~ሠ~

                                 

       ፲፭ኛ ፊደል በግእዝ አልፍ ቤት በአበገደ ስሙ ሠውት ጥሩ ስሳ አኃዝ ሲኾን () ስሳ ወይም ሥልሳ ይባላል ሠለሰንና ሰደሰን እይ። ጸሐፍት ግን ነግሠ የሚጣፍ በርሱ ስለ ኾነ ስሙን ንጉሥ ይሉታል። በዐረብና በዕብራይስጥ አንዱ ኅርመት ፊደል በነቍጣ ምክንያት ሲን ሺን እንዲባል በጥንታዊም ግእዝ የሚባል ይህ ሠውቱ እንጂ ሳቱ አይዶለም። ሳቱ ግን እንደ ሳምኬት በስምና መልክ ተለይቶ ተራውና ቍጥሩ ሳይፋለስ ስሳነቱን ሳይለቅ ብቻ ከመባል በቀር እንደ ሠውት መባል የለውም አልነበረውም። ዐይነት በግእዝ በሱርስት በዕብራይስጥ እንጂ በዐረብ የለም ጻዴ ግን ሳድ እየተባለ ንደ ይጠራል ፤ለሠና ለጸ መልክ በቀር የድምጥ ልዩነት የላቸውም። ደግሞ በቅበጥ እንጂ በጽርእ አይገኝም ከግእዝም ጽርኣዊው ሰላማ መጻሕፍትን ጽርእ ወደ ግእዝ መልስ ያን ጊዜ አውጥቶት ከዚያ ወዲህ በግእዝ ቃላት ውስጥ መጣፉና መነገሩ ቀርቷል ይኸውም ሊታወቅ ዕብራይስጥና ዐረብ ሱርስትም የሚሉትን ይልቁንም ዐረብ በሺን የሚጥፈውን ዲልማን ለይቶ በሠውት ጥፎታል። (ዐረብ) ሸሐጸ ሸረበ ሸረዐ ሸረጸ ሸረቀ ነገሸ። ሥሕጸ ሠረበ ሠርዐ ሠረጸ ሠረቀ ነግሠ የሳቱ ፍች እይ

ሠሀለ -ሳለ አሰላስሒል ሰሐለ

ሠሐለ [1]-ራራ ይቅር አለ፤ሥሂል ሠሀለ።

 [2]-ሳለ ሰነገለስሒል ሰሐለ

ሠሀቀ -ሣቀሥሒቅ ሠሐቀ።

ሠሓቂ ሥሑቅ -(ቃን ቃት ሕቅት) የሚሥቅ ሣቂ የሣቀ ሣቃም።

ሠሐቅ -(አው ሣሕቅ ሥሓቅ ሥሐቅ) በቁሙ፤ ሥቆሽ አሣሣቅ መሪር ሠሐቅየ ዘእሥሕቅ። ወለሠሐቅክሙ ሚጥዎ ውስተ ላሕ ምሑረቱ ወእምሠሐቁ ይትዐወቅ ዕዙ -(ኤር፳ -፰። ያዕ፬ -፱።  ሢራ፲፱ -)

ሠሀተ -ዐረፈ ረፍት አገኘሥኂት ሠኀተ

ሠኃቲ ሥኁት -(ታን ታት ኅት) የሠከተ፤ ያረፈ ዐራፊ ረፍት ያገኘ ዝም ዕክም ያለ ጸጥተኛ -(ማቴ፲፩ -፳፪)

ሠሀነ ሞቀ ስሒን ሰኀነ።

ሠሐነ -ሞቀ ተኰሰስኂን ሰኀነ

ሠሐገ  -ጮኸ አሞሸ ሳገስሒግ ሰሐገ

ሠሐጠ -ነካ ጫረ ነጠጠ፤ስሒጥ ሰሐጠ።

ሠሓጺ ሥሑጽ -(ጻን ጻት ሕጽት) ደፋር ዕቡይ አላጋጭ አሽሟጣጭ ተሳዳቢ -(ሆሴ፯ -፭። ሮሜ፩ -፴። ፪ጢሞ - -) መኰንን ሥሑጽ ዕልዋን ወጽልሕዋን ወሥሑጻን። ልሳን ሥሕጽት -(ስንክ -ሠኔ፲፬ ቀሌ። ቄር)

ሠለለ -በቁሙ፤ሰሊል ሰለ ሰለለ

ሠለመ -በቁሙሰላምታ ሰጠሰሊም ሰለመ።

ሠለሠ -ሦስት አደረገሠልሶ ሠለሰ

ሠለስ() -ሦስት፤ ሦስቱ ሦስተኛው። ሠለስቱ አቅርንት በእሉ ሠለስቱ እንዘ ሐዱ ሠለስቱ -(ዳን፯ -፰። ሢራ፳፮ -፳፰ ሃይ -አበ)

ሠለቀ [1]-(ዕብ ቃሌስ) ዘበተ አፌዘ አላገጠ፤ በነገር መታ ሠለቀ ተሣለቀ ምስጢሩ እንደ ጤፍ ዶቄት ልዝብነትና ስላስነት ነው ቅና ጨዎት ስላለበት።

[2]-(ዕብ ሳሌቅ) ላጠ መለጠ ለቀቀ፤ ገፈፈ አነሣ አራቀ ሸልቋቋ ሸለቆ ማለት ዚህ የወጣ ነው

ሠለበ -ገፈፈሰሊብ ሰለበ

ሠለጠ -ፈጸመ ረሰ፤ሰልጦ ሰለጠ።

ሠለፈ -በቁሙ፤ሰሊፍ ሰለፈ

ሠሉስ -የዕለት ስምና ቅጽል፤ ማግሰኞ ማግስተ ሰኞ፤ የሰኞ ማግስት የእሑድ ሣልስት በሰኞና በረቡ መካከል ያለው ዕለት ቅጽልም ሲኾን ሦስት ሦስተኛ ያሰኛል ምሕዋረ ሠሉስ ዕለት ስከ ሠሉስ መዋዕል። በሠሉስ ዕለት ኣነሥኦ። ሠሉስየ ዮም -(ዮዲ፪ -፳፩ አስቴ፬ -፲፮ ዮሐ፪ -፲፱ ፩ነገ - -፲፫) ሲበዛም ሠሉሳት ያሰኛል

ሠሊቅ ቆት -(ሠለቀ ይሠልቅ ይሥልቅ) መሠለቅ፤ ማላም ማድቀቅ

ሠሊክ -ሽቱሰሊኅ

ሠሊጥ ጦት -(ሠለጠ ይሠልጥ ይሠልጥ ዕብ ሻላጥ። ሱር ሽላጥ። ዐረ ሠሊጠ) የጠፈረ ሰርዌ መሠልጠን ጌታ መኾን፤ ማየል መበርታት፤ ኀይል ክሂል፤ መብት ማግኘት፤ እንደ ወደዱ ለማድረግ። ዐበይቶሙ ይሠልጡ ላዕሌሆሙ ወአልቦ ዘእሬሲ ይሠለጥ በላዕሌየ መኑሂ -(ማቴ፳ -፳፭ ቆሮ - -፲፪) በሠለጠ ፈንታ ተሠልጠ ተሠለጠ ተሠልጠነ ይላል ስሕተት ነው። አግብርት ተሠልጡ ላዕሌነ። ወሶበ ርእዩ ዛቲ ኀጢአት ተሠልጠት ላዕለ ብዙኃን ዘይሤለጥ በመንፈሱ። ዘይሤለጥ ላዕሌከ ተሠለጥከ በሥጋከ -(ሰቈ፭ -፰። - -፲፫ ምሳ፲፮ -፴፪። መክ፰ - ሢራ፵፯ -፲፱)

ሠላሲ -(ሲት ስያን ያት) የሠለሰ የሚሠልስ፤ ሠላሽ ሦስት አድራጊ።

ሠላሳ -(ዕብ ሽሎሽም) በቁሙ፤ የአኃዝና የቍጥር ስም -() ጊዜ ዐሥር ወይም ጊዜ ሦስት። መዋዕለ ላሕ ለሙት የሚለቀስበት። -(ተረት) በሠላሳ እግርኽን አታንሣ፤ ባርባበረኽ ግባ እየዐርግ ምሠላሳ ወኢይወርድ እምሠላሳ ወትረ ይከውን ሠላሳ -(መር -ዕዉ)

ሠላስ -የቍጥር ስም ሦስት፤ በኹለትና ባራት መካከል ያለ ጥር ጊዜ አንድ ወንድና ሴት ያስተባብራል፤ መደቡ ግን የሴት ብቻ ነው ሠላስ አኃቲሆሙ ምስሌሆሙ። ወሀሎ ህየ ሠላስ መራዕየ ባግዕ ሠላስ መዋዕል። በእንተ ሠላስ ጢአቶሙ። ሠላስ አርዳኢሁ -(ኢዮ፩ -፬። ዘፍ፳፱ -፪። -፲፪። ዓሞ፩ -፫። ስንክ -ጥቅ፳፩)

ሠላጢ መሠልጥ ሥሉጥ -(ጣን ጣት ልጥ) በቁሙ፤ የሠለጠነ፤ ሥልጡን ሠልጣና፤ ሥልጣኔ ያለው ሥልጣን የተሰጠጥው ሥሉጥ ውእቱ በዘፈቀደ። ንጉሥ ሥሉጥ ርእዩ ከመ ኵሉ ሥሉጥ ይሕየውሂ ወይእመንሂ ንትሙ ሥሉጣን ላዕለ ኵሉ ሕዛብ -(ዮዲ፰ -፲፭ መክ፰ -፬። ኪዳ ዲድ - ራእ፲፩ -)

ሠሌዳ -በቁሙሰለደ

ሠልሶ ሶት -(ሠለሰ ይሤልስ ይሠልስ። ዕብ ሻሌሽ) መሠለስ ሦስት ማድረግ ሦስት መክፈል ሦስት ማለት። ይቤሎሙ ሠልሱ ወሠልሱ። ንሤልስ ዘንተ ስብሐተ ዋሕድ አምላክ እን በአካል ይሤልሶ -(፫ነገ -፲፰ -፴፬። ኪዳ ስንክ -ግን፳፯)

ሠመርመር -መወደድ ያለው ንስር ቀይና ጥቍር ያንበጣ ፀር። ዖፍ ዘይሰመይ ሠመርመር ዘባኑ ጸሊም፤ ርሡ ወእገሪሁ ቀይሕ . . . ወሶበ ይመጽእ አንበጣ ውስተ ሀገረ ዐዘም ይመጽኡ ሙንቱ አዕዋፍ ሠመርመር ወይቀትልዎሙ ለእሙንቱ ናብጥ ወያሀጕልዎሙ -( - - -ገ፳፩)

ሠመነ -ስምንት አደረገሰምኖ ሰመነ።

ሠመከ -ተጠጋሰሚክ ሰመከ

ሠሚር ሮት -(ሠምረ ይሠምር ይሥመር ዕብ ሻማርጠበቀ) መሥመር መውደድ ርጥ ፈቃድ ማድረግ እሺ በጎ ይኹን ሠመርኩ ማለት፤ ልመናን ነገርን ወዶ መቀበል ሠምረ እግዚ። ሥመር እግዚኦ ታድኅነኒ። ዘትጸልእ ርእስከ ጽላእ ካልእከ፤ ወሥመር ሰብእ ዘትሠምሮ ለርእስከ ሠምረ በዝንቱ ምድኅረ ሰአልዎ ሎቱ መሥዋዕተ ቤል ዘሠምረ -(ያዕ፬ -፲፭ መዝ -፴፱። ፈላስ - -፬። ድጓ)

ሠማሪ -(ሪት ርያን ያት) የሚሠምር የሚወድ  ወዳጅ። ንሕነ ኵልነ መዋትያን ዘጸላኢኒ እምኔነ ወሠማሪ -(ግንዘ)

ሠምረ -አፈራ በጀሰሚር ሰምረ።

ሠምዐ [1]:-ሰማ መሰከረ፤ሰሚዕ ሰምዐ

[2]-ሠም ኾነ ጦፈ ቀለጠ ነጠረ ረጋ ጸና ተጋገረ

ሠምዕ -(ዓት። ዐረ ሸመዕ) ሠም ጧፍ የጧር ሰፈፍ፤ ንጥሩ ግግሩ፤ ልጥልጡ ነጋሪቱ ፋናው መብራቱ ለእመ ሰረቀ ምንተኒ እምንዋየ ቤተ ክርስቲያን፤ ሠምዕ ዘይት ሠምዕ። መኃትው ብሩሃት ወሠምዓት ንጹሓት -( - -፲፯ -፮። ግንዘ። አፈ -ተ፬)

ሠሥዖ ዖት -(ሠሥዐ ይሜሥዕ ይሠሥዕ ዐረ ሸሠዐ) መሣሣት መራራቅ ዘር ዘር ማለት የቡቃያ የዘር ያታክልት የጠጕር።

 -መሣሣት መርቀቅ፤ ሥሥ ረቂቅ መኾን -(ዐማርኛ)

 -መሠሠት መንፈግ ሆዳም ሥሥታም መኾን ትሠሥዕ ለኵሉ መብልዕ። ካህናት ዘሠሥዐት ነፍሶሙ በረኀብ ርኩስ። ይሤሥዑ በሊዕ -(ሢራ፴፯ -፳፱ ቀኖ -ኒቅ ዲድ -፯። ተሰ - -)

ሠረረ -በረረ መጠቀሰሪር ሰረረ)

ሠረቀ -(ዐረ ሸረከ) አሰረ ቋጠረ፤ አዋሰበ ጐነጐነ ሠረከን ተመልከት።

ሠረቃዊ -(ዕብ ማሕ) ሠርጽ ቡቃያ ለጋ ወጣት ገና የሚያድግ ገብርየ ሠረቃዊ ናሁ ብእሲ ሠረቃዊ ስሙ፤ ወይሠርቅ -(ዘካ፫ - - -፲፪)

ሠረበ -ፈሰሰ ጐረፈ፤ሰሪብ ሰረበ

ሠረከ -(ዐረ ሸረክ) አዋሰበ ጐነጐነ ሰረ፤ ዐዘበ የቶታን የጫማ፤ የወጥመድ። አሠመረ አስነበረ፤ የሢር የብራና። ኹለተኛውን ሠረቀን ተመልከት ዚህ ጋራ ነው ለቀ ተለውጦ ወደዚያ ኺዷል

ሠረዝ [1]-ዐጥር፤ የስሕተት ምልክት፤ ከማንበብና መነበብ የሚከለክል።

[2]-የቅኔ መንገድ ስም፤ ኹለት አርእስት ያለው፤ ንባቡም ምስጢሩም በዋዌ እየተጫፈረ የሚኼድ። እምከዊነ ካህን ይኄይስ ዊነ ኖላዊ፤ ወጎለ እንስሳ ትትበደር ምቤተ መቅደስ ባይ ስመ ቤተ መቅደስ ኮነት ፈያታይ፤ ወበላዕለ ኖሎት ኢሀለ ዕለ ካህናት ዘሀሎ እከይ፤ ይህን የመሰለ። ይህ ነጠላ ነው፤ ድርብ ሲኾን አርእስቱ ሦስት ይኾናል። አስተብፅዑ ፍስተ ዓሣ ኢየሱስ ወጴጥሮስ ወሩፋኤል፤ ባሕረ ጥብርያዶስ ኮኑ ኢየሱስ ወፈረ በኅዳጥ ዓሣ አጽገበ ማኅበረ፤ ወእምከርሠ ዓሣ አውፅአ ጸባሕተ ቄሳር ናረ መሠግር ጴጥሮስ አሥገረ፤ ሩፋኤልኒ ሥራየ በዘአእመረ በዓሣሁ ሕየወ ዕዉረ

