~ለ~

                                 

      [1]-፲፪ኛ ፊደል በግእዝ አልፍ ቤት በአበገደ ስሙ ለውይ ላዊ። ቍጥሩ ሠላሳ፤ አኃዝ ኾን -() ሠላሳ ይባላል።

[2]-(ደቂቅ አገ) በቁም ቀሪ ዘርፍ አያያዥ የዘርፍ ደፊ ተጠቃሽ ወደ አዳማቂ፤ ቀባይ አቀብሎ ሸሽ ይኾናል ልየ ሊተ ለከ፤ ሎቱ ላ፤ ለነ፤ ክሙ ክን ሎሙ፤ ሎቶሙ ሎን ሎቶን እያለ እንደ ይዘረዝራል። ለአበዊነ ለአብርሃም ወለዘርዑ በቁም ቀሪ። ለእግዚአብሔር ምድር በምልኣ ሐማቱ ስምዖን ዘርፍ ኣያያዥ። ለኖኅ ሐመሩ ለአሮን በትሩ ደፊ ኅድጋ መዐት ወግድፉ ለቍጥዓ ተጠቃሽ ን። ተከፍለ ለክልኤ ተሠጠ ለክልኤ ኢትበል ለየማን ኢለፀጋም፤ ወደ። ለእ ርኅበ ጸላኢከ፤ ኀበ ሰማያት፤ አዳማቂ ስብሐት ለእግዚ ኵሉ ለአምላክ ማሰሪያ ሰጭ ወይም አቀባይ። ይደሉ፤ ይትከህል አለበት፤ ምስጢሩ ከየና ከበቁም ቀሪነት ይገባል። ለይትጋባእ ማይ ለታውፅእ ባሕር አቀብሎ ሸሽ የዚህም ምስጢር አዳማቂ ካለው ይገባል። ወአምጽአ ረኀብ ለብሔር ምድር ላይ ትጸሊ ለዝ ሕዝብ ላዕልና በእንተ መኾኑ በመላሾች ስሕተት ነው እንጂ ፍችው ኹኖ አይዶለም ጽርኡም ብራይስጡም ዕለ ምድር በእንተ ሕዝብ ያሉትን ለብሔር ለሕዝብ እያሉ አላገባቡ ጥፈውታል ነባር አንቀጽ ሲኾን ወሎቱ ብእሲት ወውሉድ እያለ ይዘረዝራል ቦቱ ማለት ነው ሊተ ለከ ያለውም ዚህ ኹሉ አፈታት ይፈታል ለኔ የኔ እኔን ወደኔ፤ ልኝ አለኝ አለልኝ ያሰኛል ወሀብከኒ ሊተ ውእቱ ስምዑኒ ሊተ ምጽኡ ሊተ ወይ ልየ ልየ ወይ ሊተ አሌ ሊተ ሊተ ዐርክ ምእመን እያለ ሌላውን ኹሉ ያሳያል። ዝናም መጺእ ቢል ሊመጣ ያሰኛል የለ ስልትና አፈታት በመጻሕፍት ውስጥ ብዙ ነው። -(ዕር፳፩ -፻፲፫ ር፲፩ -ቍ፺፫)

ለሓማ -(ዐረብ) በቁሙ የማዕደናት መጣብቅ።

ለሀሰ -ላሰ ላላሰ፤ለሐሰ።

ለሐሰ -(ዐረ ለሒሰ። ዕብ ወሱር ላሓኽ) ላሰ መሰ በላ ጠጣ ምላሱን አንቀሳቀሰ ረገ አበሰ ከለባት ይልሕሱ ሰሊሁ ሐሱ ከለባት ደሞ ሳት በልዐት መሥዋዕቶ ወለሐሰት መሬቶሂ። ኢትልሐስ መጻብኅተ -(ሉቃ፲፮ -፳፩ ነገ -፳፩ -፲፱ ፲፰ -፴፰። ሢራ -፴፬ -፲፬)

 -መጠጠ መጠመጠ በከመ ይልሕስ ጽሙእ ወይሰቲ እምነ ኵሉ ማይ -(ሢራ -፳፮ -)

 -ደረቀ በተ ላሸ ዛገ ይልሕስ ልሳኖሙ በጽምእ -(ኢሳ፵፩ -፲፯)

 -አሰላ አሾለ፤ አሾተለ፤ ለመላስ ለማልመጥ ወይም በነገር ለመጐነጥ ምስጢሩ የለኈሰ ነው ከልብ ጥቀ ይልሕሶሙ በልሳኑ ልቦ ዘለሐሶሙ በልሳኑ። ከልብ ኢይልሕስ ልሳኖ በቅድሜከ አሳባቂ ነገረ ሠሪ -(ዘፀ፲፩ -፯። ኢያ፲ -፳፩ ዮዲ፲፩ -፲፬)

ለኈሰ -(ልሒስ ለሐሰ ዕብ ላሐሽ) ለኰሰ አቃጠለ፤ ሹክ አለ በዦሮ ነገረ ሾከከ ተንሿከከ በዦ ለመንገር ወይም ለመሰማት፤ እንደቅኔ መሪ እንደ ተመሪ ዘሩ ልሒስ ነው፤ አካኼዱና መንገዱ ሰቈረን ይመስላል።

ለኈሳስ -ሹክታ ሹክሹክታ ምስጢር ቀስታ ይትናገሩ በለኈሳስ። ርአዮሙ በለኈሳስ መጻሕፍቲሁ -(ኢሳ፰ - አስቴ፫ -፲፬)

 -ድጋም ኅቡእ ንባብ ጽራሐ ልብ ኅሊና ልብ ጸሎተ ነፍስ አልቦ ማኅለቅተ ቅኔ በልዑል ዜማ ዘእንበለ በለኈሳስ። ወዓዲ በል በለኈሳስ እግዚኦ መሐረነ ምእተ ጊዜ። ጸመም ዐውያተ ልሳን ዘኢይሰምዕ ወነአምር ለኈሳሰ ልብ -(ስንክ -ግን፲፩ ቄድር። ቅዳ -ግሩ) አልኆሳሰ ለኆሳስ እያለ በሳብዕ ይጥፋል፤ ስሕተት ነው። ግስነቱ እንዳስቈቀወና እንዳስቈረረ ቅጥይ ተቀጥላ ነውና፤ ቀወንና ቈረን እይ

ለሐቀ -(ዐረ ለሒቀ) ለጠቀ አጣበቀ ጣብቆ ያዘ

ለሓኵ -(ኵት ያን ያት) የሚሠራ ሠሪ ፈጣሪ ይብሎኑ ልሕኵት ለሓኵሁ ለሓኵ ወፈጣሪ -(ኢሳ፳፱ -፲፮ አፈ -ድ፪)

ለሓዲ -(ዲት ድያን ያት) የሚያሟርት ማርተኛ፤ ጠንቋይ። ሓዲ በትእምርት ወዘይትኣመር በንቅወተ ርዌ -(ቈስጠ -፲፫)

ለሐጸ -(ዕብ ላሐጽ፤ ለተመ አጣበቀ) ላጠ መለጠ ቀረፈ ገፈፈ። ሥረዊሁ ረምፁ በእሳት ወይልሕጹ -( -ፈ። ዘፍ፴ -፴፯)

