕቱ እንስሳ -(ገድለ አብርሀ ወአጽብሐ) የዜማውን ትሥልስት ዜማው ግእዝና ዕዝል አራራይ መኾኑን ያሳያል ዜማ ጠቅላይ ስም ነው ያንድነት ስሙ የሦስትነት ምልክቱ ግን የኋላ ሰዎች ያበጁት ነው የያሬድ አይዶለም ወበመዋዕሊሁ ለዝንቱ ንጉሥ ገላውዴዎስ ተንሥኡ ዛዥ ጌራ ወአዛዥ ራጉኤል ካህናት ማእምራነ ዜማ ወወጠኑ ውፅኦ ምልክት ዘድጓ -(ታረ -ነገ) ከዚህ የቀረውን የድጓን ዘይቤ ምስጢርና አፈታት ድጓ መምህራን ይጠይቋል

ድፉር -(ራን ራት ፍርት) የተደፈረ የተናቀ የተጠቃ ጥቁ

ድፉን -(ናን ናት ፍንት) የተደፈነ የተቀበረ፤ ስውር ድብቅ -(ኢያ፯ -፳፩ -፳፪) ያልተቈረሰ ያልተከፈተ፤ ድፍን ምሉ ፍጹም፤ እንጀራ ቅል፤ የመሰለው ኹሉ። ለሀገርና ለሕዝብም ይኾናል፤ ድፍን ዐማራ ድፍን ትግሬ፤ መላው ጠቅላላው፤ ሳይቀር .

ድፍረት -በቁሙ፤ መድፈር መደፈር አደፋፈር፤ የትቢትና የጭካኔ ሥራ ዝንቱ ይከውን ድፍረተ ወተኀብሎ ያሴስል ድፍረተ ዝኁራን ይትናገሮ ለንጉሥ በድፍረት ዘእንበለ ፍርሀት ድፍረትክሙ ለእመ ቀረብክሙ ነሢአ ሥጋሁ በድፍረት ወድፍረት ውስተ ሀርብዶ -(አፋ -ተ፭ ቈስጠ -፶፩። ስንክ -ሠኔ፲፩ ቅዳ አፈ -ወር ማር -ይሥ፳፰ -)

ድፍነት -መድፈን፤ መደፈን አደፋፈን አቀባበር ድፍነተ ምዉት ውስተ ምድር ከመ ዘሪዐ ዘርዕ ውስቴታ ምቅድመ ድፍነተ ምዉታን -(ግንዘ)

ድፍዕ -ድፋት አደፋፍ፤ ድፎ

ድፍድፍ -ጭቃ፤ የጠላ ቡሖ ተሰብረ ገንዕ ወኢተክዕወ ድፍድፍ -(ገድ -ተክ)

ዶርከኖ -(ዕብ አርጋማን) ኀምራዊ ቀይ ሕብር ደባባ የበሰለ ፍሬ ወይም የጥቍር ወይን ደም የሚመስል። በርሱ የታለለ  ልብስ ፈትል።  መጻሕፍ ግን በያክንት ፈንታ ደርከኖ ይላሉ፤ መምህራንም ሰማያይ ይሉታል -(ራእ፱ -፲፰)

ዶሐን -(ዕብ ወሱርዐረ ዱኅን) ስመ እክል፤ አንድ ይነት እኽል፤ አገዳው ላንፋው የማሽላ ዐጫጭር ቀጫጭን ፍሬው የዳጕሳ ይነት -(ሕዝ፬ -)

ዶር [1]-(ዐረ ዱር ዶረ ጠራ በራ) ጥሩ ወርቅ ዕንቍ ፈርጥ በወርቅ ኅርወት የሚሰካ ወማእከሌሆሙ ታቦተ ዶር ዘስርጉት በሡራኄ ጸዳል ታቦት ዘዶር -(መጽ -ምስ ቅዳ -ሕር)

[2]-(ዕብራ) ትውልድ፤ ዘመን፤ የትውልድን ፍች ተመልከት። በዶሮሙ -(ዘፀ፴ -) በዐረብ ግን ዶር ተራ ዱራ ዑደት ይኾናል።

[3]-ጥሩ ወርቅደዊር ዶረ ደወረ

ዶርሆ -( ደዋርህ) ዶሮ፤ ብዙ የሚወልድ የሚዋለድ ለማዳ የቤት ወፍ ምስጢሩ መርባት ነው፤ ወንድና ሴት ያስተባበራል። በድምፀ ክነፊሆሡ ሱራፌል ይነቁ ዶርሆ ዶርሆ ተባዕት ዶርሆ እን ታስተጋብእ ዕጐሊሃ ታሕተ ክነፊሃ መጋዝአ ደዋርህ ክልኤተ እልፈ ደዋርሀ -(ቀሌ። ምሳ፳፬ -፷፮ ማቴ፳፫ -፴፯። ፫ነገ - -፳፫። ገድ -ተክ)

-በቁሙ ዶሮዶር ደወር

ዶርቃስ -(ጽር ዶርካስ) ፌቆ፤ ወይጦ ልንና ጣቢቃን እይ፤ ዚህ ጋራ አንድ ነው ባለሐዲሶች ግን ድሪቶ ጁሕ ጀባ ይሉታል -(ግብ፬ -፴፮ -፴፱)

ርገ ባንድነት አንድ ኹኖ ዐብ ደርገ ይፌውስ ዐጠነ ደርገ ምስሌሆሙ። ከመ ታዕርፍ ፍሶሙ ወይኵኑ ደርገ ምስለ ሊቃናት ሰማያውያን (ቄር ገድ ተክ። ግንዘ)

ዶታይም - ሀገር፤ የኢይዝራኤል ቅርብ አጠገብ -(ዘፍ፴፯ -፲፯)

ዶዲ -የሰው ስም፤ ወዳጄ ዘመዴ ማለት ነው -(፪ነገ -፳፫ -፳፬) አንዳንድ መጣፍ ግን ዱድ ዶዳኢ ይላል ስሕተት ነው። ዱድ ታላቅ ድስት ቅርጫት፤ ዱዳኢም የሽቱ ቅጠል ነው ዕንጐትን ተመልከት።

ዶድ -(ዕብራ። ሱር ዶዳ) አጐት፤ ያባት የናት ወንድም ያክሥት ባል። ወዳጅ ዘመድ ባልንጀራ እኩያ አምሳያ ዐብሮ አደግ ወንድም አከል

ዶፎኒ -(ሱር -ዱፍና) የሬሳ ሣጥን አስክሬ ዶፎ ጸበተ -(ስንክ -መጋ፰)

 

~ ጀ ~

 

ጀውዛ -ስመ ኮከብ፤ገውዛ

ጀይብ -(ዐረብ) የቀሚስ ሕፅን ሰላጤ በሰላጤው ላይ የሚሰፋ ኪስ ከረጢት፤ ውስጠ ክፍት ኹኖ ማረሚያ ገንዘብ የሚከት -( - -፴፩ -) ምስጢሩ የዲብና የድብኝት ነው።


No comments:

Post a Comment

ማውጫ

ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