[3]-ማእከላዊ ነቍጥ ኹለት ዐይነት ያለው ነጠላና ድርብ፤ የቃል መክፈያ፤ የምስጢር መለያ፤ () ነጥብ የሚያንስ የነጥብ እኩሌታ ( -) ነቍጥ የሚበልጥ፤ ኹለተኛና ሦስተኛ የጥፈት ምልክት ነጠላ ሠረዝ ወይም ፥። ድርብ ሠረዝ፤። ሲመች እንደ አኃዝ ቀይ ይጨመራል፤ ሳይመች ይቀራል። ነጠላ ልዩ ልዩነት ባለው በማይጫፈር ቃል በስም ይገባል። ዘምእት ወቦ ዘስሳ ወቦ ዘሠላሳ። ወናሁ ነግረክሙ ዘትብሉ በበይናቲክሙ አነ ጳውሎስ ወአነ ዘአጵሎስ ወአነ ዘኬፋ ወአነ ዘክርስቶስ። ድርብ ባስረጅና በተመሳሳይ ቃልይ ይገባል። ንበር ማእከሌነ ስመ ኪያከ ልሀቀ እግዚ ስመ ይቤ መጽሐፍ አነ ሀጕል ጥበቢሆሙ ጠቢባን ወእሜንን ምክሮሙ መካርያን መኑ እንከ ጠቢብ፤ ወመኑ እንከ ጸሓፊ ወመኑ ዘየኀሥሦ ዓለም፤ ኮኑ አእበዳ እግ ጥበበ ዓለም

()           ሠረየ -ሠየ፤ ፈተለ፤ አቀጠነ፤ አሾረ፤ አንሻረረ እንዝርቱን።

ሠረገ -በቁሙ ወደ ውስጥ ገባ፤ ተሥረገረገ -(ዐማርኛ)

ሠረገላ -(ላት) [1]-ጋድም፤ የቤት የቤተ ክሲያን ዖፉ ወይም ምሰሶው ዋልታ ገበታ ተሸክሞ የሚቆምበት ተጋዳሚ መሥመራዊ ዕንጨት። ወገብረ ዐበይተ ማኅፈዳተ እምዕፀ ወታሕቴሁ ሠረገላ -(ዮሴፍ)

[2]-የመንኰራኵር ዘንግ፤ ተጋዳሚው ተሸካሚው ብረት መንኰራኵሩ እንደ እንዝርት ራስ በኹለት ወገን የሚሰካበት፤ የሚዋደድበት ከርሱ ጋድምነት የተነሣ ላዩም ታቹም፤ መላው ኹለንተናው፤ ፈረሶች የሚስቡት ኹሉ ሠረገላ ይባላል። ፪ኛም የኼደበት መንገድ፤ መሥመር መምሰሉ የስሙን ምስጢር ያስረዳል ሠረገላ ሠናይ በብዙኅ ሠረገላየ ሰብአ ሠረገላት በሠረገላ ይረውጹ -(ኢሳ፳፪ -፲፰ ፴፬ -፳፬ ዮዲ፯ - ድጓ) በመንኰራኵርም ፈንታ ሠረገላ ይላል ቃለ ነጐድጓድከ በሠረገላት -(መዝ -፸፮)

ሠረገላዊ -ባለሠረገላ፤ ነጂ፤ ተቀማጭ ሠረገላዊ ዘእንበለ ድርዐ ጺን ፈረሳዊ ዘእንበለ ያንው -(መጽ -ምስ)

ሠሪም ሞት -(ሠረመ ይሠርም ይሥርም) ማረግረግ፤ መቅለጥ፤ መሳብ መዋጥ ማስጠም ማስመጥ፤ የመሬት የውሃ

ሠሪቅ ቆት -(ሠረቀ ይሠርቅ ይሥርቅ ዐረ ሸረቀ ዕብ ዛራሕ ሱር ድናሕ) መነሣት፤ መውጣት፤ ብቅ ማለት፤ መብቀል መወለድ፤ መብራት መታየት መገለጥ፤ የፀሓይ የጨረቃ እምከመ ሠረቀ ፀሓይ የአትዉ ብርሃን ዐቢይ ሠረቀ ላዕሌሆሙ። እገብር ሐዲሰ ዘይእዜ ይሠርቅ ሠረቀ በሥጋ ትሬእዮሙ ንዘ ይሠርቁ -(መዝ -፻፫ ኢሳ፱ -፪። ፵፫ -፲፱ ኤፍ አረጋ -ድ፩)

 -መባት፤ መግባት፤ መዠመር፤ የወር ያመት። ኅሣሥ ለእ ሠረቀ በሠሉስ። በክልኤቱ መተ መንግሥቱ ሠረቀ መስከረም በዕለተ ሰኑይ -(ሥር -ድጓ ታሪ -ነገ)

ሠሪብ ቦት -(ሠረበ ይሠርብ ይሥርብ ዐረ ሸረበ) መማግ መጠጣት መሳብ መምጠጥ። ይሠርብ ደምየ። ይሠርባ ለኀጢአት ከመ ስታይ። ወሠሪቦ ብሒአ -(ኢዮ፮ -፬። ፲፭ -፲፮ ዮሐ፲፬ -)

ሠሪዕ ዖት -(ሠርዐ ይሠርዕ ይሥራዕ ዐረ ረዐ ዕብ ሣራዕ) መሥራት ማድረግ፤ ማበጀት፤ ማዘጋጀት፤ መምረጥ፤ ማቅረብ፤ መዘርጋት፤ መሰደር መደርደር፤ የሥራ የማእድ የወጥመድ የሕዝብ የሰራዊት። ሥርዑ ማእደ ዘሠርዐ መሥገርተ። ብዙኀ ሠርዑ ውስቴቱ ይሠርዖሙ ለአሕዛብ ሠርዑ ሰራዊቶ ኪያሆሙ ሠርዐ -(ዘፀ፳፮ -፴፭። ሢራ፳፯ -፳፮ ፴፬ -፲፪። ኢዮ፲፪ -፳፫ ዮሴፍ። ሮሜ፰ -፳፱) ዘርዐንና መዝርዕን ተመልከት በሠ ተለውጧል

 -ማዘዝ፤ መወሰን፤ መጣፍ፤ ማኖር፤ የሕግ የሥርዐት ስንክሳር ዘሠርዑ በዊነ ያሬድ ሠርዐ ማሕሌተ ለለ ዘመኑ ሠራዕኩ ኆጻ ወሰነ ባሕር፤ ንበርኩ ረሰይኩ ብሂል -(ስንክ -መጋ፩ ግን፲፩)

()           ሠሪው ዎት -(ሠረወ ይሠሩ ይሥሩ) አው ሠርዎ ዎት -(ሠረወ ይሤሩ ይሠሩ። ዕብ ሻሬሽ) መንቀል፤ ከሥር ማፍለስ ጨርሶ ማጥፋት፤ መደምሰስ ትሥሩ ወትትክል ይሤሩ መሠረተ ንዑ ሥርዎሙ እምአሕዛብ -(ኤር፩ -፲። ራ፫ -፲። መዝ -)

 -ሥር መስደድ፤ ሥር መያዝ፤ ሥራም መኾን መጽደቅ ካፈር ከመሬት መሰማማት የዛፍ የተክል የቡቃያ

ሠሪዝ ዞት -(ሠረዘ ይሠርዝ ይሥርዝ) መሠረዝ፤ ማጠር፤ የተጣፈን ቃል ስሕተት ስለ ኾነ ቀለም ማልበስ ወይም በላዩ እንደ መሥመር ማሳለፍ፤ ማጋደም።

ሠሪጽ -መሥረጽ፤ አሥራጺውን አኽሎ በባሕርይ በመልክ መስሎ ተካክሎ፤ ከአሥራጺው አካል መውጣት መገኘት፤ ያው ግን ተድኅሮ ተመትሮ፤ የባሕርይ ተከፍሎ ሳይኖር። ወወሰኩ ላዕለ ሃይማኖት ዘሠርዑ ሠለስቱ ምእት ዐሠርቱ ወሰመንቱ -(፫፻ -፲ወ፰) ወይቤሉ ወነአምን በበመንፈስ ቅዱስ ዘሠረጸ እምአብ ስከ ተፍጻሜታ። ወእሎንቱ አበው ምእት ወኀምሳ አውገዙ ዘይዌስክ ምድኅረ ዕለ ሃይማኖት ያሐጽጽ እምኔሃ። ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ ዘሠረጸ ምአብ። ከመ መንፈስ ቅዱስ ሠረጸ እምአብ፤ ወነሥአ እምወልድ ወሞገስ ይሠርጽ ዘእንበለ ምኀበ ምግባራት ሠናያት -( - - -ገ፻፸፱ ጸሎ -ሃይ ያዕ -ዘእል ማር -ይሥ፳ -) በሠረጸ ፈንታ ወፅአ ይላል፤ ፍችው ወመንፈስ ቅዱስ ይዜኑ ዘከመ ወፀአ እምአብ ወዘከመ ሥአ እምወልድ -(ቅዳ -ግሩ)

ሠሪጽ ጾት -(ሠረጸ ይሠርጽ ይሥርጽ። ዕብ ሻራጽ) መፍላት መውጣት፤ መብቀል ሥር መስደድ፤ መለምለም፤ ማፈጥፈጥ፤ የተሐዋስያን የአዝርዕት የአትክልት። ለታውፅእ ባሕር ባለው፤ ዕብራይስጡ ይሽርጹ ሀማዪም እንዲል -(ዘፍ፩ -) ውእተ ጊዜ ሠረጸ እስመ አልቦ ዕመቅ ለመሬቱ። ይሠርጽ ሥርዎሙ። ዕፀው ሠረጹ በትር ትሠርጽ። እምሥርወ እሴይ ሠሪጻ -(ማቴ፲፫ - መዝ -፹፬። ኢሳ፴፯ -፴፩። ሉቃ፳፩ -፴። ዘኍ፲፯ - ድጓ)

ሠራብ -(ዐረ ሸራብ) ዝኒ ማሁ። አዕረገ ህየንተ ሥራበ ወይን ሠራበ ሦከ -(አብጥ -)

ሠራዒ -(ዒት ዕያን ያት) የሚሠራ፤ የሚያዝ፤ የሚጥፍ፤ የሚወስን። እግዚ ሠራዒሃ ሰንበት። ሠራዒ ጳውሎስ ሠራዕያነ ሕጋቲሃ ለቤተ ክር -(ቀሌ ቂር ቅዳ -ግሩ)

(ላጥ)         ሠራዊ -(ዊት ውያን ያት) የሚነቅል የሚያጠፋ፤ ነቃይ አጥፊ።

ሠራዪ -(ዪት ይያን ያት) ሥራይ የሚያደርግ፤ ሥራየኛ፤ አስማታም፤ መድኀኒታም

ሠራጺ -(ጺት ጽያን ያት) ሚሠርጽ፤ የሚወጣ፤ ወጪ። መንፈስ ቅዱስ ሠራጺ፤ ወኢአሥራጺ። ከዊነ ሠራጺ መንፈስ ቅዱስ ባሕቲቱ -(አትና። ያዕ -ዘእል) መሥረጽ ግብሩ፤ ሠራጺ አካሉ ሠራጺነት ዊነ ሠራጺ የአካሉ ባሕርይ፤ ወይም ህላዌ ይባላል፤ የህላዌን ፍች ተመልከት እነትና ከዊን አንድ ወገን ነው።

ሠር -ቁመት፤ሰሪር ሰረረ።

()          ሠርሖ ሖት -(ሠርሐ ርሕ ይሠርሕ ዐረ ሸረሐ፤ ከሠተ) ማበጀት ማሳመር ማቅናት፤ ማስላት ማሳካት፤ ማከናወን፤ ማሰናበት። ሠርሐ ምግባሮሙ በእደ ነቢዩ። ይሤርሕ እግዚ ፍናዊሁ። ይሤርሐከ በኵሉ ግብርከ ዘእንበለ ይትፈጸም ዕርገተ ርባን ወበረከተ ካህን ወሠርሖት። እምቅድመ ሠርሖቱ -(ጥበ፲፩ -፩። ኩፋ -፳፯። ጦቢ፬ -፲፱ - -፲፪ና -፲፫። ዘኍ፮ -፳፫፳፯) በሠርሖት፤ ፈንታ ሥርሐት ይላል፤ ስሕተት ነው ንቀድም በረድኤተ እግ ወበሥነ ሥርሐቱ -(ያዕ -ዘእል)

ሠርም -(ዐረ ሸርም) ረግረግ፤ ማጥ፤ የሚያጠልቅ የሚያሰምጥ፤ ያዛባ የጭቃ ጕድጓድ ዘቅት። ለእለ ውስተ ሠርም ይትመነደቡ መድኅን። ዕመቀ ሠርመ ጢኣት። ረዳኢ ለእለ ውስተ ሠርም -(ኪዳ። ቀሌ። ድጓ)

ሠርቃዊ  [1]-የጨረቃ ወር ወርኅ ሠርቃዊ -(አቡሻ -፴፫)

[2]-(ዕብ ቄዴም) ምሥራቅ ምሥራቃዊ ደብር ሠርቃዊ -(ዘፍ፲ -)

ሠርቅ [1]-መውጫ መገለጫ ምሥራቅ መንገለ ሠርቀ ፀሓይ ደብረ ዘይት ዘሀለወት በሠርቀ የሩሳሌም። በከመ ይርሕቅ ሠርቅ ምዐረብ -(ዘፍ፳፭ - ዮሴፍ። መዝ -፻፪)

[2]-መባቻ፤ የወር መዠመሪያ፤ ልደተ ወርኅ፤ መብቀያዋ መወለጃዋ፤ ወር ቀን ጌሠም ሠርቀ ወርኅ ሠርቀ ርኅክሙ ዕለተ ሠርቅ ርእሰ ሠርቅ በኀሙስ ሠርቅ በዐሡር ሠርቅ -(፩ነገ -፳፭ - ኢሳ፩ -፲፬። መዝ -፹። ዘፀ፵ - ሕዝ፩ -፩። ኤር፶ -)

ሠርብ -መጠጥ፤ የተበጀ የተዘጋጀ። መጽሐፍ ግን በሠርብ ፈንታ አሥራብ ይላል ያንዱን በብዙ። አሥራበ ወይን ሥራበ ሶከር -(አብጥ -፫። አርጋ -)