ለሐፈ -(ዐረ ለሂፈ) ዘነ ተከዘ ተጨነቀ ዐሰበ መጽሐፍ ግን በለሐፈ ፈንታ ተልሕፈ ይላል ሕተት ነው ውስተ ዘኢኮነ ትካዝከ ትትለሐፍ -(ሢራ፲፩ -)

ለሆሳስ -ሹክሹክታለኈሰ።

()          ለለ [1]-(ሌለየ) ደቂቅ አገባበ በበንና ዘዘ የመሰለ ተጸውዖ ስም በቀር በብትን ኹሉ ዘርዝሮም ሳይዘረዝርም እየገባ እየ ደጊመ ቃል ይኾናል ቁም ቀሪነትም አለው ለለ ዕለቱ፤ ለለ ርእሱ እየለቱ እየራሱ እየለት እየለቱ እየራስ እየራሱ ለለ ሐዱ እያንዳንዱ ለያንዳንዱ አንዱም አንዱም ላንዱም ላንዱም በበ በማለት ፈንታ ይላል የመላሽና የጣፊ ስሕተት ነው ምዕረ ለለ ዓመት ይበክዩ ለለ ዓሙ ወለለ በዓል።

[2]-ዐቢይ አገባብ፤ አመንና እንዘን የመሰለ በኀላፊና በትንቢት ይገባል። ለለ ናገርኩ ዐወዩ በግፍዕ በተናገርኹ ጊዜ ናገር ስናገር -(ኤር፳ -) ወለለ ወለዳ ተባዕተ ቅትላሁ ወንድ ወንድ ሲወልዱ፤ በወለዱ ጊዜ -( - -፳፫ -) ለለ ይወፅኡ ውስተ ጸብእ። ወኮኑ ለለ ይሰምዑ ነገ ያፈደፍዱ ዘፈ -(አቡሻ -፶። ዮሴፍ) -(ዕር፳፩ -፻፲፫)

ለለ አሐዱ ለለ አሐዱ አሐዱ -ለያንዳንዱ፤ ላንዱም ላንዱም፤ ለኹሉ -(ዘፍ፲፪ -)

ለሊነ -(ክሙ ክን ሆሙ ሆን) እኛ ቅላችን፤ ራሳችን ባለቤታችን። ለሊነ ሰማዕነ ወጠየቅነ ዘለሊነ ነአምር አባሁ ወእሞ -(ዮሐ፬ -፵፪። -፵፪)

ለል -ርስ ራስ የራስ ቅል ባለቤት አካል የተገብሮ ዐጸፋ እየኾነ እንደ ውእቱና እንደ ኪያ እስካሥር መደብ ይረባል።

ለልየ -(ሊከ ) እኔ ቅሌ ራሴ ባለቤቴ ለልየ በእዴየ -(ድጓ)

ለመጸ -(ለሐጸ መለጠ) ለመጠ ለምጣም ኾነ ለዘበ ለሰለሰ እብን ይለምጽ ማይ -(ኢዮ፲፬ -፲፱ ገድ - -፲፯)

 -ለመጠ ለማመጠ ረቀ ለማስተካከል ወይም ለማጣ ጐባጣ ለማድረግ።

ለሚድ ዶት -(ለመደ ይለምድ ይልምድ ዕብ ላማድ ዐረ ለመደ ሱር ልማድ፤ ተማረ) መልመድ ማወቅ መውደድ ለማዳ ቤተ ሰብ መኾን ማዘውተር ዘኢትለምዱ ይበጽሐክሙ። ደም ዘይለምዳ አንስት እሙንቱ ይለምዱ ቤቶ -(፩ጴጥ - -፲፪ ዲድ -፴፫። ስንክ -መስ፳፰ ታኅ፯ ፊልጵ፬ -፲፪)

 -መማር ልማድ ማድረግ፤ ፊደል መቍጠር ውቀት መጨመር በማየት በመስማት በነቢብ ገቢር ምስጢሩ ዚያው መልመድ አይወጣም። «ማጥራት ማበጠር የምርት የነገር» ልሳኖሙ ለመደ ተናግሮ ሐሰት ይልምዱ ፀሪፈ ዘከመ ይለምዱ ብዙኃን እለ ቀቲለ ለመዱ ስመ ኢለመዱ አፍራሲሁ ተጻብኦ ምስለ መስተጽዕናነ ጌያት ኢለመደ ይፃእ ምበኣቱ -(ኤር፱ -፭። ፩ጢሞ - - ዕብ፲ -፳፭ ምሳ፩ -፲፰ ዮሴፍ። ፊልክ -፻፲፭) በለመደ ፈንታ አልመደ ይላል ሕተት ነው እለ ያለምዱ ዝሙተ -( - - -፪። ማቴ፳፯ -፲፭)

ለምለመ -(ሐመለ፤ አሕመልመለ። ዕብ ላብሌብ) ለመለመ ረጠበ ቅጠል አወጣ ምከመ ለምለመ አዕጹቂሃ። ይለምልሙ ዕፀው -(ማር፲፫ -፳፰ ተረ -)

 -ራሰ ለዘበ ለሰለሰ ልሕሉሕ ኾነ ከመ እብን ዘኢይለመልም። አእባን እንዘ ይለመልሙ ከመ ሠምዕ ትለመልም ልባቢሆሙ -(ገድ -ተክ ገድ -ላሊ ዮሴፍ)

ለምለም -( ለማልም ዕብ ሊብሉብ) ቁሙ ሐመልማል ለጋ ቀንበጥ ቅጠል ዐጽቅ ለባልብ ውልብልቢት ሙሽራ ወመተሮ ለምለሙ። ርእሶ አንደየ ለምለመ ዕፅ ተሴሰየ፤ ጠለ ገዳም ሰትየ። ሲሳይከ ምለመ ዕፅ -(ሕዝ፲፯ -፬። ድጓ መዋሥ)

ለምንት -ለምን ምንት

ለምአ -ለማ በራለምዐ

ለምዐ -(ለሚዕ ዐረ ለመዐ) ለማ ለም ኾነ ያገር በራ ቍልጭ አለ፤ አማረ ተከናወነ የብርሃን የማዕድን የመልክ የግብር መጽሐፍ ግን በለምዐ ፈንታ ተለምዐ ተላምዐ ይላል አያሰኝም። በእደ ኬንያሁ ይት() ላማዕ ብሩ -(ሢራ፱ -፲፯)

ለምድ -በቁሙ፤ ደበሎ የደበሎ ዐይነት የወታደሮች ጌጥ ሽልማት። አንቀልባ ነት የልጅ ማዘያ -(ተረት) የታዘለ በለምድ፤ የተረገዘ በሆድ።

ለምጻዊ -ለምጣም ለምጥ የወጣበት -(ግጥም) አትቅጣኝ እንደኾን በቍርጥ ፍርድኽ ያለምጣም ምኒልክ ብዬ ልስደብኽ -(የዓለም ጣዕም)