ሠርክ -(ዐረ ሽሪክ ሽርክ ሱቱፍ) በቁሙ፤ ማታ ምሽት፤ ካ፲፩ ዓት እስከ ቀዳማይ ዓተ ሌሊት፤ የመዓልት ጫፍ መጨረሻ መሰናበቻ የሌሊት መባቻ፤ ሱቱፈ ጽልመት ዐርብን ተመልከት መሥዋዕተ ሠርክ ምነግህ እስከ ሠርክ ፍና ሠርከ በበ ሠርክ ሠርከ ሠርከ ትበልዕ ሠርከ ሠርከ ይዴረሩ -(መዝ -፻፵ ዮዲ፪ -፯። ዘሌ፮ -፲፫ ፪ዜና -፲፫ -፲፩ ዮዲ፲፪ - ሱቱ -ዕዝ፲፬ -፵፯)

ሠርዌ [1]-(ራዊት። ሱር ሣሪታ) ንድ ሥር የሚወጣ፤ ዐምድ ምሰሶ ወጋግራ የቤት ዕንጨት የድልድይ ጋድም፤ መሸጋገሪያ የመርከ ምሰሶ ደንቀል ንግዝም ሠርዌ። ወናሁ ሠርዌ። ታሕተ ሠርዌ ቤትከ ዕፀው ለጠፈረ ቤት ወለሠራዊት ሠርዌ ተንከተም። ሠርዌ ሐመር -(፬ነገ - - ማቴ፯ -፬። ሢራ፳፱ -፳፱ ዜና -፳፬ -፲፩ ፪ነገ -፳፫ -፳፩ አርጋ)

[2]-ጥራጊ፤ ጕድፍ ጭራሮ። ከመ ሠርዌ ይውዕዩ -(ተረ -ኤር)

[3]-ሉሕ ጠርብ ዝርግ ጠፍጣፋ ዕንጨት ሳንቃ። መስመክተ ሠርዌሁ። ሠራዊተ ዐጸድ -(ዘፀ፳፮ -፲፯ ፴፱ -)

-የሸማኔ ዕቃ፤ መጠቅለያው። ሠርዌ አነምት -(፩ዜና -፲፩ -፳፪)

[4]:-አለቃ፤ ጭፍራ፤ሰሪው ሰረወ፤ ሰርዌ።

ሠርዮ -ቀለም ስባቅ ማናቸውም ዐይነት። ሠርዮ ምስለ ፀምር -(ቄር)

ሠርዮ ዮት -(ሠረየ ይሠሪ) መሠረይ ሥራይ ማድረግ፤ አስማት መድገም፤ መጠንቈል ማሟረት፤ ምትሀት ማሳየት፤ የክፉ እንዘ ይሤርያ መሠርይ ጠቢብ። ንትሙ መሰግላን ትሤርዩ ገረ -(መዝ -፶፯። ስንክ -ሐም፲፭)

 -ማዳን መፈወስ፤ መድኀኒት ማድረግ፤ ለማዳን። ውእቱ አቍሰለነ ወይሤርየነ ሥረይ ለነፍስየ -(ሆሴ፮ -፩። መዝ -)

ሠርገለ -አጋደመ፤ መሥመር ጣለ፤ አሠመረ፤ በርሳስ በቀለም በወስፌ ነደፈ በገረ፤ አስነበረ፤ የወረቀትና የብራና።

ሠርገል -(ዕብ ሳርጌል) መሥመር ማሥመሪያ፤ አራት ገጽ ያለው፤ ቀጥ ያለ የተካከለ ዐጭር ዘንግ።

ሠርጕ -ጌጥሰረገ፤ ሰርገወ።

ሠርግ -(ዐረ ሸርግ) መስኖ፤ የመስኖ ውሃ ቦዩ መትረቡ፤ ታናሽ ወንዝ ኵሬ ዐዘቅት።

ሠርጽ -(ጻት። ዕብ ሼሬጽ ተሐዋሲ) ቡቃያ፤ ዐዲስ ወጣት ለጋ ቀንበጥ ሙሽራ ውልብልቢት ዘርዕ ምስለ ሠርጽ ሠርጽነ ዘእንበለ ይጸምሒ ሠርጸ ሊባኖስ ሠርጸ ገዳም ዘሠናይ ሠርጹ ወጽፉቅ ጽሉ -(ዓሞ፱ -፲፫ ጥበ፪ -፰። ሢራ፶ -፰። ሕዝ፲፮ -፯። ፴፩ -) ሠርጸ ጢስ ቢል ዐምደ ጢስ ማለት ነው፤ ዐምደ ደመና እንደ ማለት -(ማሕ፫ -)

ሠቀየ -አጠጣሰቅይ ሰቀየ

ሠቂቅ ቆት -(ሠቀ ይሠቅቅ ይሥቅቅ። ዕብ ሣክህ) ማልበስ መክደን መሸፈን። መሠቀቅ ማሠቀቅ

ሠቅ -ማቅሠቂቅ ሠቀ።

 -(ቃት። ዕብ ሣቅ። ሱር ሣቃእ። ቅብጥ ሦክ) በቁሙ፤ ማቅ፤ ጕራጅ ምንጣፍ፤ ፀምር የሚሠራ ሸካራ፤ የሚኰሰኵስ፤ የሚያሠቅቅ፤ በሐዘን ጊዜ የሚለብሱት፤ የሚያሸርጡት። ታላቅ ኪስ፤ ከረጢት የማቅ ዐይበት ዳውላ ጠብለልዎ በሠቅ። ሰሊሆሙ መዝመዙ በሠቅ አልበሱ ምሥዋዐ ሠቀ። ቅንቲ ሠቀ እግ ረበቦ ሠቅ ተባዕታይ ማይ ወገብረ ሠቃተ ምሉአ ኆጻ -(ስንክ -መስ፩ ኅዳ፩ ዮዲ፬ -፲። ኢሳ፫ -፳፬ መቃ -ገ፳፭ ስንክ -መጋ፰)

ሠቅሠቀ -(ዕብ ሣባኽ ዐረ ሸበከ) ሸከሸከ ሠራ ታታ በሳሳ የማቅ የመግለቦ የወንፊት ያይነ ርግብ ሥራ። ከጥፊው በቀር አንቀጹ አይገኝም።

ሠቅሠቅ -ዝኒ ከማሁ፤ የተበሳሳ መግለብ ዐይነ ርግብ። በሥቅሡቅ ፈንታ ሠቅሠቅ ይላል ወግበር መጥበስቶ ሠቅሠቀ ከመ መሥገርተ ዓሣ ዘብርት። ንተ ሠቅሠቅ ትሬኢ -(ዘፀ፳፯ -፬። መሳ፭ -፳፰)

ሠበ ሠበበ -(ሠቢብ ዕብ ሾቤብ ሻቤብ) ወጋ በሳ፤ አሳለፈ። ሰበረ አጐበጠ፤ ጠመዘዘ ሽባ ሽቦ ማለት የዚህ ነው።

ሠበረ -በቁሙ፤ሰቢር ሰበረ

ሠበን -በቁሙ ነጭ ልብስ፤ሰበን

ሠበከ [1]:-አስተማረሰቢክ ሰበከ

[2]:-ሠራ ጠፈጠፈሰብኮ ሰበከ

ሠበጠ -(ሠቢጥ በጠ ተፀብጠ) ቀረበ ተዘጋጀ፤ ዝግጁ ኾነ፤ ለመብላትና ለመበላት የሰውና የምግብ። ፈንታውን ያዘ ረከበ፤ እጅ አደረገ፤ ለመቍረስ ለመጕረሥ ፀበጠንና ኔአን እይ

ሠቢሕ ሖት -(ሠብሐ፤ ይሠብሕ ይሥባሕ ትግ ሐባ ብሐ) መሥባት መወፈር፤ መደንደን ጮማ መኾን። ይሠብሕ መራዕይከ ሠብሐ ወገዝፈ ወርሕበ። ዘሠብሐ ትጠብሑ -(ኢሳ፴ -፳፫ ዘዳ፴፪ -፲፭ ሕዝ፴፬ -)

()          ሠብሐ አመሰገነ -አመሰገነሰብሖ ሰብሐ

ሠብል -በቁሙ፤ሰቢል ሰብለ

ሠብሠበ -(ሰበበ፤ ወሰበ ዕብ ሻብሼብ) ታጠረ ተከበበ ተቀዳጀ፤ በዐጽቅ በሐረግ የሥራ የጌጥ ሸበሸበ አሸበሸበ ሽብሽቦ ሽብሸባ ደረገ፤ የስፌት የማሕሌት ሰበበንና ወሰበን እይ

ሠብሣብ [1]-(ባት ጽር ርጋኒ ዐረ ንቢል። ዕብ ሳል) ታላቅ ቅርጫት አፈ ሰፊ የጐታ ዐይነት ዐጽቅ ከሐረግ የተሠራ ወአውረዱኒ በሠብሣብ እንተ መስኮት እምአረፍት -(፪ቆሮ -፲፩ -፴፫)

[2]:-ጋብቻ ግቢወሰበ ሰብሳብ

ሠብእ -ሰው፤ሰቢእ ሰብአ

ሠተረ -ዘረጋሰቲር ሰተረ

ሠትር -መሥመር ወስፌ ርሳስ ቀለም ያለፈበት፤ ሰንበሩ ንድፋ ቢጋሩ።

ሠቲር ሮት -(ሠተረ ይሠትር ይሥትር ዕብ ሣታር ዐረ ሸተረ) መሠንተር መቅደድ፤ መሠንጠቅ፤ መክፈል መቍረጥ መበጠስ መቈንጸል፤ መግረፍ መግጠብ ማቍሰል። ገብር ኩይ ሥትሮ ገበዋቲሁ። ዘዘ ይሥትርዎሙ ስከ ያስተርኢ ንዋየ ውስጦሙ። አዘዘ ይስቅልዋ በሥዕርታ ወይሥትርዋ ሠለስተ ሰዓተ -(ሢራ፵፪ -፭። ዲድ -፳፪። መቃ ስንክ -ጥቅ - -፲፰ -፳፭) ዘትርን ተመልከት፤ የዚህ ዘር ነው

ሠነነ -እሾለ፤ኒን ሰነነ።

ሠኑይ -ኹለት፤ሰንይ ሰነየ።

ሠኒቅ ቆት -(ሠነቀ ይሠንቅ ይሥንቅ። ዐረ ሸነቀ፤ ዐነቀ። ሱር ሥናቅ ዐጣ ተቸገረ) መሠነቅ፤ ሥንቅ መያዝ መውሰድ፤ ለመንገድ የሚኾንን ነገር ማከት፤ ማሰናዳት። ሠነቀ ምንዋይከ ዘእንበለ መግነዝ -(ግንዘ። ኢያ፱ - ማር፱ -)

ሠናይ -(ይት ያን ያት) መልካም ውብ፤ ደግ በጎ ቅን፤ ደስ የሚያሰኝ፤ የመልክ የጠባይ። ሠናይ ለርእይ ሠናይት በራእይኪ ምግባር ሠናይ። ሠናይት ለሠናያን ተፈጥረት ሠናይ ልብ መክፈልት ሠናይ ዐስብ ሠናይ ዜና ሠናይ። ቃል ሠናይ -(ዘፍ፪ -፱። ዮዲ፲፩ -፳፫ ማቴ፭ -፲፮ ራ፴፱ -፳፬ ሉቃ፰ -፲፭ -፪። መክ፬ -፬። ሮሜ፲ -፲፭ መዝ -፵፬) ሠናይ ቅጽልና በቂ እየኾነ እንዳወራረዱ በብዙ ዐማርኛ ይፈታል ምስጢሩ ግን መልካምነት አይወጣም። ውስተ እዴሆሙ ሀለወት ሠናይቶሙ ቢል፤ ብዕል በረከት ድልብ ገንዘብ ያሰኛል -(ኢዮ፳፩ -፲፮)

ሠኔ -(ቅብጥ ፓዎኒ። ዕብ ሲዋን) የወር ስም፤ ዐሥረኛ ወር በግብጽና በኢትዮጵያ ሠናየ ዘርዕ ወርኀ ዘርዕ ሠናይ ማለት ነው -(ተረት) ለሞኝ ሠኔ በጋው መስከረም ክረምቱ ጋላም ዘር ሲል ሠኚ ይላል

ሠንአ -ገጠመ ተስማማ፤ሰኒእ ሰንአ

(ጥን)         ሠንዮ ዮት -(ሠነየ ይሤኒ ይሠኒ ዐረ ሠነዐ ሐሡነ ሻናህ መልኩን ለወጠ ሌላ ኾነ) ማማር፤ መዋብ ሐዲስ መልክ ማውጣት፤ ጥሩ ውብ ደመ ግቡ መኾን በመልክና በጌጥ ደስ መስኘት። ሠባሕኪ ወሠርይኪ ጥቀ ፈድፋደ ሕሥምት ንተ ነየት ይሤኒ ሕዩ ሠነየት ራእዮሙ -(ሕዝ፲፮ -፲፫ ማሕ፯ -፯። አርጋ -፩። መዝ -፵፬። ዳን፩ -፲፭ መሳ፲፭ -)

 -መብለጥ፤ መሻል፤ ደግ ደኅና መልካም መኾን የጠባይ ብእሲት ንተ ትሤኒ ምብእሲት ዘይሤኒ ወይነ ይሠርሕክሙ በእንተ ትሤኒ በእከየ ገጽ ይሤኒ ልብ -(ሢራ፴፮ -፳፮ ዮሐ፪ -፲። ጦቢ፯ -፲፩። መክ፯ -)

ሠዐለ [1]:-ለመነ፤ስኢል ሰአለ።

[2]:-ሳለ፤ሰዐለ።

ሠዐረ -ሻረስዒር ሰዐረ

ሠዓሊ -(ሊት ልያን ያት) የሚሥል፤ የሚፈጥር ሣይ ሣዪ ፈጣሪ ሠዓሊና እንዘ እሬኢ ባማርኛ ይተባበራሉ። -(ግጥም ሚስቱን ሠዓሊ የቀማው) ባላየው ነው እንጂ ተኝቼ ሌሊት፤ ሚስቴን ሳይ በወሰዳት። -(የሠዓሊው መልስ) እንቅልፋምነትኽን ይልቅ እኔ ዐውቃለኹ፤ ብሥል ሰው እንጂ ነኝ ምን መስዬኽ አለኹ። ሠዓሌ ሕፃናት -(ቅዳ። ድጓ)

ሠከረ -(ሠኪር። ዕብ ሣካር) ተከራየ በቍርጥ ገዛ ተዋዋለ የከብት የጕልበት የመሣሪያ ዐሰበንና ዐሰየን እይ፤ አሽከር ማለት ከዚህ ወጥቷል። ሻከረ፤ ሸካራ ኾነ -(ዐማርኛ)

ሠክረ -ሰከረ፤ሰኪር ሰክረ።

ሠወን -ልጋግ በር ሐረፋ የአፍ ዛሕል

ሠዊት -(ዕብ ሽቦሌት) እሸት ጐምር ዛላ ዘለላ እንቡጥ፤ ታሽቶ ተፈልፍሎ የሚበላ የእክልና የተክል ወናሁ ሰብዐቱ ሠዊት ወአኀዙ ይምሐዉ ሠዊተ -(ዘፍ፵፩ -፯። ማቴ፲፪ -) ሦታ ወጣት ጐበዝ ጕልማሳ ልጅ እግር እሸቴ ውብ እሸት እንዲሉ በኵር በኵራት ቀዳምያት ማእረር በማለት ፈንታ ሠዊት ይላል፤ የመላሽ ስሕተት ነው አመ ዕለተ ሠዊት -(ዘኍ፳፰ -፳፮ ዘዳ፳፫ -፳፭ መሳ፲፭ -)

ሠዊን ኖት -(ሦነ ሠወነ ይሤውን ይሡን) ማልገግ መቈበር ማዝረብረብ፤ ልጋጋም በራም መኾን ሐረፋት መድፈቅ። ሐረፈንና ሤነን እይ ይሤውኑ በአፉሆሙ -(አዋል)

ሠዊዕ ዖት -(ሦዐ ይሠውዕ ይሡዕ ይሣዕ ይሧዕ ይሥዋዕ ዕብ ዌዐ ጮኸ ጠራ ዐረ ሸወይ፤ ጠበሰ) መሠዋት መሥዋዕትና ጸሎት ማቅረብ፤ ማረድ መግደል ማንደድ ማቃጠል፤ ማሳረር ማጤስ መጥበስ ማንጠስጠስ ለማሳረግ፤ ሰረፈን እይ ለሠዊዕ መሥዋዕተ ዘአምጽ ሠዊዕ። ዐርገ ከመ ይሡዕ። ወሦዐ መሥዋዕተ ሡዕ ለእግ መሥዋዕተ ስብሐት -(ዘሌ፩ - -፬። ፩ነገ - -፳፩ ዘፍ፵፮ -)

ሠዊክ ኮት -(ሦከ ይሠውክ ይሡክ ዕብ ሳኽ ያሱኽ ወደየ መስሐ) መውጋት ማድረግ፤ ማሳመም። እሾኽ ማብቀል፤ እሾኽ መባል፤ እሾኻም ሸውከኛ መኾን።

ሠዊጥ ጦት -(ሦጠ ይሠውጥ ይሡጥ ወሰጠ፤ ሶጠ ሠጠየ) መመለስ መቀለስ መልሶ ማምጣት ማግባት ቀድሞ ወደ ወጣበት ወደ ነበረበት ሠውጦሙ ውስተ ምድር አመ ሣልስት ዕለ ሦጣ ለነፍሱ ውስተ ሥጋሁ። ብዉሕ ሎቱ ሠዊጠ መንፈስ ማኅፈደ ሥጋሁ -(ኤር፳፬ -፮። ቅዳ -አፈ መጽ -ምስ) በሦጠ ፈንታ አሦጠ ይላል፤ ስሕተት ነው ወአሦጡ ቀሣውቲሆሙ ዕራቆ ወርቀ አሦጥነ ምድረ ከነዓን አሡጥ ለካልእከ -(ኤር፲፬ -፫። ኩፋ -፵፫። ዘዳ፳፪ -)

ሠዋዒ -(ዒት ዕያን ያት ዕት) የሚሠዋ አቃጣይ ዐጣኝ የምሥዋዕ አገልጋይ። አብርሃም አቅረበ ወልዶ ወኢሦዖ ወተዐሰየ ሴተ ሠዋዒ -(አፈ -ተ፴፬) ካህን ካህናት በማለት ፈንታ ሠዋዒ ሠዋዕት ይላል -(ዘፅ፲፰ -፩። ፲፱ -፳፪ -፳፬። ቆሮ - -፲፫)

ሠዋዪ ሥዉይ -የሸተ የበሰለ፤ ነፍስ ያዋለ

ሠዋጢ -(ጢት ጥያን ያት ሠወጥ) የሚመልስ፤ መላሽ ቀላሽ።

ሠውር -ኮከብ፤ተውር ቶር

ሠውት -ስመ ፊደል ሠዊት ሠዒት ወስት ራስ ሦስት ዛላ ባለሦስት ጣት ማለት ነው፤ መሥዔ እንደ ማለት። ሠለሰና ሠዐየ ጋራ ይሰማማል፤ በዕብራይስጥም እንደዚሁ ሦስት ጣት አለው

 -ሠውትስመ ፊደል፤ሠወየ

ሠውይ ዮት -(663) -(ሠወየ ይሠዊ ይሥወይ ዐረ ሸወይ ጠበሰ ዕብ ሻዌህ መሰለ ተካከለ አማረ ተዋበ ተወደደ) መሸት መጐምራት፤ መብሰል፤ ሰብለን እይ። አመ ይሠዊ ሥርናይ -(ኢያ፫ -፲፭። ያዕ፭ -፯። መጽ -ምስ) በሠወየ ፈንታ ሥወየ ይላል፤ ስሕተት ነው -(ስንክ -ታኅ፯)

ሠውጥ -ጅራፍሰወጠ።

ሠዝይ ዮት -(ሠዘየ ይሤዚ ይሥዚ ዐረ ሸዘ ሸዘእ) መለየት መነጠል መከልከል፤ ማድላት እንዘ ትሤዚ ይሤዚ ንበይነ ንዴቱ ነዳይ ምሕረተ ዳያን እለ ዘእንበለ ሥዚ -(ተረ -ር። ሲኖዶ -፲፪ ሢራ፴፪ -፲፮ ስንክ -መጋ፲፪)

ሠዪም ሞት -(ሤመ ይሠይም ይሢም። ዕብ ሢም። ሱር ሣም። ዐረ አኖረ) መሾም መሸለም፤ ሠልጠን መቀደስ ማክበር። እሠይመከ ውስተ ምድር ሤሞ ለዮሴፍ ዲበ ኵሉ ንዋዩ ንትሙ ጳጳሳት ኢትሢሙ ኵሎ ዘረከብክሙ። ሶበ ትሠይሞ ለጻሕል ወለጽዋዕ -(ዘፍ፵፩ -፵፩። ኩፋ -፴፱። ቀሌ ሥር -ቅዳ)

 -ማስቀመጥ ማኖር መምላት ማሳደር፤ ማቅረብ ማዘጋጀት፤ የምግብ የልብስ ለትንባኾም ሳይቀር ለጠላ ለምርት ይነገራል። ህየ ይሠየማ። ወሤሞ ህየ ላዕሌሆሙ መንፈሶ ቅዱሰ ውስቴቲ ምስጢራተ ብፅዓን -(ቅዳ -ግሩ። ዘፍ፪ - ኢሳ፷፫ -፲፩ ማር -ይሥ፩ -፲፫)

ሠዪብ ቦት -(ሤበ ይሠይብ ይሢብ። ዕብ ወሱር ሣብ ዐረ ) መሸበት ማርጀት መጨበር ነጭ ጠጕር ማውጣት መሻገት መበላሸት። ሣህበን እይ፤ የዚህ ዲቃላ ነው

ሠዪን ኖት -(ሤነ ይሠይን ይሢን ዐረ ሻነ አሳደፈ። ዕብ ሀሽቴን ሸነ) መሸኘት፤ ሸኝታ መኾን። መሸን መሽናት፤ ማውጣት ማፍሰስ፤ ፊር ረር ጭርቅ ማድረግ። ዘይሠይን ዕለ መንጸፉ ዘይሠይን ማየ በሊዕየ እኰስሕ ወሰትይየ ሠይን -( - -፴፫ -፫። ቄድር። ፈላስ)

ሠዪጥ ጦት -(ሤጠ ይሠይጥ ይሢጥ። ቅብጥ ሾት፤ ንግድ) መሼጥ መለወጥ መቸርቸር መሸቀጥ መስጠት መቀበል ገዢ ነገደ የሩቅ ሤጠ የቅርብ የመደብር ሠዪጥ ወተሣይጦ ዘሤጠ ብኵርናሁ -(ራእ፲፫ -፲፮ ዕብ፲፪ -፲፮) በሤጠ ፈንታ አሥየጠ ይላል፤ የጣፊ ስሕተት ነው። አሢጠኒ ኪያሁ በሤጥ -(፩ዜና -፳፭ -፳፪)

ሠያሚ -(ሚት ምያን ያት) የሚሾም አስቀማጭ አኗሪ ሠያሜ ካህናት ሠያሜ ሕግ -(ሲኖዶ ድጓ። አፈ -ድ፴፪)

()          ሠያብ ሥዩብ -ሥዩብ የሸበተ ሽበታም፤ አሮጌ ሽማግሌ ሻጋታ ብልሹ

ሠያን ሠያኒ -(ኒት ንያን ያት የንት) የሚሸኝ ሸኝታ። የሸነ የሚሸን፤ ሻኝ ሽንታም፤ ሽንት የማይቋጥር፤ ፈሪ

ሠያጢ -(ጢት ጥያን ያት፤ የጥ) የሼጠ የሚሼጥ ሸያጭ፤ ጣሪ ነጋዴ ቸርቻሪ ሸቃጭ ሠያጢ ወተሣያጢ ይሁዳ ሠያጤ እግዚኡ ሠየጠ አሕዛብ ተፋጸዩኪ። ሠየጥኪ በነፍሰ ሰብእ -( - -፴፫። መጽ -ምስ። ሕዝ፳፯ -፴፮። ራእ፲፰ -)

ሠይእ -ከንቱ ሥራ፤ሰይእ።

ሠገል -ጥንቈላሰጊል ሰገለ

ሠገም -ገብስሰጊም ሰገመ።

ሠገረ -(ዕብ ሳጋር፤ ሳካር) ጐረ፤ ዘጋ ለፈ፤ የመዝጊያ የቅናት። ጐተተ አሰረ ከሐብስ አገባ አጠመደ ወጥመድ አኖረ በወጥመድ ያዘ መጽሐፍ ግን በሠገረ ፈንታ አሥገረ ይላል ሕተት ነው አሥግሩ ለነ ናጽለ አሥጋሬ ያሠግሩ ሰብአ ከመ ኢታሥግርከ በማሕሌታ። ሥግረኒ ምባሕረ እሳት -(ማሕ፪ -፲፭። - -፴፫ -፬። ኢሳ፰ -፲፭ ራ፱ -፬። ስንክ -ጋ፴)

ሠገራ -በቁሙ ዐዘቅተ ኵስሕ ሰው ሲገባበት የሚዘጋና የሚሸጐር

ሠገራዊ ሠገራዋታዊ -የዘበኛ ወገን በረኛ እስር ጠባቂ -(ስንክ -ታኅ፲፪። መጋ፯)

ሠገር -(ራት) ወታደር ሐብስ ዘበኛ እስሮች እንዳይወጡ እንዳያመልጡ በሩን ዘግቶ ሸጕሮ የሚጠብቅ። ትካፈሉ ልባሲሁ ሐራ ገራት። ንሥኡ ሠገራተ -(ድጓ። ማቴ፳፯ -፷፭)

ሠገኖ -ሰጐንሰገኖ ሰገነ።

ሠጕዐ -ሳገ ሰነገሰጕዕ ሰጕ

ሠጊር ሮት -(ሠግረ ይሠግር ይሥገር ዕብ ሻጋር) መሥገር ቶሎ ቶሎ መኼድ ድቅ ድቅ ማለት፤ የበቅሎ የሕፃን። መሻገር ሽግር ማለት፤ መራመድ እያለፉ መርገጥ፤ ሖረንና ሄደን ኬደን እይ ወሶበ ሠግረ ምዕረ ወካዕበ ወሖረ ምስሌሆሙ እንዘ ይሠግር። ክህለ ሠጊረ ዘእንበለ በትር። ወበዘባነ ባሕር ይሠግር፤ ሐዊሮ ወሠጊሮ -(፩ነገ -፲፯ -፴፱። ግብ፫ -፰። ቀሌ ተረ -ቄር)

ሠጊው ዎት -(ሠገወ ይሠጉ ይሥጉ ዕብ ሣጋህ) አው ሠግዎ ዎት -(ሠገወ ይሤጉ ይሠጉ) መብቀል ማደግ መግዘፍ መግነን፤ መጽናት መበርታት፤ መብዛት መርባት። መሥጋት ማሰብ መፍራት ሥጉ መኾን ረገበን እይ

ሠጋሪ [1]-ሠጋር በቁሙ፤ ኸያጅ ተራማጅ

[2]-መሠግር -(ራን) ዘጊ ሸጓሪ የሚያጠምድ ጥማጅ ወጥመድ ዓሣ ወጋሪ መሠግር ጴጥሮስ አመ አሥገረ እስመ መሠግራን ሙንቱ -(ቅኔ። ማቴ፬ -፲፰ ማር፩ -፲፮)

ሠግላ -ሾላሰጊል ሰገለ።

ሠግራዊ -(ዊት ውያን ያት) የሠግር ሠግራም፤ ሠግር ያለበት ባለሠግር። ዓመተ ሓይ ሠግራዊት -(አቡሻ -፲፯)

ሠግር -በቁሙ፤ የዕለት የብተት ሥግሪያ እርምጃ፤ የጨረቃ ወር መተላለፍ፤ ወይም ትርፍ ፍድፋጅ ይገብሩ ሠግረ ሐደ ወርኀ ለለ ሠለስቱ ዓመት። በራብዕት ዓመት ይገብሩ ሠግረ ሐዱ ዕለት ወይሰምይዋ ለወርኀ ሠግር ጳግሜን ወትከውን ይእቲ ዓመት ሠግረ -(አቡሻ -)

ሠጠመ -በቁሙ፤ሰጢም ሰጠመ።

ሠጠቀ -(ሠጢቅ ሠጠጠ ዕብ ሳዳቅ። ሱር ስዳቅ። ዐረ ጸደዐ) ሠነጠቀ ፈለጠ ተረተረ ቀደደ ዐረሰ ለየ ፈለ በቁመት እንዳክርማ እንደ ቄጠማ ኢሳይያስ ዘሠጠቅዎ ክልኤ ክፍል በሞሠርተ ዕፅ መሠርይ ተናገረ ላዕለ ይሲ ወሠጠቆ ክልኤ መባርቅት እለ ይሠጥቁ ብያተ ወይሠጥቅ ምድረ አፍላግ ሠጠቁ ትዕይንተ ሎፍሊ -(መጽ -ምስ ስንክ -ሠኔ፯ ዮሴፍ ዕን፫ -፬። ፪ነገ -፳፫ -፲፮)

ሠጠወ -ሰጠ መለሰሰጢው ሰጠወ

ሠጢጥ ጦት -(ሠጠ ሠጠጠ ይሠጥጥ ይሥጥጥ ዕብ ሻጥ ቀዘፈ) ሠጠጥ ማድረግ መቅደድ፤ መሠንጠቅ፤ መሠንተር መለየት መክፈል ሠጠቀን እይ የዚህ መንቲያ ነው። ሠጠጠ ልባሲሁ ኦትሥጥጥ ልብሰተ ሥጋዌሁ እሠጥጥ መጽሐፈ ጣውኢከ ሠጠጡ ርሦ ሠጠጣ መንግሥትከ -(ማቴ፳፮ -፷፭። ተረ - ስንክ -ሐም፰ ዮሴፍ። ፩ነገ -፲፭ -፳፰) ሢጥ ሢጢጥ ማድረግ፤ ማንሚያጠጥ። ማሾጠጥ፤ ሾጣጣ ማድረግ