ለምጽ -(ዕብ ጻራዓት ዐረ በረጽ) ቁሙ ለምጥ የቈርበት ደዌ የቍምጥና ወገን  የተላጠ የተመለጠ ዕንጨት የሚያስመስል። ሠረጸ ለምጸ ውስተ ፍጽሙ። ወነበረ ውስተ ለምጽ አስከ ሞተ ናሁ ደጎ ሕብረ ምጹ ዘለምጽ -(፪ዜና -፳፮ -፲፱ -፳፩ ዘሌ፲፬ -)

ለሰነ -(ዕብ ላሼን) ለፈለፈ ባጠረ አፈቸለ ተናገረ፤ ፊት ለፊት። ነገር ሠራ አሳበቀ ባንደበት ወይም በወረቀት መጽሐፍ ግን በለሰነ ፈንታ ለሰነ ይላል ስሕተት ነው ዘእንበለ ጥበብ ይትሌስኑ -(ቄር -) ለዐለን እይ ይህም እንደዚያ ነው

ለሰደ -(ዐረ ለሰደ) መጠጠ መቀ አፈረጠ፤ የጡት የፍሬ ረጋ ጸና የወተት የማር የፈሳሽ።

ለሳኒ -መለስን፤ ለፍላፊ አሳባቂ ምላሰኛ ለሳኝ

ለስሐ -(ለትሐ) ለፈጨቀ አፉን ምላሱን አጮኸ እንጯ እንጯ አለ። ኢትልሳሕ ንዘ ትሜጽር -(ሢራ፵፬ -፲፮) ለስሐና ለትሐ የልሒስ ዘር ናቸው

 -ላሸ ዐለጠ ዐልጫ ኾነ ጣዕም ከዚህ የተነሣ ተናቀ ተጠላ ተነቀፈ የምግብ ያንደበት የነገር ወእመሰ ስሐ ምንት ይቄስምዎ ውስተ ፉሁ ለአብድ ይለስሕ ምሳል ከመ ትልሳሕ በእበድከ ስሐ ይልየ ወደከመ በጸሎትከ -(ማቴ፭ -፲፫ ራ፳ -፳። ፳፫ -፲፬ ገድ -ተክ)

ለስኖ ኖት -(ለሰነ ይሌስን ይለስን) መለሰን መምረግ ምርግን ማስተካከል፤ ምላስ የላሰው ማስመሰል የጭቃ። ብሰሰን እይ -(ዐማርኛ)

ለስድ -(ዕብ ልሳድ) ጭማቂ ውጤት -(ደም ወተት) ዕትብት አሰጅ እንግዴ ልጅ ለስታ ለጋ ትኵ ቅቤ ከረጋ ወተት የሚወጣ፤ ዝብድን እይ ሕል ሐሊበ ወይከውነከ ለስደ -(ምሳ፴ -፴፫)

ለሮስ -(ዕብ ላሮስ) ለማራስ ለማረስረስ፤ ለማበቅ ለማበስበስ ለማርጠብ ለመለወስ ለማፈርፈር ለመለፈጥ። ራሶስ ራስ ያሩስ ነውና ርሕሰንና አርሐሰን ለፈጸን እይ -(ሕዝ፵፮ -፲፬) ዳግመኛም ለሮስ በማለት ፈንታ ለለዊስ ይላል ፍችው አንድ ነው

ለሮን -(ጽር ላሮስ ሮማይ ላሩስ ዕብ ሻሓፍ) የወፍ ድምፁና መልኩ ደስ የሚያሰኝ፤ ደረቱ ብጫቴ ወርቅማ -(ዘሌ፲፩ -፲፮። ዘዳ፲፬ -፲፭) ባለብሉዮች ግን ይብራ የባሕር አሞራ ይሉታል

ለቀመ -(ዐረ ለቀጠ ዕብ ላቃጥ) በቁሙ ሰበሰበ አከማቸ -(ዐማርኛ)

ለቀሠ -ዐዘነ አለቀሰለቀሰ።

ለቀሰ -(ትግ ለቅሰ። ዐረ ለቂሰ) ዐዘነ ተጨነቀ አለቀሰ እንብ አፈሰሰ ብራይስጡ ግን ላቄሽ ብሎ ለቀመ ቃረመ ሰበሰበ ይላልና በዚህ ዘይቤ ሲፈቱት ልቅሶኛ መጥራትን አልቅሱኝ ማለትን ያሳያል በከየን እይ

ለቀቀ -(ዐረ ለቀ ዕብ ላቃህ) መታ ጸፋ ገረፈ ዘዘ ይልቅቅዎ ወይኅምይዎ ውስተ ዘነበ ፈረስ ወያዑድዎ ውስተ ሀገር -(ስንክ -ኔ፲፬) ፪ኛም አስረው ይተዉት ዘንድ ያሰኛል

ለቀወ -አቀጠለ ቅጥይ አወጣ፤ የሣር የቅጠል የማሽላ

ለቀወ ለቀየ -(በቂው በቀወ) ለቀቀ አላቀቀ ዛጋ አፋሸገ ከፈተ ፈታ፤ የአፍ የቍልፍ መኑ ልአክሙ አርምሞ መኑ ለቀዎ ለአፉክሙ ከመ ትንብቡ ዘንተ መኑ ገበረክሙ ተናግሮ -(መጽ -ምስ) ወና ተወራራሾች ስለ ኾኑ በዘረወ ፈንታ ዘረየ እንዲል፤ በለቀወም ፈንታ ለቀየ ይላል፤ ሥሩና ምንጩ በቀወ ነው። ጐድጐደ፤ ወሶበ አልቦ ዘያወሥእ ለቀየ ወቦአ ውስተ ጽርሕ -(ዮዲ፲፬ -፲፭)

ለቀየ -ለቀቀ ከፈተለቀወ።

ለቀደ -ለቈደ አሰረ የምላስ ለገደ የጕረሮ

ለቂቅ ቆት -(ለቀ ለቀቀ ይለቅቅ ይልቅቅ። ለቀወ በቀወ ዕብ ላቃቅ ላቅሌቅ ላሰ ሞለቀቀ) መልቀቅ መክፈት። መተው መስደድ -(ዐማርኛ)

ለቂድ ዶት -(ለቀደ ይለቅድ ይልቅድ። ዕብ ላካድ) መያዝ እጅ ማድረግ ፈልጎ ማግኘት ይዞ ማሳየት። ዘይሌቅድ ብዕለ ንበለ ንዋይ ወግርማ እንበለ ሢመ ወኀይለ እንበለ ዕደው -(ፈላስ -ገ፳፮)

ለቃሒ -(ሒት ሕያን ያት) የሚያለቃ አለቂ፤ አበዳሪ ወለእመ ኀለፈ ይደልዎ ለለቃሒ ከመ ይምልክ ዘአኀዘ በቍዔተ ቃሔ -( - -፳፯)

ለቅሀ -አለቃ አበደረለቅሖ ለቅሐ

ለቅሖ ሖት -(ለቅሐ ይሌቅሕ ይለቅሕ ዕብ ላቃሕ ወሰደ) ማለቃት ማበደር መስጠት ማስተማር ትርፍ ለማግኘት ኋላ ለመቀበል በደረንና ተበድረን እይ እመ ለቃሕከ ብሩረ ለነዳይ ኢትለቅሖ ለዘይብዕለከ ብዙኃን እለ ይሌቅሑ ወዘኢለቅሐ ወርቆ ርዴ -(ዘፀ፳፪ -፳፬ ራ፰ -፳፪ ፳፱ -፯። መዝ -፲፬)