ሠጣጢ -(ጢት ጥያን ያት) የሚቀድ ቀዳጅ ንጣቂ።

ሠጥሐ -አሰጣ ዘረጋሰጢሕ ሰጥሐ

ሠጥይ ዮት -(ሠጠየ ይሠጢ ይሥጢ ዕብ ሣጣህ ሱር ሥጣእ) መጽነን መሳብ መዘንበል፤ ማድላት ማጋደል። መለወጥ ማበድ ከሕግ መንገድ መውጣት። ባለመጽሐፎች ግን አሰጣ ዘረጋ ብለው በሰጥሐ ዘይቤ ይፈቱታል ኢይትቀነያ ስቴ ወኢይሠጠያ ውስተ ስካር -(ቲቶ፪ -) ብዙው መጽሐፍ ደግሞ በሠጠየ ፈንታ ተሠጥየ ይላል፤ አያሰኝም እመ ዘተፈግዐ ወተሠጥየ፤ ዘይፌግዕ ወይሠጠይ። ብዙኃን ሠጥየ ልቦሙ በእንተ ንስት ተመስወ ልቦሙ ወተሠጥየ -(ሄርማ። ፩ዕዝ - -፳፮ ኢያ፭ -)

ሠጺር ሮት -(ሠጸረ ይሤጽር ይሥጽር። ዐረ ሸጸረ፤ ወጋ በሳ። ሸጠረ ከፈለ) መሠንጠር፤ መሠንጠቅ፤ መክፈል መፍለጥ፤ በቁመት። የጸዐለ ቤት ነው። ዘይሤጽር ዕፀወ ምሣር ዘይሤጽር -(መክ፲ -፱። ዲድ -)

ሠፈረ -በቁሙሰፊር ሰፈረ።

ሡሩር ሥሩር -የተመሠረተ የተሠራ የተፈጠረ እስመ ሰብእ ሩር ምነፍስ ወሥጋ ሥሩራት ዲበ መንበረ ወርቅ -(ፊልክ። ማሕ፭ -፲፭)

ሡራኄ -(ኅያት) መብራት ብርሃን፤ ጸዳል ክብር ጌጥ ወሡራኄ እግዚ ተርእየ ደመና ክብር ወለሡራኄ በርሀ ገጹ በሡራኄ መለኮት። ሡራኄ ወጸዳል -(ዘፀ፲፮ -፲። ፳፰ -፪። ገድ -ተክ። መጽ -ምስ)

ሡራሬ -ሥራ፤ አሠራር። ሕንጼሃ ወሡራሬሃ ዳም -(ድጓ)

ሡዐት  -( ) መሠዋት መሥዋዕት መኾን ሥዋዕትነት። ሥምረተ በሡዐተ ወልዱ -(መጽ -ምስ)

ሡዕ [1]-( ሥዋዕ) ማቀጣጠያ ጭራሮ ገለባ በት ጧፍ ጋዝ ክብሪት፤ የተልባ እግር ፈትል የፋኖስ ቋድ ከጋዝ የሚዋሐድ  ዐብሮ የሚነድ። ሡዐ ዘይጠይስ ያጠፍእ ወጠፍኡ ሐመደ ዕ። ይልበሱ ቢጦነ ዘሡዕ -(ኢሳ፵፪ -፫። ፵፫ -፲፯ ሥር -ጳኵ)

[2]-(ሦዕከ ትሠውዕ ትሡዕ) ትእዛዝ አንቀጽ፤ ስላንድ የቅርብ ወንድ። ሠዋ መሥዋዕት አቅርብ። ሡዕ ሊተ ወልደከ -(ዘፍ፳፪ -)

ሡጠት -መመለስ አመላለስ ምለሳ ምልስነት።

ሢመት -መሾም ወይም ተሿሚ መኾን ሹምነት፤ አሿሿም። ሹመት፤ ሥልጣን፤ ማዕርግ ጸሎተ መት። ከመ ኢይንሣእ መተከ በመዋዕለ መትከ ይሰዐር እምሢመቱ መተ ክህነት አቀምክዎሙ በበ መቶሙ መታት ወሥልጣናት -(ኪዳ ሢራ፲፪ -፲፪። ስንክ -ግን፲፪። ቀሌ። ቅዳ። ነሐ፲፫ -፲፩ ዲድ)

ሢሩይ -(ያን ያት ሪት ርይት) የታለለ ቀለም የገባ፤ ያደፈ የተኵለፈለፈ። ሢሩያነ በምሕረትከ ንጽሕ -(ኪዳ)

ሢራክ [1]-(ካት ዐረ ሺራክ ሥሮኽ) ሢር ማዘቢያ፤ ታን መሥመር ወስፌው ርሳሱ ቀለሙ ያለፈበት፤ ንድፉ ሰንበሩ፤ የቆመው የተጋደመው፤ ወይም ቀለም የሚወድቅበት ተለላው መዛሪያው ወለለ ልቁ አኃዙ ቦቱ ኃዝ ዘበሢራኩ ዘይኤምር ውስተ ይ። አእሚረከ ኃዘ ልቁ ዘበሢራኩ -(መቅ -ወን)

[2]-የጸሎት የመዝሙር ክፍል፤ ቃሉ በመሥመር በመሥመር የተለየ፤ የሚያዜሙት የሚያስተዛዝሉት፤ እንደ ዳዊት ያለ -(መጽ -ምስ ሄርማ)

[3]-የሰው ስም ጥበበ ያሱ ወልደ ራክ። ወኮኑ በመዋዕሊሁ ለሰሎምን እምነቢያት ናታን ወአክያ፤ወሊቀ ካህናት ሳዶቅ ወኮነ ሊቀ ሐራሁ ያሱ ወልደ ራክ ወውእቱ ዘአስተጋብኦሙ መጻሕፍተ ሰሎሞን ወረሰዮሙ ምስተ መጻሕፍተ ወእሉ ሙንቱ ምሳልያት ወተግሣጽ ወጥበብ ወጉባኤ ወማሕልየ መሓልይ ወለኢያሱ ሊቀ ሐዱ መጽሐፍ ዘዕዉቅ ቦቱ ምሉእ ምጥበብ ወዕንቈ ባሕርይ ነገር -( - - -ገ፹)

ሢራይ -(ያት ሱር ሺራእ) ጥሩ ልብስ ሐር ፀምር ክታን ቀለም የገባ የታለለ አልባሲሆን ዘሜላት ወሢራይ። ልቡባን በሢራያት -(ኢሳ፫ -፳፩፳፫። መጽ -ምስ) በሢራይ ፈንታ ሢርዮን ይላል ፍችው ነው -(ገድ -አዳ - -፵፫ -፲፪) ሤራ ዐድማ፤ ክፉ ዱለት

ሢበት -ሽበት፤ ነጭ ጠጕር የርጅና አበባ እርጅና ሽምግልና። በቈለ በቱ በተ ልሂቅ ቅድመ ዘሢበት ተንሥእ ይደልዋ ኩንኖ ለሢበትከ ዘየሐፅኖ ለሢበትኪ -(ሆሴ፯ -፱። ጥበ፪ -፲። ዘሌ፲፱ -፪። ሢራ፳፭ - ሩት፬ -፲፭)

ሢጠት -(ላጥ ) መሼጥ አሻሻጥ ሽጦሽ። ይሁዳ መከረ ለሢጠተ እግዚኡ -(መጽ -ምስ)

ሣሃሊ -(ሊት ልያን ያት) ልበ ነገር ዐላፊ ይቅር ባይ ዐዛኝ ርሩ ሥሂል ሠሀለ ባለው በቀተለ ቤት ግን ሠሃሊ ሠሀልት ያሰኛል

ሣህል -(ላት) ይቅርታ ርኅራኄ ምሕረት ርቅ ፍቅር ይከውን ሣህል ዕሌሆሙ ልቦ ሣህል ለዘያወፅእ ምክረ ቢጹ። ዘበእንቲኣሁ ረከብነ ህሎ -(ሔኖ፩ -፰። ሢራ፲፫ -፲፪ ሮሜ፭ -፲፩) ንዴት ኀሳር ሕርትምና በማለት ፈንታ ሣህል ይላል፤ የመላሽ ስሕተት ነው -(፩ቆሮ -፲፭ -፲፱) ፪ኛም ጽርኡ ምክንያት ያለውን ሣህል ይላል፤ ባለብሉዮች ግን ምግብ ይሉታል -(ሢራ፵፬ -፲፯) እስመ ይኄይስ እምሐዪው ሣህልከ ያለውንም በሕይወት አንጻር ሞት ይሉታል -(መዝ -፷፪)

ሣህሎ -(ሣሀለ ይሣህል) መስፋት መዘርጋት፤ ቀጥ ለጥ ማለት መተካከል መለዘብ መለስለስ እንደ ነትና እንደ መሳል ኾን። ማዘን መራራት ይቅር ማለት መታረቅ ቂምን ድርቅናን ሸካራነትን መተው መጽሐፍ ግን በሣህለ ፈንታ ተሠሃለ ተሣህለ ይላል፤ አያሰኝም። ተሠሃለኒ እግዚኦ ይክል ተሣህሎ። ወለዘሂ ተሣሀልክዎ እሣህሎ -(መዝ -፶። ሢራ፲፮ -፲፩ ሮሜ፬ -፲፭) መንገዱ የቀተለና የባረከ ነው

ሣህር -( አሥህርት ሱር ሣህራ ሸሀር) ሠርቀ ወርኅ ልደተ ወርኅ የጨረቃ ወር መባቻ ረቃ የምትበቅልበት ቀን። በበዓላቲክሙ ወበአሥህርቲክሙ -(ዘኍ፲ -፲። ኢሳ፩ -፲፫ ሆሴ፪ -፲፬። ቆላ፪ -፲፮)

ሣህበበ -(ሠዪብ ሤበ ዐረ ሸሂበ) ሻገተ ተበላሸ፤ ዐመድማ ቅጠልማ ኾነ። ሤበን እይ አባቱ ርሱ ነው፤ ከቅጽሉ በቀር አንቀጹ ይገኝም።

ሣኅት -ዕረፍት ኅድእት ረድኤት ይረክባ ኅተ እሁቦሙ ሣኅተ ስቲተ መድኀኒት -(ማቴ፳፮ -፲፮ ማር፮ -፲፩ ሉቃ፳፪ -፮። ፪ዜና -፲፪ -)

ሣሉሲም -(ዕብ ሻሊሺም) ኀያላን ያርብሓን፤ አለቆች የጦር ዎች፤ ሦስተኛ ማዕርግ ያላቸው፤ ወይም ኀይላቸው ሦስቲዮ የኾነ የተጐነጐነ። ባለብሉዮች ግን ይሉታል። ርእሰ ሣሉሲም -(፩ዜና -፲፪ -፲፰)

ሣልሲት -የቍጥር መደብ፤ የኬክሮስ ፫ኛ። ኣንዱ ሣልሲት ራብዒት ይኾናል፤ ኬክሮስን እይ -(አቡሻ -፲፩)

ሣልሳዊ አው ሣልሳይ -(ዊት ሲት) ሦስተኛ፤ ከሦስት አንድ ሶ። በሣልሳዊ ልደት ምአቡሁ ሀለወነ ተዘምዶ ምስሌሁ። በእንተ ተዋስቦ ሣልሲት። ሣልሲተ -(ቅኔ - - -፮። ሕዝ፵፮ -፲፬)

ሣልስ -(ስት) ሦስተኛ፤ ሦስት በስቲያ ወዲያ ናሁ ሣልሶሙ ዮም እንዘ ይጸንሑኒ። ሣልስት ዕለት ከብካብ ኮነ እስከ ሣልስ ወራብዕ ትውልድ። ትማልመኒ ወሣልስተኒ -(ማር፰ - ዮሐ፪ -፩። ዘፀ፳ -፭። ፩ዜና -፲፩ -)

ሣራሪ (ሪት ርያን ያት) የሚመሠርት መሥራች ሠሪ ፈጣሪ ሣራሪሃ ለምድር ሣራሪሃ ለነፍስ (ኪዳ)

ሣራብ -(ዕብራ) ሳማ ቢ፤ ናጫ አለብላቢት፤ ሲያበዛ ሣራቢም፤ ይላል እስመ ሣራቢም ወአሥዋክ ምስሌከ -(ሕዝ፪ -)

ሣሬት [1]-(ርያት) ሸረሪት፤ ፈታይ አቅጣኝ ዘሣሬት ውእቱ ተመይኖ ብር ፈትለ ሣሬት እንመተ ሣሬት ሣሬት ፈትለ እምነ ዕርቃን ያትረፎ -(ፈላስ። አፈ -ተ፴፬ ቅኔ)

[2]-ሣሬትሸረሪትሠረየ

ሣርኅ -(ኃት) ዝኒ ማሁ ወአርኣያ ሣርኁ እግዚ ሳት -(ዘፀ፳፬ -፲፯)

ሣርኆ ኆት -(ሣርኀ ይሣርኅ ዐረ ሸረኀ ዕብ ዛራሕ) መብራት፤ መጽደል፤ መሸብረቅ፤ መፍለቅ ማንጸብረቅ፤ መንደድ መቃጠል፤ ቦግ ማለት

ሣርሮ ሮት -(ሣረረ ይሣርር ዕብ ሻራር ነግሠ፤ ኀየለ። ያሣድ) መመሥረት፤ አጥልቆ ቈፍሮ መሠረት መጣል፤ ማቆም መትከል፤ ዚያ በኋላ መንደቅ፤ መሥራት፤ መናስ መገንባት ቅደምከ ሣርሮታ ለምድር ረሩ ቤተ -(መዝ -፻፩ ሐጌ፪ -፲፱)

ሣሮን -(ዕብ ሻሮን) ስመ ሀገር፤ የባሕር የወንዝ ዳር፤ ሜዳ ረባዳ፤ ከኢዮጴ እስከ ቀርሜሎስ ያለ በምሥራቅም ዮርዳኖስ ማዶ ሮቤልና ጋድ የወረሱት -(ኢሳ፴፫ -፱። ፩ዜና - -፲፭) ባለብሉዮች ግን ችፍርግ ታናሽ ዛፍ ይሉታል ፍችው አይዶለም

ሣቃዪ -(ዪት ይያን ያት) የሚሣቅይ፤ መከራ የሚያሳይ፤ አስጨናቂ። ሣቃዪተ አህጉር -(፩ዕዝ - -፳፪)

ሣቅዕ -የምድር ማእዝን፤ አንዲት ክፍል ምድር እስመ ደቂቀ ስራኤል ኢነበሩ ውስተ ኵላ ምድር፤ ዳእሙ ውስተ ሣቅዕ ዘውእቱ ማእዘንት ውስተ ኵሉ ሣቅዕ -(ግብ -ሕማ -ገ፶፱ ፻፭)

ሣቅዮ  ዮት -(ሣቀየ ይሣቂ ዐረ ሸቂየ፤ ተጨነቀ) መሣቀይ ማስጨነቅ፤ ማስጠበብ፤ ባለመከራ ማድረግ። እለ ይሣቅዩኒ ሣቀይዋ ወአልሐውዋ -(መዝ -፫። ራእ፲፰ -)

ሣባጥ -(ዕብ ወሱር ወዐረ ሽባጥ) ስመ ወርኅ የዕብራውያን ፲፩ኛ ወር የካቲት -(ዘካ፩ -)

ሣቤቅ -ጽፍቅ ዱር ዐጽቅ ሐረግሰቢቅ ሰበቀ

»ሣእሣእ -መልስ ምላሽ፤ የሚበቃ አፍ የሚያሲዝ ቃል፤ ይልና ጣዕም ያለው የሚደነቅ የነገር ጣዕም ለዛ አጣጣል አሰካክ። ወሰው ውሽን ዋሽንት ማለት ከዚህ ወጥቷል። ሞገሰ ቃሉ ወጣዕመ ነገሩ ወሣእሣአ ፉሁ። ወአንከሩ ሣእሣኦ ሣእሣአ ቃልክሙ። ጥበብ ለርእይ ዳም ለሰሚዕ ጥዑም ለአፍ ሣእሣእ ለከናፍር ሕይ ለአዕይንት -(ሉቃ፬ -፳፪ -፳፮ ኢዮ፮ -፳፮። ቀሌ)

»ሣእሥአ -(ተቀ ) ሰበቀለ ቀለጠፈ ቅልጥፍጥፍ አለ፤ ተባ ረታ ሾለ ሰላ ያንደበት

ሣዕሥዐ -ተባ ቀለጠፈወሢእ ወሥአ ሣእሣእ

ሣዕር -ሣር ቡቃያ፤ የብር ያገዳ እኽል የሚታጨድ ኹሉ ገለባ ቈሻሻ፤ ድርቋ ድርቆሽ፤ ነፋስ የሚወስደው ወብዙኅ ሣዕሩ ውእቱ መካን ሣዕረ ምድር ሣዕር ዘያነሥኦ ነፋስ -(ዮሐ፮ - ዘፀ፲ -፲፪። ኢዮ፲፫ -፳፭)

 -የስፌት ዕቃ ማለቢያ ቄጆ ጮጮ የውሃ የወተት የማር የቅቤ ስልቻ፤ ጠጕሩ ያልተነጨ ያልተመለጠ ቀርበታ ሣዕረ ማይ። ሣዕረ ሐሊብ -(ዘፍ፳፩ -፲፬ -፲፭ -፲፱ መሳ፬ -፲፱)

ሣዕሮ -(ትግሬ) ወገርት፤ ቅጠሉ ሣር የሚመስል

ሣእን -( አሣእን። ዕብ ስኦን ሱር ሴናእ) ጫማ መጫሚያ የውስጥ እግር ቤዛ ክፍት ወይም ኩፍ ፈትሐ ሣእኖ። ይሑርዎ በአሣእን ዘእንበለ ሣእን ፍታሕ ሣእኒከ ታነ ሣእን -(ሩት፬ -፯። ኢሳ፲፩ -፲፭። - ዘፀ፫ -፭። ማር፩ -)

ሣውዕ -(ዓን ዓት) ዝኒ ማሁ ካህን የሚጠብስ የሚያጤስ -(ኩፋ - - -፵፬) በትረ ዋዊ ሣውዕ። ሚካኤል ሣውዕ -(ደራሲ)

ሣጹን -(ናት። ዐረ ሻጹነት። ዕብ ጺንጼኔት፤ የሸክላ ዕቃ) ሣጥን፤ የልብስ የገንዘብ የሬሳ መክተቻ፤ ማኖሪያ የንጨት የብረት እምወርቀ መባእ ዘሣጹን። ገብረት ክልኤተ ሣጹነ ሣጹነ ምዉታን ወቦአት ውስተ ሐዱ፤ ወወልዳ ቦአ ውስተ ካል -( - -፲፯ -፩። ዮሴፍ)

ሤመተ አውሠይመተ -(ሤመ) ሸመተ፤ እኽል ገዛ

ሤራዪ -(ዪት ይያን ያት ረይት) የሚያሤር፤ ሤረኛ ዐድመኛ። የሚያልል ዐላይ ቀለም አግቢ -( - -፴፮)

ሤሬቅ -(ዕብ ሦሬቅ ጽር ሶሬክ) ጥሩ ወይን ዘረ መልካም አስካሉ ሕንባቡ ታላላቅ፤ ጣዕሙ ምቱቅ የኾነ። ባለብሉዮች ግን ስመ ሀገር፤ የወይን ቦታ ይሉታል። ተከልኩኪ ሤሬ ወይን ኅሩይ ዘሤሬቅ። መረ ወይን ዘሤሬቅ -(ኤር፪ -፳፩። ኢሳ፭ -፪። ደራሲ)

ሤርዮ ዮት -(ሤረየ ይሤሪ ይሤሪ) ማሤር መቍረጥ ክተተንና ተሰካተየን እይ ማለል ማቅለም፤ ቀለም ማግባት መንከር ማራስ ማጥለቅ መዝፈቅ ቀብዖ በሕጕሬ ወሤረዮ ለእ ተዐገለ ልብሰ ጸዐዳ ወሤረዮ። ፀምር ዘተጠምዐ በሤርዮ ርዪዮን ለመላትሕኪ በአንብዕ -(ጥበ፲፫ -፲፬ - -፴፭። መጽ -ምስ ማር -ይሥ፲፫)

ሤጥ -(ጣት) ሸያጭ ዋጋ ገንዘብ ገዢ ለሸያጭ የሚሰጠው ዘብዙኅ ሤጡ። ዘእንበለ ጥ። ወሀቦ ለውእቱ መካን። ዚኣሁ። ሤጠ ግንዘት -(ኢዮ፴፩ -፳፬ -መዝ -፵፫ ዜና -፳፩ -፳፭ - -፳፯ )

ሥሁል -(ላን ላት ልት) ይቅር የተባለ ይቅርታ ያገኘ፤ የተማረ። ዕደው ሥሁላን ሥህልት -(ሢራ፵፬ - ሆሴ፩ -፮። -)

ሥሂል -(ሠሀለ ይሥህል ይሥሀል ዐረ ሠሁለ) አው

ሥሒቅ ቆት -(ሠሐቀ ይሥሕቅ ይሥሐቅ። ዕብ ሣሐቅ ሐቅ ዐረ ፀሒከ) መሣቅ መፍካት ማሽካካት ንፈርን መሰቅጠጥ ጥርስን መግለጥ፤ ደስታና ከጨዎታ ብዛት ማየት ከመስማት የተነሣ። ብፁዓን እለ ይበክዩ ይእዜ፤ እስመ ይሥሕቁ አሌ ክሙ እለ ትሥሕቁ ይእዜ ስመ ትበክዩ። ትሥሐቅ ሎቱ -(ሉቃ፮ -፳፩ -፳፭ ሢራ፴ -)

ሥኂት ቶት -(ሥኅተ ይሥኅት ይሥኀት ሠኀተ ይሤኅት ይሥኅት ዐረ ሠከተ ዕብ ሣካት ሱር ሥካት) መሠከት ዝም ዕክም ጸጥ ሠክ ሹክክ ማለት መስማትና ለማድመጥ ለኈሰን እይ ማረፍ ዕረፍት ማግኘት መከራ። እሥኅት እምሕምዝ። ታዕርፍ ምድር ወትሥኀት ምኵሉ ሕማም ይሥኅታ ምድረ ሰዶም ወገሞራ ፈድፋደ እምይእቲ ሀገር -(ኢዮ፲፫ -፲፫ ሱቱ -ዝ፲፩ -፵፮። ማቴ፲ -፲፭) በሥኅተ ፈንታ ተሥኅተ ይላል፤ አያሰኝም። ወበዝየኒ ኢተሥኅትኩ -(ጸሎ -ምና)

ሥሒጽ ጾት -(ሥሕጸ ይሥሕጽ ይሥሐጽ። ዐረ ሸሐጸ። ዕብ ሔጽ) መታበይ መኵራት፤ መድፈር አላቅሙ መናገር መስደብ ማዋረድ መናቅ መሣለቅ። ከሰው ነገር መግባት ጥልቅ ማለት፤ እንደ ወገሜት ዝንብ። ሰሐጠንና ሠጠጠን እይ የዚህ ጎሮች ናቸው ይሥሕጹ ዘእንበለ ዐቅም እለ እንበለ ጥበብ ሥሕጹ ዕለ ትሥጉተ መድኀኒነ ምንት ይሥሕጹ ዕለ ስብሐት መለኮት -(ቄር - ተረ)

ሥህቡብ -(ባን ባት ብብት) የሻገተ ሻጋታ፤ ብልሹ ዐመድማ። ኅብስት ሥህቡብ ወንቁዝ -(ኢያ፬ -፭። ኢዮ፰ -)

ሥህተ -ስሒት ስሕተ።

ሥሕተ -ሳተስሒት ስሕተ።

ሥሕከ -ሻከረሒክ ስሕከ።

ሥሕወ -ተሳበስሒው ስሕወ

ሥሕጸት -(ታት) መናቅ ማቃለል፤ ትዕቢት ድፍረት፤ ቅለት ጠለቅላቅነት፤ የስድብ ኀይለ ቃል ቃለ ሥሕጸታት ያወፅእ ምአፉሁ ወበዘያጽሕ ርእሶ እምሥሕጸታት ዘሰምዐ ሥሕጸታት ላዕለ ርስቶስ -(ቄር -እስት። ጰላ)

ሥሉስ -(ሳን ሳት ልስት) በቁሙ የተሠለሰ ሦስት የኾነ ሦስቲዮ ሥሉሴ። ፈትል ሥሉስ። ቅዱስ ሥሉስ። ሥሉሰ አካል -(መክ፬ -፲፪። ኪዳ። ደራሲ)

ሥላሴ -መሠለስ፤ ሥለሳ ሦስትነት፤ ሦስት መኾን። ኀበ ሀለዉ ሠለስቱ ኤጲስቆጶሳት ይቄድሶ እግዚእነ ሥላሴሆሙ -(መጽ -ምስ) በቁሙ፤ የአካላት ስም፤ ሦስቶች ሦስቶ ሦስቲዮ ሦስት ብቻ፤ ተውሳክና ሕጸጽ የሌለው ዘላለማዊ ሦስት ባንድም በብዙም በወንድም በሴትም ይነገራል። ዓዲ ናቄርብ ዘንተ አኰቴተ ዘለዓለም ሥላሴ። አለብዉኒ ሥላሴ ቀትለ መስተቃትል መጽሐፍ። ሥላሴ እንተ እምቅድመ ዓለ ሀለወት ወኢኮነት በመዋዕል -(ቅዳ -ኪዳ ደራሲ ተረ -ቄር፲፱)

ሥላቅ -(ቃት) በቁሙ፤ ሣቅ ጨዎት ለግጥ ልት ዋዛ ፈዛዛ ዘበት ዘበታ ወዘበሬታ ነገረ ሥላቅ። ሠሐቀ ወሥላቀ ኮንክዎሙ -(ሢራ -፳፫ -፲፫ ኢዮ፲፯ -)

ሥላት -ለግጥ ፌዝ፤ሰልቶ ሰለተ።

ሥልሳ -(ስሳ ስድሳ ሰደሰ) ሠላሳ ወይም ኻያ -(ዐማርኛ)

ሥልስ -ሦስት ጊዜ ሦስት እጅ፤ ሦስት ክፍል ሦስት ብቻ። ወሰገደ ሎቱ ሥልሰ። ትክሕደኒ ሥልሰ። ዘዘርዐ ስድሰ ያአቱ ሥልሰ -(፩ነገ - -፵፩። ማር፲፬ -፪። ኢሳ፭ -) በቁሙ እሳት ያልነካው መባያ፤ እንደ ሰላጣ ያለ ሹሮና ድልኽ ቅባኑግ የመሰለው ኹሉ፤ ሦስትነት ያለው -(ዐማርኛ)

ሥልቅ -ስመ ሀገር፤ በግዳድ የምትባል የባቢሎን ክፍል -( - -)

ሥልጣናዊ -ንጉሣዊ የንጉሥ የጳጳስ ወገን፤ ሥልጣን ያለው ባለሙሉ ሥልጣን። የሹመት ሥራ ዳኝነት። አቅምተ ውሳንያት ሥልጣናውያት ዘፍትሕ -( - -፲፱)

ሥልጣኔ -በቁሙ፤ መሠልጠን ማሠልጠን አሠለጣጠን ሥልጥንና ሥልጡንነት ጠፍተኛነት፤ በሥራ በነገር።

ሥልጣን -(ናት) [1]-በቁሙ ችሎት መብት ሹመት ጌትነት። ሕይወት ወለሞት ሥልጣን ብከ ከመ ዘሥልጣን ቦ። ወሀቦሙ ሥልጣነ መኳንንት ወእለ በሥልጣናት -(ጥበ፲፮ -፲፫ ማቴ፯ -፳፱ -፩። ቅዳ -ኪዳ)

 -ገዥ አለቃ፤ ንጉሥ መልአክ። ሥልጣናተ ሰማይ ሥልጣናት ወኵሉ ይል። መናብርት ወሥልጣናት -(ሔና፹፰ -፰። ፩ጴጥ - -፳፪ ዲድ)

[2]-( ሠላጢን) ሹል ስል መውጊያ፤ የንጨት የብረት ሽብዳ ዐንካሴ ምዥራጥ ሠላጤ ማለት ከዚህ ወጥቷል ኹሉም ዐማርኛ ነው

ሥሙር -(ራን ራት ምርት) የተሠመረ፤ የተወደደ ወብ መልካም። ሥሙር ወኅሩይ ሥሙር ንጉሥ ዐጽቀ በለስ ሥሙር ጥቀ ምድር ሥምርት -(ሮሜ፲፪ -፩። ምሳ፲፬ -፫። ኤር፳፬ - ሚል፫ -፲፪)

ሥምረት -(ታት) መውደድ፤ መወደድ፤ አወዳደድ ውድነት እሺታ ውዴታ፤ ውድ ቍርጥ ፈቃድ ገበርኩ ቅድሜከ ሥምረተከ ሥምረቱ ለአምላክነ ዕሌነ ንበለ ፈቃዳ በሥምረተ ልባ ይኩን ቦቱ ሥምረት -(ኢሳ፴፰ -፫። ባሮ፬ -፬። - - -፲፫ - -፳፬ -)

ሥሡዕ -(ዓን ዓት ሥዕት) የሣሣ፤ ሥሡ ሆዳም፤ ሥሥታም ብእሲ ሥሡዕ ዘኢይጸግብ። ሥሡዐ ልብ። ሥሡዓን በላዕያን -(ሢራ፴፬ - መዝ - መቃ)

ሥሣዔ -መሣሣት፤ መሠሠት፤ ሥሥ ሥሡ መኾን፤ ሥሥት፤ ሥሡነት።

ሥሥዕት -በቁሙ፤ ሥሥት ንፍገት ሆዳምነት እመ ይፈደፍድ ሥሥዕትከ ምርዓት ወዝሙት ወሥሥዕት ያበዝኆ ገብጥ ሥሥዕት ብዙኃን ቀተሎሙ ሥሥዕት -(አፈ -ተ፫ ቀሌ ሢራ፴፯ - -፴፩)

ሥረው -ሥሮች፤ ዥማቶች። ይየብስ ሥረዊሁ። ንተ በምድር ሥረዊሃ -(ኢዮ፲፰ -፲፮። ሆሴ፱ -፲፮)

ሥሩሕ -(ሓን ሓት ርሕት) ያማረ የበጀ፤ የቀና የሰላ የተከናወነ ከመ ሥሩሐ ይኩን ፍኖትከ ገባሬ ሠናይ ኵሉ ፍናዊሁ ሥሩሕ -(ጦቢ፬ -፲፱። ፈላስ)