ለቅለቀ -(ለቂቅ፤ ለቀ) ለቀለቀ ቀባ፤ መረገ ዘጋ ደፈነ፤ የቤት የዐዘቅት ያውድማ የንቅ የሥንጥቅ። ኢገብአ ውስቴቶሙ ማይ ወለቅለቅዎሙ በዐረር -(አዋል -ትርጓሜ። ኤር፪ -፲፫) ጠበ አጠራ የልብስ

ለቅዳ -ቁሙ፤ ቅምሖ ያንቃር የጕረሮ የምላስ በሽታ ሕበጥ ቅምሖ የቀምሐ ዘር ነው

ለቆ -(ዕብ ሌቄሽ) በቁሙ ደኃራዊ ሣር ዳግማይ ቡቃያ ቅጥይ፤ ከቈረጣና ካጨዳ በኋላ በገፍና በብላጊ ዝናም የሚበቅል -(ዐማርኛ)

ለቆታ -(ትግሪኛ) አቅማዳ ልቻ አፋም አፈ ሰፊ ማለት ነው አቅማዳፍ ስልቻፍ እንዲሉ

ለበን -(ዐማርኛ) ለንቦጭ ታችኛ ከንፈር ለበናም እንዲሉ በዐረብ ግን ርጎ ማለት ነው

ለበወ -(ዲቃ ለበበ የበ ለውጥ ነው) ለበመ ልባም ኾነ ልብ አደረገ አስተዋለ፤ ወቀ ተረዳ፤ ጠነቀቀ ለበየን እይ የዚህ መንቲያ ነው ዘትሬኢ ወዘአልቦ ይሌብዎ ዝንቱ። በውኩ ዘትቤ። ንለቡ ቢረ ዕለተ ፋሲካ -(ዳን፱ -፳፫ መዝ -፺፩። ቄር - ዲድ -)

ለበየ -(የለበወ መንቲያ) ልበ ቢስ ኾነ ዘነጋ ተሳሳተ ተደናገረ ጸየፈ ኰለተፈ የቃል ያንደበት እመ እሌቢ ውስተ ነገራት ስረዩ ተ፤ እስመ እለ ይነግሩ እምአፉሆሙ ድንቀተ ወኢቀደሙ ጽሒፈ ዮጊ ይሌብዩ ወኢይክሉ ብዎ ወነገረ ሰርግዎ -(ተረ -ቄር)

ለቢስ ሶት -(ለብሰ ይለብስ ይልበስ። ዕብ ላባሽ ላቤሽ ሱር ልቤሽ ዐረ ለቢሰ) መልበስ መክደን፤ በልብስ ውስጥ መኾን መጐናጠፍ። -(ተረት) ካልበሉ ካለበሱ እንስሳ እንዘ ይለብሱ። ወይለብሱ ብሩሀ ወንጹሐ -(ራእ፲፩ -፫። ፲፭ -) በለብሰ ፈንታ ተለብሰ ተላበሰ ይላል ሕተት ነው። ተለበሲ አልባሰኪ። አኮ በተለብሶ ልባስ ዘብዙኅ -(ሩት፫ -፫። ፩ጴጥ - -) ወተላበሰ ንጉሠ ስራኤል ይፈቅዱ ያንሶስዉ ተላቢሶሙ ይመጽኡ ተላቢሶሙ አልባሰ ባግዕ -(፪ዜና -፲፰ -፳፱ ማር፲፪ -፴፰። ሉቃ፳ -፵፮። )

ለቢብ ቦት -(ለበ ይለብብ ይልብብ) መለበብ፤ ልባብ ማግባት፤ ሐስለን እይ። መገረም መጨመት ልበ ቅን መኾን እንደ ተገራ ብት

ለቢን ኖት -(ለበነ ይለብን ይልብን ዕብ ላባን) ማንጣት ነጭ ማድረግ ማጠብ ማጥራት መጥበስ መተኰስ ማጠን ማጤስ የብረት የሸክላ የዕጣን ስኂንን እይ፤ የዚህ ጎር ነው

ለቢጥ ጦት -(ለበጠ ይለብጥ ይልብጥ። ዐረ ለበደ፤ ላጠ ዕብ ላጥ) መለበጥ ማስጌጥ ማልበስ መሸፈን መምረግ መለሰን ወርቅ በጨርቅ በጭቃ በንጨት ገለወን እይ ብእሲ ዘይክል ለቢጠ ወርቅ ወብሩር ወለበጠ እንተ ውስጡ በወርቅ ጽሩይ ወንጌላተ ቢጦ በወርቅ ወበብሩር -(፪ዜና - -፯። -፬። ገድ ዘሚ) መሠንበጥ፤ ማላገጥ ለበጥ ማውጣት -(ዐማርኛ)

ለቢጦን -(ቅብጥ ሊቢቱ) ዐጭር ቀሚስ እጅጌው እስከ ክርን የሚደርስ እጀ ራጣ እንደ ኪታ ያለ የመነኵሴ ልብስ ቢጦን ዘሡዕ -(ሥር -ጳኵ)

ለባሲ -(ሲት ስያን ያት) የሚለብስ ለባሽ ባሴ ምላክ ባሲተ ሞገስ ወግርማ ባስያነ መስቀል -(አረጋ -ድ፳ ደራሲ ቅዳ)

ለባዊ -(ዊት ውያን ያት) ልባም ልብ አድራጊ፤ ተመልካች አስተዋይ፤ ብልኅ ዐዋቂ ንቃቂ ኵሉ ባዊ ይረክባ ጥበብ ፍጥረት ባዊት ወሥጋዊት። ይኩኑ ለባውያነ ወንቁሃነ መናፍስት ባውያት -(ሢራ፲፰ -፳፰ ግንዘ። ዮሴፍ። ጥበ፯ -፳፫)

ለባዪ -(ዪት ይያን ያት) ልበ ልበ ቢስ ደፋር፤ አፉ እንዳመጣ የሚናገር

ለባጢ -(ጢት ጥያን ያት) የሚለብጥ ለባጭ

ለቤሳት -(ጽር ሌቢሲ) ጽህርት የብረት ድስት በገ ፈጅ ወይም ፈጅ -(፪ዜና -፴፭ -፲፫)

ለብሐ -(ዐረ ለበከ) ቀላቀለ ደላለቀ የዕቃ። ለወሰ አቦካ ሠራ የጭቃ። ለሐኰን እይ

ለብሓ -ሸክላ ተቦካ የሚሠራ ዋየ ብሓ -(መዝ -)

ለብሓዊ -(ዊት ውያን ያት) የሸክላ ወገን የሸክላ ይነት ሸክለኛ ሸክላ ሪ፤ ጠቢብ ገራህተ ብሓዊ። እሉ ሙንቱ ብሓውያን -(ማቴ፳፯ -፯። ዜና - -፳፫ ሮሜ፱ -፳፩)

ለብሕ -ቅልቅል ድብልቅ ጭቃ

ለብዎ -ዝኒ ማሁ። ለብዎ ወአእምሮ -(ምሳ፪ -)

ለተመ -(ዐረ ለተመ፤ ቀጠቀጠ) ቁሙ መታ ገጨ ወገጠ ፈተገ ኅፅቦ ርዶ አወጣ፤ ዐሸ በቀ የቈሎ የሸት ለዶቄትም ይኾናል ፈጸን እይ። መለተም በግና ፍየል ውጊያ የመጣ ነው።

ለታሒ -መልትሒ የሚጐርሥ የሚጐነጭ ታች ላማጭ።

ለታት -(ለታቲ ቲት ትያን ያት) በቁሙ ለታታ ልታፋ፤ ክቡደ ልሳን ድዳ አጥርቶ የማይናገር ወለታት ውእቱ ሙሴ -(ተረ -ቄር፪)

 -ለክላኪ፤ አለክላኪ፤ በምላሱ ውሃ የሚልስ የሚጠጣ -(ገድ -አዳ)

ለትሐ -(ለስሐ) ጐረሠ አላመጠ ተጐነጨ ተጕመጠመጠ፤ ንጩን አሳበጠ። ከተተ አገባ፤ ልብስን በሣጥን ወይም ሰውነትን በልብስ በቀሚስ። መክተትና ማግባት መጕረሥና ከመጐንጨት ጋራ ይሰማማል፤ ምስጢሩ አንድ ነው። ለትሐና ለስሐም አኀው ናቸው።

ለትቶ ቶት -(ለተተ ይሌትት ይለትት ላዕልዐ ዐረ ለትለተ) መለተት፤ መኰልተፍ መኰላተፍ፤ ታታ መኾን ያንደበት። ለትቶ የሕፃናት ነው ልተፈንና ላዕልዐን እይ መጽሐፍ ግን በለተተ ፈንታ ተለተተ ይላል ሕተት ነው ወዝንቱ ሕፃን ይትሌተት በግዕዘ ሕፃናት ወቦ አመ ይነብብ በነገር ጽኑዕ ከመ ወሬዛ ዘዕሥራ ዓመት እንዘ ይትሌተት ልሳኑ በሥርዐተ ደቂቅ -(ገድ -ተክ መጽ -ምስ)

 -መለክለክ ማለክለክ ምላስን መጐልጐል ውሃን በምላስ ማንካ መጨለፍ መጠጣት የውሻ የድመት የአራዊት -(ገድ -አዳ) መድከም መልፋት መታከት የኀይል የጕልበት -(ዐማርኛ)

ለነ -ለኛ የኛ እኛን ለከ

ለንጳስ -(ጽር ላምፒስ ላፒድ) የእሳት ላንቃ ነበልባል ምላሱ ውልብልቢቱ ወይም ችቦ ፋና ቀንዲል። ብርሃን ዘለንጳስ ጣሕተ ራኄ ለንጳስ -(ዘፀ፳ -፲፰ ደራሲ) ባለቅኔዎች ግን ግእዝ መስሏቸው፤ ለንጰሰ አበ ለበሰ ብለው ይገሱታል፤ ምስክር የለውም።

ለንጳኔ ላምጴኔ -ላምጴኔ -(ጽር ላምፒኒ ዕብ ማዕጋል) ረገላ ወይም ስፈር የስፈር ቦታ ራዊት ጉሡን ከቦ የሚሰፍርበት ባለብሉዮች ግን ዐልጋ ድንኳን ይሉታል -(፩ነገ -፳፮ - -)

ለንጽ ለንጼዎን -ለንጼዎን -(ጽር ሌንቲዎን) የሥራ ልብስ መክፌ ማጠቆ። ከፈየን እይ ባለሐዲሶች ግን ዝናር ይሉታል መክፌ ለንጽ መዝመዘ በለንጽ ነሥአ ለንጼዎነ ወኀፀበ እግ ርዳኢሁ -(ዮሐ፲፫ - -፭። መዋሥ) መክፌና ለንጽ ናቸው መክፌ ብቻ ይበቃ ነበረ ለንጽ እንዲያው በከንቱ ተጨምሯል፤ ኮሬ ሙራዱን እይ ይህም እንደዚያ ነው

ለዐት አው ላዓት -አው ላዓት፤ ቁሙ ላት፤ የበግ ዥራት። ቅጠል የበግ ላት የሚባል። ውላጋ እጀታ የሰይፍ የካራ የነፍጥ ወአብአ ሎቱ አስከ ዓታ -(መሳ -፳፪)

ለዐከ -ላከ ሰደደልኢክ ለአከ

ለዓለመ ዓለም -ዝኒ ማሁ፤ ለዘላለም ይህ ግን ዕጥፍ ድርብ ቃል ስለ ኾነ፤ ተለይቶ ፍጻሜ ለሌለው፤ ለማይጨረስ ይነገራል ኢይጠፍእ ለዝሉፉ ወለዓለመ ዓለም። ወደምሰስከ ስሞሙ ዓለመ ዓለም። መንበርከ እግዚኦ ለዓለ ዓለ -(ሢራ፳፬ -፱። መዝ - -)

ለዓለም [1]-ድንት፤ ዓለም፤ ዐልሞ ዐለመ

[2]-(ዕብ ልዖላም) ለወትሮ ለዘላለም። ለዝሉፋ ዘልፈ ወትረ በኵሉ ጊዜ በኵሉ መን። ፍጻሜ ላለውም ለሌለውም ኹሉ ይነገራል እንደ እስከ ው። ፍጻሜ ላለው ሲነገር ምድርሰ ለዓለም ትቀውም ኢይትሀወክ ለዓለም እነብ ቤተከ ዓለም ይላል -(መክ፩ -፬። መዝ -፳፬) ወፍጻሜ ለሌለው ሲነገር ቦኑ ለዓለ ሐዩ ቦኑ ለዓለም ይነብር መዐቱ። አኮ ዓለም ዘእትመዐፅ ወይነግሥ ቤተ ያዕቆብ ለዓለም -(ኢዮ፯ -፲፮ ኤር፭ -፭። ኢሳ፳፰ -፳፰ ሉቃ፩ -፴፫)

 -አካቶ ፈጽሞ በውነት መቼም መች። አንሰ ኢየዐልወከ ግሙራ ባለው ለዓለም እንዲል -(ማቴ፳፮ -፴፫) ኢይትሀወክ ለዓለም ያለውም እንደዚህ ሊፈታ ይቻላል።

ለኣኪ -(ኪት ክያን ያት) የሚልክ ላኪ ሰዳጅ

ለዓሊ -(ሊት ልያን ያት) ላይ ላይ የሚል ከፍ ከፍ ባይ ወደ ላይ የሚያርግ የሚወጣ ወጣ

ለከ -ላንተ

()          ለከመ -(ይሌክም ይለክም) ለፈለፈ አሳበቀ። ሳበ ጨመረ ከነገር አገባ -(ዐማርኛ)

ለከወ -(ከበወ። ዐረ ከለ፤ ደከመ) ፈዘዘ ቦዘ ደነገዘ፤ የዐይን የአእምሮ። ወብርንነ ዕይንትየኒ ለከወኒ -(መዝ -፴፯)