ሥሩኅ -(ኃን ኃት ኅት) የበራ፤ ብሩህ ጽዱል።

ሥሩዕ -(ዓን ዓት ርዕት) የተሠራ፤ የተበጀ፤ የተዘጋጀ፤ የቀረበ የተጣፈ የተወሰነ፤ የቆመ የተተከለ። ጽጌ ረዳ ሥሩዕ ማእድ ሥሩዕ። ሥሩዕ ወዕቁም። ወሥሩዕ ወርኅ ዓለም -(አስቴ፩ -፮። ሕዝ፳፫ -፵፩። ፩ቆሮ -፲፬ -፵። መዝ -፹፰ )

 -የተመረጠ፤ የተሾመ፤ ኅሩይ ሥዩም፤ ጽዉዕ። ሥሩዕ ጴጥሮስ፤ ሥሩዕ ጳውሎስ -(ቄር)

ሥሩጽ -(ጻን ጻት ርጽት) የሠረጸ የወጣ፤ የበቀለ፤ የለመለመ፤ ለምለም ጨፌ መስክ ወተርእየት ማይ ምዘቀዲሙ ርግዕተ ወሥርጽተ ምድር ይብስት -(ጥበ፲፱ -)

ሥራሕ -ድካም፤ሰሪሕ ሰርሐ።

()          ሥራዕ -(ዓት ዐረ ሺራዕ) የመርከብ ሸራ መጋረጃ መዝርዕ ውረዱ ሥራዐ ወሰቀሱ ሥራዐ ዘይንእስ ሐመር ንተ አልባቲ ሥራዓት -(ግብ፳፯ -፲፯ -፵። ማር -ይሥ፬ -) በመልሕቅ ፈንታ ሥራዕ፤ ሥራዓት ይላል፤ የመላሽ ስሕተት ነው ወአልዐሉ ሥራዓት -(ግብ፳፯ -፲፫)

ሥራይ -(ያት) መድኀኒት፤ የሚዋጥ የሚላመጥ፤ የሚጠጣ የሚቀባ። ሥራይ ዘቀብዕዎ ይጠይዕዎ ሥራየ። ዐቃቤ ሥራይ -(ጥበ፲፮ -፲፪ ኢሳ፩ -፮። ሢራ፲ -)

 -ጥንቈላ ሟርት ምትሀት ዘሥራይ ብእሲሁ እለ ሥራይ ሰብአ ሥራይ መጽሐፈ ሥራያት -(ግብ፰ -፱። ራእ፳፪ -፲፭ ዘፀ፱ -፲፩። - -፲፭)

ሥርቀት -መውጣት፤ አወጣጥ፤ መታየት። ሥርቀተ ፀሓይ ሥርቀተ ከዋክብት። ሥርቀተ ቤዝ -(ዮሴፍ። ጥበ፲ -፲፯ ገድ -ተክ)

ሥርቅ -ስርቆት፤ሰሪቅ ሰረቀ።

ሥርቆ -ሸምቀቆ ገመድ ወጥመድ ቆቃሕ ተሠግረ በቈጽለ አሥርቆ -(በቈጽለ ሥርቆ) ጽል ልጡ ገመዱ፤ ሥርቆ ውሉ ሸምቀቆው -(ሢራ፲፩ -)

ሥርናይ -(ያት) ስንዴ የስንዴ ወገን፤ ዐጃ። አመ ማእረረ ሥርናይ። እክለ ሥርናይ። ኅጠተ ሥርናይ። ሥርናያት -(ዮዲ፪ -፳፮። ራ፴፱ -፳፮ ዮሐ፲፪ -፳፬ ስንክ -ጥር፳፱

           

 -ስንዴ፤ሥዒር ሥዕረ።

ሥርዐት -(ታት) መሥራት፤ መሠራት፤ አሠራር፤ ሥራት፤ ደንብ፤ አገባብ፤ ሕግ ትእዛዝ ዐዋጅ ፍርድ ልማድ፤ የሥራ መንገድ መኰንን ባዊ ይገብር ሥርዐተ ዐቃቤ ሥርዐት ሥርዐተ ዲያቆን ዐቀበ ወኢተዐደወ ንሕነ ወለጥነ ሥርዐተ ንሥተተ ሥርዐተ ሰብሳብ ሥርዐተ ምሥዋዕ። ሥርዐተ ውራኅ ሥርዐተ ጳኵሚስ -(ሢራ፲፮ -፳፮ ፩ዜና -፲፰ -፲፭። መዋሥ አፈ -ተ፰ ጥበ፲፬ -፳፮። ዕብ፱ -፬። ኩፋ -፬። ሥር -ጳኵ)

 -መኖር፤ አናዎር፤ ኑሮ ይኄይስ ሥርዐተ ብሕትውና ምሥርዐተ ማኅበር። ብዙኃን እለ ያስተካብዱ ሥርዐተ ንዴት -(ፊልክ - -ተ፲፰)

ሥርወ ሕሩም -የሹልዳ ዥማት -(ዘፍ፴፪ -፴፫)

ሥርዋጽ -ሽብልቅ፤ስርዋጽ

ሥርው [1]-(ዕብ ሾሬሽ ሱር ሽርሻ። ዐረ ) ሥር ዥማት ወደየ ሥርወ። አኀዘ ሥርወ። ዘኀጺን ሥርወ ክሣድከ ይሌሊ ሥርወ እመሌሊት -(ሱቱ -ዕዝ፰ -፳፯ ኩፋ -፴፯ ኢሳ፵፰ -፬። ብ፬ -፲፪) ሥርውና ዥማት ልዩ ሲኾን፤ በመትን ፈንታ ሥርው ይላል፤ የመላሽ ስሕተት ነው።

[2]-ሥሮች፤ ዥማቶች። ይየብስ ሥረዊሁ። ንተ በምድር ሥረዊሃ -(ኢዮ፲፰ -፲፮። ሆሴ፱ -፲፮)

[3]-መዠመሪያ መነሻ መውጫ መብቀያ ሥርዋ ጥበብ ፈሪሀ እግዚ -(ሢራ፩ - ጥበ፲፭ -፫። ፩ጢሞ - -)

 -የትንቢት መነሻ፤ ትንቢት አንቀጽ የሚነሣባቸው ፊደላት፤ የተአነ ለ፫ መደብ ላ፭ ለአነ፤ ለንሕነ አሥራወ ትንቢት ይባላሉ፤ የይቤንና የየራሳቸውን አፈታት ተመልከት።

[4] ዘር የትውልድ ምንጭ፤ ሐረግ ሥርወ እሴይ ሥርወ ዳዊት ወአንተሰ ምነ ዐቢይ ሥርው። ሥርውኪ ወዘመድኪ -(ኢሳ፲፩ - - ራእ፭ -፭። ጦቢ፭ -፲፬ ሕዝ፲፮ -)

[5] መዠመሪያ መጽሐፍ ሐዲስ የወጣ፤ የተፈጠረ፤ ረቂቅ፤ መዝገብ ቅዱስ መጽሐፍ ብሉይ ሐዲስ መጽሐፈ ሥርው -(ዮሴፍ - -፶፩)

[6]-(ዋን ዋት ሩት) የተነቀለ ንቁል፤ የጠፋ ጥፉ፤ የተተከለ ሥር የያዘ የሰደደ

ሥርየት [1]-ማለል፤ መታለል፤ መነከር ማደፍ -(ዘፀ፳፭ - ፴፫ -፳፫)

[2]:-በቁሙ፤ሰርይ ሰረየ

ሥርጸት -መሥረጽ መውጣት መብቀል፤ አበቃቀል፤ ቡቃያነት -(መጽ -ምስ)

ሥቁይ -(ያን ያት ቅይት) የተሣቀየ የተጨነቀ፤ ሥቃይ የጸናበት። ወትከውን ጽዑረ ወሥቁየ በኵለ መዋዕል -(ዘዳ፳፰ -፴፫)

ሥቃይ -(ያት) በቁሙ ጭንቅ መከራ መቅሠፍት፤ ግፍ ቅጣት። ኣበዝኆ ሕማምኪ ወለሥቃይኪ። ወሣቀዮ ፈርዖን ዐቢየ ሥቃየ። ይትዔገልዎሙ፤ ወይቀንይዎሙ በሥቃይ። ሥቃያተ ኵነ -(ዘፍ፫ -፲፮ ፲፪ -፲፯ ዘፀ፩ -፲፫ና -፲፬። -ድ፮)

ሥቅሡቅ -(ቃን ቃት ሥቅት) የተበሳሳ፤ የተነዳደለ። መሳክዊሁ ሥቅሡቅ ስከ መልዕልት። ወመሳክው ሠናያን ወሥቅሡቃን -(፫ነገ - -፮። ገድ -ላሊ)

ሥቡሕ -(ሓን ሓት ብሕት) የሠባ የወፈረ፤ ወፍራም ደንዳና ከመ ዘእምሥቡሕ ሥቡሓኒሆሙ ልሕድ ወሥብሕት -(መዝ - ፍ፬ -፬። ኢሳ፴፯ -)

ሥባጥ ሥበጥ -ሽባጥ ሽብልቅ፤ ሠላጤ ወሽመጥ፤ -(ዐማርኛ) ጕርሻ ምግብ፤ የበሰለ የተዘጋጀ፤ ወይም ገንዘብ የገንዘብ ሥንቅ፤ የምግብ መግዣ ሥበጠ መብልዕ ልያስ በልዐ ሥበጠ ኅብስት ዘወሀቦ መልአከ እግዚ ወሖረ በኀይለ ውእቱ ክል አርብዓ መዓልተ ወአርብዓ ሌሊተ -(መጽ -ምስ)

ሥብሐት - ሥባት ሥብነት አሠባብ አወፋፈር ወፍር ድንዳኔ

ሥብሕ -(ሓት) ሥብ ጮማ ሞራ ትርፍ ነጭ ሥጋ ላት ወፍር ድንዳኔ ለመሧዕት የሚቀርብ ጥሩ ነገር ኹሉ ሥብሕ ይባላል። ዘእንበለ ይጢስ ሥብሕ። ሥብሐ ከርሡ ወሥብሐ ሊቱ ሥብሐ ሥርናይ -(፩ነገ - -፲፭ ዘፀ፳፱ -፲፫ መዝ -)

ሥቱር -(ራን ራት ትርት) የተሠነተረ፤ ግርፍ፤ ገጣባ።

ሥትረት -መቅደድ፤ መቀደድ፤ አቀዳደድ፤ ግርፋት፤ ቍስል፤ ሰንበር።

ሥኑይ -ያማረ የተዋበ ውብ ሥኑይ ወርጉፍ በሜላት። ወከመ ቤቱ ሥኑይ ወአዳም። ወሢመትክሙኒ ድልው ወሥኑይ -(አስቴ፩ -፮። መቃ -ገ፫ ቄር -) በሥኑይ ፈንታ መሠንይ ይላል ፍችው ንድ ነው መሠንየ ንስሳ መሠንየ ማእሰር። መሠንየ ቃለ ትንቢት -(፩ነገ -፲፭ -፱። ራ፳፪ -፲፮ አርጋ -)

ሥን -(ናት) [1]-መልክ ውበት ደም ግባት ጌጥ ሽልማት፤ ጥራት፤ ጥዳት ጠፍታ በሥንከ ወበላሕይከ ሥነ ስብሐቲሁ። ሥነ ዜና ዘለዓለም ሥና ብእሲት። ትዘኀር በሥነ አልባሲከ -(መዝ -፵፬። ፵፱ ሢራ፱ -፰። ፲፩ -)

[2]-መልካምነት፤ ደግነት፤ በጎነት። ሥነ ምግባሩ። ሥነ ዕዙ -(ሢራ፮ -፲፭ ያዕ፫ -፲፫)

[3]-ፍጥረት፤ አዝርዕት አትክልት፤ እንስሳት አራዊት ምስጢሩ ጌጥ ሽልማት ካለው ይገባል። እሳት አኅለቀ ሥነ ዳም ወሥነ ገዳምኒ ኀቤየ ሀሎ -(ዮኤ፩ -፲፱ና -፳። መዝ -፵፱)

ሥንቅ -በቁሙ፤ የመንገድ መሣሪያ፤ ልብስ ምግብ፤ ገንዘብ። ወአስተዳለወ ሥንቀ ፍኖት ወሀቦ ክልኤተ ምእተ መካልየ ወርቅ ይኩን ሥንቀ ፍኖት። ቍርባን ቅዱስ ሥንቀ ነፍስ -(ኩፋ -፪። ጦቢ፭ -፲፮። ታሪ -ነገ። - -፳፮ -)

ሥንት -(ዕብ ሻይን፤ ሽታን) ሽንት የሽንት ውሃ ፈሳሽ   የመጠጥ ሐሠር ከሆድ የሚወጣ። ሥንት ይስተዩ ሥንቶሙ -(ፈላስ -ገ፴፯ ኢሳ፴፮ -፲፪። ፬ነገ -፲፰ -፳፯) ባማርኛ ግን የቍጥር ጥያቄ ይኾናል፤ ስንት በቁሙ ምን ያኽል ስፍንና እስፍንቱን እይ

ሥዑል -(ላን ላት ዕልት) የተሣለ የተቀረጸ የተፈጠረ ፍጡር ሥዑል ዲበ ረፍት ታስተርእዮሙ ሥዕልታ። ህየ ሀሎ መልክአ ገጹ ሥዑል። እለ ሥዑላን በነደ እሳት -(ሕዝ፰ - ጥበ፮ -፲፯ ቅዳ ሳታት)

ሥዑር -(ራን ራት ዕርት) የሻረ የዳነ የበቀለ የለመለመ ምለም፤ ሣርማ ሣራም፤ ምቹ ቦታ ብሔር ሥዑር መካን ሥዑር -(መዝ -፳፪ ኢሳ፴ -፳፫። ግንዘ) በሥዑር ፈንታ መሥዕር ይላል፤ አያሰኝም።

ሥኡብ -(ባን ባት እብት) ያደፈ የተዳደፈ፤ እድፋም ርኩስ -(ዘሌ፲፭ -፲፮ ፲፰ -፪። ሐጌ፪ -፲፫ ኩፋ -) ቤትኩ ሥኡብየ ሥኡብ ወዘኢኮነ ንጹሕ። ርኩስ ወሥኡብ ውእቱ። ሥኡባነ ፍስ -(ጦቢ፪ -፬። ቅዳ ቀሌ አርጋ -)

ሥኡን -(ናን ናት እንት) የተጫማ ጫማ የለበሰ ወይም የተለበሰ ሥኡናን እገሪሆሙ ወግልቡባን አርእስቲሆሙ -(ታምረ ማር)

ሥዒል ሎት -(ሠዐለ ይሥዕል ይሥዐል። ዕብ ያጻር። ዐረ ጸወረ) መሣል፤ ማስመሰል፤ መንደፍ መበገር። መፍጠር፤ ማስገኘት መቅረጽ ንሣእ ንፋለ ወሠዐል ውስቴቱ ሀገረ የሩሳሌም። ናሁ በእደውየ ሠዐልኩ ረፋተኪ። ዘዘ ይግበሩ ጻሕለ ዘወርቅ ወይሥዐሉ ዕሌሁ ሥዕለ ምድረ ግብጽ በምልኣ ዛቲ ሥዕል ሠዐላ ቃስ ወንጌላዊ ሣለ -(ሕዝ፬ -፩። ኢሳ፵፱ -፲፭ ዮሴፍ። ስንክ -መስ፲) ዘይሥዕሎሙ፤ለሕፃናት በውስተ ማሕፀን እግዚ ፈጠረ ሥጋክሙ ወመንፈሰክሙ፤ ወሠዐለክሙ በክሂሎቱ -(ድጓ። ዮሴፍ)

ሥዒር ሮት -(ሥዕረ ይሥዕር ይሥዐር ዕብ ሣዐር ራደ ታወከ) መብቀል ቡቃያ መኾን፤ መለምለም፤ ማደግ እምነ ዝናም ይሥዕር ሐመልማል -(፪ነገ -፳፫ -)

 -መሻር መዳን፤ መፈወስ መታደስ፤ ባለጤና መኾን፤ የቍስል የደዌ -(ዐማርኛ)

ሥኢብ ቦት -(ሥእበ ሠአበ ይሥእብ ይሥአብ። ሱር ወዕብ ሣኤብ) ማደፍ መርከስ የሩካቤ የሕልመ ሌሊት የገሲሰ በድን። ወለእመ ሐለመ ኤጲስቆጶስ አንስተ ይቅረብ ወኢይትከነስሂ ወአኮ ዘሥእበ አላ በእንተ ብረ ምሥዋዕ -(ኪዳ -ገ፲)

ሥዒዕ ዖት -( ይሥዕዕ ይሥዐዕ ዐረ ሸዐ ነቃ ተበተነ) መግፈፍ መቅረፍ፤ ማብነን መበተን፤ ለማጥራት ለመግለጥ፤ የዐይን የብሌን። ሠዐየን ተመልከት፤ ከዚህ ጋራ አንድ ነው

ሥዓዕ -ግፋፊ፤ ግልፋፊ፤ ብናኝ ርጋፊ። ወድቀ ምነ ምጋሁ ሥዓዐ ቅርፍት -(አዋል)

ሥዕል -(ላት) በቁሙ፤ መልክ፤ የመልክ ጥላ፤ አምሳል፤ ንድፍ ቢጋር በውሃ በመጽሔት፤ በጥልፍ በስፌት፤ ወይም በቀለም በወረቀት ገዝፎ ተጥፎ ከጽቡር ከእብን ከዕፅ ማዕደን ታንጦ ተቀርጦ፤ ተሸልሞ አጊጦ የሚታይ፤ የሚዳሰስ ነገር። ሥዕለ ኪሩብ። ሥዕለ ቤት ሥዕለ ጣዖት። ሥዕላት ወምስላት። ይረቅሙ ሥዕላ ዲበ ልባሲሆሙ አስተርአየ በአየረ ሰማይ ሥዕለ መስተጽዕናን በአፍራሰ ሳት -(፫ነገ -፳፯። ሕዝ፵፫ -፲፪ ዲድ -፳፭ አፈ -ድ፲፪ ዮሴፍ)

»ሥእሡእ -(ኣን ኣት ሥእት) የሰበቀለ ስብቅል ትብ ቀልጣፋ በሊኀ ልሳን ከናፍሪሁ ጥዑም ወአፉሁ ሥእሡእ -(ደራሲ)

»ሥእሣኤ -መሰብቀል አሰበቃቀል፤ ስብቀላ ቅልጠፋ፤ ያንደበት

»ሥእሥእና -ብቅልነት፤ ቀልጣፍነት

ሥዕር ሥዕርና -ሥዕርና፤ -(ዕብ ሥዖራ ዐረ ሸዒር) ገብስ፤ የገብስ ዐይነት ኹሉ ጠመዥ ሌላውም

ሥዕርት -(ታት ዕብ ዓር ሣዐር ሱር ሣዕራ፤ ሥዓርታ ዐረ ሸዕር ሸዕረት) ጠጕር የሥጋ ሣር፤ ቀጫጭን ደቃቅ በቍርበቱ ላይ በዝቶ ጽፍቅ ኹኖ የሚበቅል፤ ራስን ገላን የሚሸፍን የሚያሞቅ የሚያደምቅ፤ ጋማ ጭራ በዝኀ ሥዕርትኪ ወኢአሐቲ ሥዕርትነ ሥዕርት ቀጣን -(ሕዝ፲፮ -፯። ዲድ -፳፭ ፲፫ -)

ሥእበት -(ታት) ማደፍ መርከስ፤ ርኵሰት ርስሐት እድፍ ዘኢኮነ ጹሐ ምነ ሥእበቱ ዘሌሊት አልቦቱ ሥእበት ዘበሥእበት -(ዘዳ፳፫ -፲፩። ዕብ፲፫ -፬። ቀሌ)

ሥእነ [1]-ሳነ ተሳነስኢን ስእነ

[2]-ሠአነ -(ሰንአ ዕብ ሳአን) ተጫ ለበሰ እግሩን ከመጫሚያ ሰካ አገባ አዋደደ አሰማማ ሰንአን እይ፤ የዚህ ጎር ነው መጽሐፍ ግን በሥእነ ፈንታ ተሥእነ ተሠአነ ይላል ያሰኝም። ተሥእነት ኤሣእኒሃ። ተሠአን አሣእኒከ። ተሥኢነክሙ ይለ ወንጌል -(ዮዲ፲ -፬። ግብ፲፪ -፰። ኤፌ፮ -፲፭)

ሥዕይ ዮት -(ሥዕየ፤ ሠዐየ ይሥዒ ይሥዐይ) ማዝራት መበተን መመሸን የምርት። ማጥፋት፤ ማባከን፤ የገንዝብ። ፋስ ይሥዕዮሙ። እለ ጢስ ፍጉገ ይሥዕዩ ትሰድዶሙ በቃልከ ወትሥዕዮሙ በመንፈሰ ይልከ -(ጥበ፭ -፳፬ ፲፩ -፲፱ -፳፩)

ሥኩር -(ራን ራት ክርት) የተገዛ ግዝ፤ የተከራየ የክራይ። መላጺ ሥክርት -(ኢሳ፯ -) ምላጭ የተባለች ሰይፍ ናት -(ሕዝ፭ -) የሻከረ ሸከራ።

ሥውየት -መሸት መብሰል፤ አሻሻት አበሳሰል እሸትነት ሰብዐቱ ሰብል ዘሠዊት ሠረጹ ምአሐዱ ብርዕ ወንኩር ሥውየቶሙ -(ዮሴፍ)

ሥዉጥ -(ጣን ጣት ውጥ) የተመለሰ ምልስ ቅልስ

ሥዉዕ -(ዓን ዓት ውዕት) የተሠዋ መሥዋዕት የኾነ።

ሥዩም -(ማን ማት ይምት) የተሾመ ሹም፤ ንቡር ድልው፤ ቅምጥ ዝግጁ። ሥዩማነ ቤተ እግ ኤጲስቆጶሳት ወባዕዳን ሥዩማን በእንተ ተስፋክሙ ዘሥዩም በሰማያት ስመ ዝንቱ ሥዩም ለድቀቶሙ ወለተንሥኦቶሙ -(ግብ፲፪ -፩። ዲድ -፮። ቆላ፩ -፫። ሉቃ፪ -፴፬)

ሥዩጥ -(ጣን ጣት ይጥ) የተሼጠ የተዋጀ፤ ውጁ መሼጦ። አንሰ ሥዩጥ ለኀጢአት ወለእመ ኮነ ነውር በሥዩጥ -(ሮሜ፯ -፲፬ - -፴፫ -)

ሥጉር -(ራን ራት ግርት) ከወጥመድ የገባ የተያዘ የተዘጋ ዝግ፤ የተዘጋበት የተሸጐረበት።

ሥጋ -( ሥጋው፤ ዋት ሥጋት) በቁሙ፤ ግዙፍ ልሕሉሕ ደማም ደመ ነፍሳም የሕያዋን ገላ የኀሙስና የዐርብ ፍጥረት፤ ባጥንትና ሥር በዥማት የጸና። ለማግሰኞም ፍጥረት ይበገራል ደመወን እይ አምላክ ለኵሉ ዘሥጋ። ደመስስ ዘሥጋ። እስመ ሥጋ ሙንቱ -(ኤር፴፱ -፳፯ ዘፍ፮ -፲፯ ኩፋ -)

 -ሰው የሰው ልጅ የአዳም ዘር፤ በሥጋነቱ ላይ ነፍስ ያለችው ነባቢና ቀዋሚ ፍጥረት ካሉ ገላው እንደ ዐምድ የቆመ እንደንስሳት ያልተጋደመ፤ ከሞተም በኋላ እንደ ግንድና እንደ ሌላው ነገድ ወድቆና ተጋድሞ ፈርሶ በስብሶ የማይቀር ረቆ ታድሶ የሚነሣ። እሰውጥ እምነ መንፈስየ ዲበ ኵሉ ዘሥጋ ቃል ሥጋ ኮነ ወኀደረ ላዕሌነ ዘይሔድስ ሥጋነ ትሑተ ወይሬስዮ ምሳለ ሥጋ ስብሐቲሁ -(ዮኤ፫ -፩። ዮሐ፩ -፲፬ ፊልጰ፫ -፳፩)

 -ወገን ነገድ የቅርብ ዘመድ ልጅ ሚስት። -(ተረት) የሥጋ ራጭ ያጥንት ፍላጭ። ሰብኡ ወሥጋሁ ሐዱ ሥጋ ንሕነ በክርስቶስ ይኩኑ ክልኤሆሙ አሐደ ሥጋ -(ዘሌ፲፰ -፮። ሮሜ፲፪ -፭። ፩ቆሮ - -፲፮)

 -ሬሳ በድን አስክሬን ነፍስ የተለየችው የሞተ የታረደ ድፍ ሥጋየ ዕለ ሥጋቲሆሙ። ላንቱ ሥጋት ይቢታ ዲበ መሳቅሊሆን ይትጋብኡ ሥጋት ኮኑ ጸበል ሥጋ ዘመሥዋዕት። ዐቃቤ ሥጋ -(ዮሴፍ። ዮሐ፲፱ -፴፩። ቀሌ። ሕዝ፵፩ -፵፫። ፩ነገ -፳፰ -)

 -ግዘፍ፤ ግዙፍንት እስመ አኮ ምሳለ ጺን ዘይትሜሰል በኵለንታሁ ትስብእት፤ አላ በሥጋ ባሕቲቱ -(ሃይ -አበ)

ሥጋዊ -(ዊት ውያን ያት) በቁሙ የሥጋ ሥጋማ ሥጋም ግዙፍ። ኵነኔ ዝሙት ሥጋዊ ወመንፈሳዊ። አበው ሥጋውያን ጣውእ ሥጋውያት -( - -፵፰። አፈ -ድ፳፱ - - -) በጋማች ሥጉያ ሥጋ ሸያጭ ባለሥጋ ሥጋ ቤት ሥጋ መልከኛ።

ሥጋዌ -ሥጋነት፤ ሥግና ሥጋ መኾን የሥጋ ባሕርይ፤ መወፈር መግዘፍ። ምስጢረ ሥጋዌ። ዓመተ ሥጋዌ የሱስ ክርስዮስ ፍጹመ ትስብእት ወሥጋዌ -(ደራሲ) በሥጋ ፈንታ ሥጋዌ ይላል፤ የጣፊ ስሕተት ነው፤ ያሰኝም ምስለ ሥጋዌ ዘነሥአ ምኔሃ -(አርጋ -)

ሥግረት -መሥገር፤ ሥግሪያ መሻገር መራመድ፤ አረማመድ እርምጃ፤ አካኼድ እግር አነሣሥ ኈለቈ ሥግረትየ -(ኢዮ፴፩ -)(662) ሥግረት፤ መዝጋት መዘጋት ዝግነት፤ አያያዝ አከባበብ

ሥግው -(ዋን ዋት ጉት) ሥጋ የኾነ ሥጋ የለበሰ ሥጋማ ግዙፍ። እስመ እግዚ ሥግው ውእቱ። አብ ዘኢሥግው -(ቄር - አፈ -ድ፭)

ሥጠት -(ታት) (መቅደድ መቀደድ አቀዳደድ ቀዳድነት ቅድ ሥንጥቅ። ሥጠተ ልብስ ብሉይ፤ ወይከውን ሥጠቱ ዐቢየ -(ማቴ፬ -፲፮)

ሥጡቅ -(ቃን ቃት ጥቅት) የተሠነጠቀ፤ ሥንጥቅ ሠንጣቃ ቀዳዳ ሥጡቅ ጽፍሩ ማእከሉ ምብኳሐ ሃቢ ሥጡቅ -(ሥጡጥ) -(ዘሌ፲፩ -፫። ኢዮ፴፪ -፲፱)

ሥጡይ -(ያን ያት ጢት) የጸነነ የተሳበ፤ የተለወጠ -(ሄርማ)

ሥጡጥ -(ጣን ጣት ጥጥ) የተቀደደ ቀዳዳ ሠንጣቃ ክፍት ሥጡጥ አልባሲሁ። ሥጡጥ መታክፉ በሰይፍ። ዝቅ ሥጡጥ ይለብስ ሥጡጠ ወአጽርቅተ ኵሉ ነዋሚ -(፩ነገ - -፲፪። ስንክ -ጥር፪። ኢያ፱ -፪። ምሳ፳፫ -፳፩) የሾጠጠ ሾጣጣ፤ ሞጥሟጣ

ሥጥቀት -(ላጥ ) መሠንጠቅ፤ መቀደድ ሠንጣቅነት ሥንጥቃት ንቃቃት። ሥጥቀተ ገቦ በመጥባሕት እንተ ሥጥቀተ ረፍት ሥጥቀተ ፈለግ ውስተ መሬት -(ስንክ -ሠኔ፳፯ አቡሻ -፶። ኢዮ፳፰ -)

ሥጥየት -እብደት ስካር፤ ጥጋብ፤ የእብደትና የስካር የጥጋብ ሥራ ስክረት ወሥጥየት -(፩ጴጥ - -)

ሥጹር -(ራን ራት ጽርት) የተሠነጠረ የተከፈለ የተሠነጠቀ ሥጹር ለክልኤ -(መጽ -ምስ)

ሥጻር -(ራት) ሥንጣሪ ሥንጥር ሥንጣቂ ሥጻረ ዕፅ -(ገድ -ተክ)

ሦር -በሬሰውሮ ሰወረ ሶር

ሦቀ -ደገፈሰዊቅ ሶቀ

ሦካዊ -የሾኽ ዐይነት ወገን እሾኻም ሹካ። ሹላፍ እሾኻፍ፤ ሸውከኛ አሻዋኪ ሾካካ።

ሦክ -( አሥዋክ ዕብ ሶክ ሱካ ዐጽቅ ዐረ ሸውክ ሸውከት) ሾኽ እሾኽ የሾኽ ዛፍ። ወግዐኒ አክሊል ዘሦክ ይቀሥሙሁ እምአሥዋክ አስካለ -(መዝ -፴፩። ማር፲፭ -፲፫ ማቴ፯ -፲፮)

ሦጠ -መረሰዊጥ ሶጠ

No comments:

Post a Comment

ማውጫ

ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