ለኪእ ኦት -(ለክአ ይለክእ ይልካእ ዐረ ለኪየ፤ ቀነወ) መለካት። መላከክ መቅባት፤ መለጠፍ ማጣበቅ፤ መቀርቀር መቸንከር በሙጫ በምስማር አምጽአ ቅንዋተ ጺን ወለክአ ውስተ ብረኪሁ -(ስንክ -ጥር፭)

ለኪፍ ፎት -(ለከፈ ይለክፍ ይልክፍ) መልከፍ፤ -(መለኰፍ) በጥቂቱ መንካት መድረስ መቅመስ ማግኘት። ይለክፍዎ በአጽባዕቶሙ ኢለከ በበትሩ። ኢይልክፉ ረፍተ ቤት። ርእሳ ትለክፍ ሰማየ። ወኢለከፎሙ ሥቃይ -(ማቴ፳፫ -፬። አስቴ፬ -፲፩ ሕዝ፵፩ -፮። ኩፋ -፳፯ ጥበ፫ -)

ለካኢ -(ኢት እያን ያት) የሚለካ፤ የሚላክክ ለጣፊ ሠዓሊ

ለክአ -ጣፈ ተመ፤ መሰለ መልክ አወጣ፤ በቀለም በቅርጽ። ለካእክዎ ውስተ መጽሐፍ። ወይልክኦ ውስተ መጽሐፍ ክኡ ዝክሮ -(ሢራ፴፱ -፴፪። ኢዮ፲፱ -፳፫ ስንክ)

ለክዐ -ለካ ጣፈለኪእ ለክአ

ለኰመ -(ዐረ ለከመ) መታ ደሰቀ ጐሰመ ረኰመ፤ ገፋ ገጨ መጽሐፍ ግን በለኰመ ፈንታ አልኰመ ይላል ስሕተት ነው ወግበር ስግደታተ ምስለ ልኵሞተ ርእስ ወአንገርግሮተ ዲበ ምድር -(ፊልክ -፻፲)

ለወወ -(ለወየ ዐለወ) መመ ነነ ልበ ክፋ ኾነ ደፈረ ተኰረ፤ በክፉ አየ ከለወየና ከዐለወ ከኹለቱ የተዴቀለ ነው

ለወየ -(ዐረ ለወይ) ጠወየ መጠመ ጠቀለለ ፈተለ አከረረ፤ ቀለሰ አጐበጠ፤ ቈለመመ ጠወየን ተመልከት ሥሩና ምንጩ ርሱ ነው፤ በጠ ፈንታ ገብቷል

ለዊስ ሶት -(ሎሰ ይለውስ ይሉስ ዕብ ሉሽ ሱር ላሽ። ዐረ ላሰ) መለወስ ማቡካት መፈትፈት ማጨማለቅ። ለፈጸን እይ ዚህ ጋራ ንድ ነው ሥኦት ሐሪጸ ወሎሰት። ዊሶሙ ያምጽእዎ ሎሰ ጽቡረ ልምሉመ -(፩ነገ -፳፰ -፳፬ ፪ነገ -፲፫ -፰። ዘሌ፮ -፲፬ ጥበ፲፭ -)

ለዋሕቅ -(ዐረብ) ጳግሜን -(አቡሻ -) እንሰይን እይ

ለዋው -ማማ ክፉ ደፋር ተኳር ቡየ ይን ገጸ ቢስ አኩይ ወለዋው። ሐራውያ ሐቅል ዋው። ከመ ዋው ይመስል ገጹ -(፩ነገ -፳፭ -፫። ነገ -፲፯ -፰። ሄርማ -ገ፳፯)

ለውሕ -(ሓት ዕብ ሉዋሕ ሱር ሉሓ ዐረ ) ሉሕ፤ ሌዳ ዝርግ ሥሥ ጠፍጣፋ ርብ ሳንቃ ሰደቃ ብራና ወረቀት የመጽሐፍ ገበታ ጽሌ ጽላት ውሕ ሐቲ ለውሕ እምዕፀወ ሐመር -(ክብ -ነገ፶፮ - ስንክ -ጥር፲፬)

ለውዝ -(ዕብ ሉዝ ሱር ሉዛ ዐረ ሎዝ) ቁሙ ዕፅ ከርካዕን እይ ዚህ ጋራ አንድ ነው ገውዝ ወለውዝ ተከልከ በለሰ ቦኑ ይበቍል ለከ ለው -(ሆሴ፬ -፲፫ መቃ -ገ፭)

ለዚዝ ዞት -(ለዘ ይለዝዝ ይልዝዝ) መልዘዝ፤ መራስ መለስለስ ሐለዚዝን እይ የዚህ ነው ለዛ ላዛ ማለት ዚህ ወጥቷል፤ ምስጢሩም ጣዕምና ውበት ለስላስነት ነው ለዛ የነገር ላዛ የጠጕር ላሑጫ እንደ ማለት ለዛ ቢስ ክቾ ደረቅ ጭንጫ ልጫ

ለይ -ፈትል ቀይ ልብስለወየ

 -ፈትል ልብስ፤ ቀይ ቀለም የገባ። ሰረት ለየ ውስተ እዴሁ መሂ ለበስኪ -(ዘፍ፴፰ -፳፰ ኤር፬ -)

 -ቀይ ቀለም፤ ከጥቍርና ከነጭ ብጫ ልዩነት ያለው የፈትልና የልብስ መንከሪያ። ሕብረ ለይ ፈትሉ ዘለይ። ከለሜዳ ዘለይ -(፪ዜና - -፯። ራ፵፭ -፲፩ ማቴ፳፯ -፳፱)

ለገነ -አቦካ፤ ጋገረ አገነፋ።

ለጕም ሞት -(ለጐመ ይለጕም ይልጕም ላጋም) መለጐም ማጕረሥ በአፍ መወተፍ አፍን መዝጋት ዝም ማሰኘት መከልከል መግአት ንኅንቃ ለነፍስነ ወንለጕማ ፈረስ ኀያል ወድሩክ። ለከናፍር እለ በባ ስብሐታተ ርመሞን ሞት ወለጐሞን በልጓም ዘኢይትበተክ። ልጕም ልሳነከ ትተክዝ ድኅረ። ለጐመ ሰማየ ኢየሀብ ዝናሞ -(አፈ -ተ፴፩ ግንዘ። ፈላስ አርጋ) በለጐመ ፈንታ አልጐመ ይላል ስሕተት ነው ዘኢያለጕሞ ልሳኑ። በንጽሕ ልጐሙ ሥጋሆሙ -(ያዕ፩ -፳፮ ተረ -ቄር፲፱) ለገመ ልግም ልግመኛ ማለት ዚህ ወጥቷል። ፈአመን እይ

ለግርዮን -(ጽር ሊጊሪዮን፤ የዕንቍ ሕብሩ ጥቍር ደባባ ደምማ ወይም ደመርጽማ -(ዘፀ፳፰ -፲፱ ፴፮ -፲፱) ያክንትን እይ

ለግን -(ጽር ላጋኖን) ዕንጐ እንደ ጣቢታ ያለ ሥሥ ረቂቅ ባለብሉዮች ግን አንባሻ ይሉታል -(ዘሌ፪ -)

ለጐተ -(ዲቃ ልገት ወሊግ) ስፋ፤ ጥልቅ ኾነ ማለት ከዚህ ወጥቷል ለገተ ደቀነ አቀረበ ወይም ተለገተ፤ ለመክተት ለመቀበል

ለጢን ኖት -(ለጠነ ይለጥን ይልጥን) ማመልጠን፤ ማስተዛዘል፤ መቀባበል መመላለስ መሪና ተመሪ ወይም ግራና ቀኝ በመኾን የዜማ የንባብ። መላልሶ ማመስገን መለመን፤ መለማመጥ ማቈላመጥ። አንጠየንና አስተብቍዐን በነጠየና በበቍዐ ተራ ተመልከት

ለጥሐ -(ዕብ ላጣህ ሰደበ ረገመ) ለጥ እጅ ነሣ ተገዛ ገበረ ተኛ ተጋደመ ተዘረጋ ለጥ ይበሉ ማለት ከዚህ ወጥቷል።

ለጺቅ ቆት -(ለጸቀ ይለጽቅ ይልጽቅ ዐረ ለጺቀ ለዚቀ ለሲቀ) መለጠቅ መጣበቅ መጠጋት፤ ልክክ ልስቅ ማለት መሰማማት እን ይለጽቅ እስከ ጸቀ ማእስ ሥጋሁ ዲበ ዐፅሙ። ጠግዐ ወለጸቀ ምስለ መንበሩ -(ዘፀ፳፮ -፳፰ ስንክ -መስ፲፬ ግን፮)

ለጺጽ -(ለጸ፤ ለጸጸ) መለጠጥ -(ጥለ) መለጠጥ ለጣጭ ተለጣጭ ልጥጥ መኾን።

ለጽለጸ -(ዐረብ) ተናወጠ ተውለበለበ ወዲያ ወዲህ ላይ ታች ደፋ ቀና አለ ተቅመደመደ፤ የሚዛን የልሳኑና የሰሓኑ ለከይሲም ይኾናል ባለቅኔዎች ግን መዘነ ብለው ይፈታሉ። ለጠለጠ ልጥልጥ አደረገ በልክ በሚዛን -(ዐማርኛ) ዘሩ ለጺጽ ነው

ለጽሊጽ -የሚዛን ምላስ፤ ውልብልቢት ላንሴታ ማእከል ኹኖ ግራና ቀኙን የሚያስተካክል ከመ ለጽሊጸ መዳልው ፍትሐ እግዚ -(ምሳ፲፮ -፲፩ ጥበ፲፩ -፳፫) አንዳንዱ መጽሐፍ በለጽሊጽ ፈንታ ለጽላጺ እንደ ማለት ልጽላጼ ይላል፤ የጣፊ ሕተት ነው

ለጽቅ -ማጣበቂያ መጣብቅ፤ ሙጫ ሙቅ

ለፈቀ -(ትግ ሐባ ለፍቀ ሰፋ ጠቀመ) ነበዘ አጥብቆ ያዘ፤ ቀለመ ቢያጥቡ ይጠራ ኾነ የደም የቀለም የርስሐት። በተነስሖቱኒ ተሰርየ ሎቱ ኀጢአቱ እስመ ደመ መለኮት ዘለፈቀ -(መጽ -ምስ)

ለፈየ -(ፈለየ ጠ፤ ሌለየ) ለየ ፈለ ኹለት አደረገ ትልፍይዎ ለአሐዱ ክርስቶስ ወኢትረስይዎ ለወልድ ወለሥጋ ዘነሥኦ -(ሃይ -አበ) ወዲያ ዲህ ተገላመጠ።

ለፈጸ -(ፈለጸ። ሎሰ) ለፈጠ ለወሰ ዐሸ አበቀ በሰበሰ የዶቄት የበሶ ከፈለጸና ከሎሰ ኹለቱ ሥር የወጣ ነው

ለፊፍ ፎት -(ለፈ ለፈፈ ይለፍፍ ይልፍፍ ዕብ ላፌፍ ሱር ላፍ። ዐረ ለፈ) መለፈፍ መሸፈን፤ መጠቅለል መልፈፍ መለፍለፍ፤ መስበክ ዋጅ መንገር። -(ተረት) የሹም ነፍ አይለፍ አይለፈልፍ። ባፍ ይጠፉ በለፈለፉ መልፋት መድከም የቈርበት የጕልበት።

ለፋፊ -(ፊት ፍያን ያት ፈፍት) በቁሙ የሚለፍ የሚለፈልፍ ባኪ፤ ቅላይ። ባለቅኔዎች ግን ለፈፈ ጻፈ ለፋፊ ጣፊ ይላሉ።

ለፌ -(ጽር ) ወዲህ ወደዚህ ወዲያ ወደዚያ፤ የጊዜ የቦታ ለፌ እማርያም። ለፌ ምጥምቀት፤ የጊዜ እምለፌሂ ወእምለፌሂ። ነጸረ ለፌ ወለፌ፤ የቦቃ -(አፈ -ተ፰ መጽ -ምስ ፩ነገ -፲፬ -፲፮ ዘፀ፪ -፲፪) ዝየንና ሃን ተመልከት

ለፍለፈ -በቁሙ፤ ለፈለፈ ቀባጠረ ነገር አበዛ -(ዐማርኛ)

ሉል -(ዐረ ሉእሉእ) ቁሙ ንቍ የዕንቍ ስም ባሕርይ ከሰደፍ የሚገኝ ነገሥታት እንደ ሎሚና እንደንቍላል የሚጨብጡት በሉሉ በዘውዱ እንዲሉ ብሕረንና ቆቅሐን ነቀን እይ -(አርጋ)

ሉሲፌር -(ሮማይ) የዲያብሎስ ስም ሽፍትነት በፊት የነበረው። ጸዋሬ በር ፍድፉደ ርህ ቤዝ ብሩህ ኮከበ ጽባሕ ማለት ቤዝን እይ -(ኢሳ፲፬ -፲፪) በትቢቱና በኵራቱ ብዛት ጥናኤል ኾነ በኋላ ስሙና ብኵርናው ኮከብነቱ ለዳግማይ ዳም ተሰጥታል -(ዘኍ፳፬ -፲፯ ማቴ፪ -፪። ጴጥ - -፲፬)

ሉባር -የተራራ ስም ላቅ ረዥም ራራ፤ ሐመረ ኖኅ የቆመችበት ወሖረት ታቦት ወአዕረፈት ዲበ ርእሰ ባር ሐዱ እምአድባረ አራራት -(ኩፋ -፭። ዘፍ፰ -)

ሉዓላዊ -(ዊት ውያን ያት) ልዕልና ያለው፤ ላይኛ ከፍተኛ፤ የላይ የሰማይ መሐላ ሉዓላዊ ወማእከላዊ ወዘይቴሐት እምኔሆሙ። ስኬዴሬያት ሉዓላውያት። ኀይላት ሉዐላውያን ረድኤት ሉዓላዊት -( - -፳፪ -፭። ሕዝ፵፪ -፭። አፈ -ድ፫ ተ፲፪) ሉዓላዊ በማለት ፈንታ ላዕላዊ እንደ ማለት ልዑላዊ ወመትሕታዊ ይላል ፍችው አንድ -(ፊልክ -፻፸፭)

ሉዓሌ -ልዕልና ፍታ ምጥቀት ርዝመት ዓሌ ዐቢይ። ያእምር ሉዓሌሁ ለሰማይ -(መክ፲ -፮። ቅዳ -ሕር)

 -ላይ ጫፍ መጨረሻ ደርብ ሰገነት። ዘወረወ ፍሶ መልዕልተ ዓሌ ይመውት ውስተ ዓሌ -(ዮሴፍ። አፈ -ድ፩)

ሉጹይ ልጹይ -(ያን ያት ጺት) የተላጨ ልጩ ልጹያን ጽሓሚሆሙ። እስመ ከመ ሉጹት ይእቲ -(ኤር፵፰ -፭። ቆሮ -፲፩ -)

ሉጺት -ቡሓ መላጣ፤ላጸየ።

ሊሉይ -(ያን ያት ሊት) የተለየ የተለያየ ልዩ ልይዩ ሊሉይ እምነ ብእሲቱ። ተኣኅዎ ሐዱ ፍስ ውእቱ በሥጋ ፍሉጥ ወሊሉይ። ሊሉየ መልክእ ወአካል -(ስንክ። ፈላስ -ገ፲፫ ደራሲ)

ሊሊት -(ዕብ) የሌቶፍ፤ ቀን አዕዋፍ የተለየች ይጥማ ወይም ጕጕ ፊተ ክብ ድመትማ የቀን ዳፍንታም የሌት ዐይናማ በሊሊት ፈንታ ሌሎ ይላል ሌሊቶ ሌሊት ቀኑ ማለት ነው -(ጥሬ -ሰዋ)

ሊላይ -ልየታ፤ ልዩነት፤ መለዮ። ዘእንበለ ፍልጠት ወሊላይ -(መጽ -ምስ)

ሊቀ ጳጳስ -በቁሙ፤ በትረ ያሬክ፤ የጳጳሳትና የኤጲስቆጶሳት አለቃ፤ ደምሳሽ። እሊህም ሦስቱ ሊቃናት፤ ራስና ንጉሥ ንጉሠ ነገሥት እንደ ማለት ናቸው ወይርአይ ሊቀ ጳሳት በእንተ ኵሉ ግብር ወትእዛዝ ዘይገብርዎ ጳጳሳቲሁ ወኤጲስቆጶሳቲሁ ውስተ በሓውርቲሆሙ ዘተሠይሙ ላዕሌሆን -( - -)

ሊቃን ሊቃናት ሊቃውንት -(ልሂቃን ናት) አለቆች ሹማምቶች፤ መምራኖች ሽማግሎች። ሊቃነ ሕዝብ ሰብዓ ሊቃናት መንበረ ሊቃውንት ሊቃናትኒ ወመሓዛት -(ዘፀ፲፰ -፲፪ ዘኍ፲፩ -፳፭ መዝ -፻፮ ፻፵፰)

ሊቃኖስ -ተስዐቱ ቅዱሳን ንዱ ወይም ሊባኖስ ባና ተወራርሰዋል።

 -ማርጀት መላቅ፤ እርጅና፤ ላቂያ ልቅና ብኵርና ረከበት ወልደ በልህቀቲሃ አግብእ ልህቀተከ ዘቅድመ ልደት -(ሉቃ፩ -፴፮። ኩፋ -፳፬)

 -እርጅና፤ የድሜ ብዛት። ውስተ ልህቃነ ዓመታቲሁ -(ፊልክ)

 -ላቂያ ልቅና፤ ብኵርና። ወሀበኩ ልህቃንየ ያዕቆብ -(ኩፋ -፴፮)

ሊቃኦንስጢ -(ጽር ሊካዎኒስቲ) ስመ ሀገር በቱርክ አገር ውስጥ ዚያውም በፍርግያ ክፍል ያለች ታላቅ መዲና -(ግብ፲፬ -፲፩)

ሊቅ [1]-(ቅት ቃን ቃት) ቁሙ ለቃ ታላቅ፤ አባት ጌታ መምህር፤ ሹም አሮጌ ሽማግሌ። -(ተረት) ሊቅ እስከ ደቂቅ ልሂቅና ሊቅ ልዩነቱ ሂን በመጕረድ ብቻ ነው እንጂ ምስጢሩና ፍችው አንድ ነው ባለቅኔዎች ግን ሌቀ ይለይቅ ብለው ይገሳሉ ወዘሰ ብዉሕ ሊቅ፤ ዘውእቱ ሊቀ ጳጳሳት ሊቅት። ሊቃነ ሪት -( - -፶፩። ስንክ -ኅዳ፲፯ ሉቃ፭ -፲፯)

 [2]-በቁሙ አሮጌልሂቅ ልህቀ

ሊቅና -(ልህቅና) ሊቅነት፤ አለቅነት ልቅና ሹመት፤ እርጅና ሢመተ ሊቅና ዘካህናት ሊቀ ጳጳሳት ሊቅናሁ ዕለ መሲሓውያን -(ዮሴፍ - -)

ሊባ -(ጽርእ ዕብ ኔጌብ ዳሮም። ዐረ ጅኑብ) የማእዝን ስም፤ ንኡስ ማእዝን ደቡብ ከዚያውም የደቡብ ምሥራቅ በደቡብና በምሥራቅ መካከል ያለ የባሕር ትይዩና አንጻር ሰሜን ወሊባ ወባሕር ወጽባሕ ውስተ ወጰራልያ ወኮነ ደወሎሙ እምነ ስከ ሐዱ ብር -(ኩፋ -፲፫ ዘዳ፩ -፯። ፴፫ -፳፫ ያ፲፭ -) በሊባ ፈንታ ሊቦስ ይላል፤ ደቡባዊ ማለት ነው

ሊባኖስ -(ጽር ዕብ ልባኖን) ስመ ድባር ነዋኃን እለ በሰሜና ለከነዓን ደጋ ታላላቅ ተራራ ገመገም ከዐቢይ ባሕር በመለስ ከሲዶን እስከ ኤርሞን ተያይዞ ሶርያና በምድረ እስራኤል መካከል ያለ ዛፋም ዕንጨታም ዱራም ደናም፤ የተራሮች ራስ ሰማይ ጠቀስ ውርጭና ረዶ ንደ ሻሽ ሸፍኖት የሚኖር ፍችው ሒት እንደ ማለት ነጮ ወይም ነጫም ማለት ነው -(መዝ -፴፭። ማሕ፫ -፱። ኢሳ፵ -፲፮)

 -የሰው ም፤ ሶርያዊ አንጾኪያዊ ቅዱስ፤ ተስዐቱ ቅዱሳን በፊት የመጣ፤ ደብረ ዐስቦን በስሙ ደብረ ሊባኖስ ያሰኘ። መጣዕ፤ ይስሪን ይባላል -(ስንክ -ጥር፫ ድጓፊልክ -)

ሊቤርጢኖን -(ጽር ሊቤርቲኖን) ግዑዛን፤ ነጾች ነጻዎች ነጻነት ያላቸው ቃሉ የሮማይስጥ ነው ሊቤርታስ ማለት ወጥቷል ይኸውም -(ግዕዛን) ነጻነት ማለት ነው ክርስቶስ በፊት ወደ ሮማ ተማርከው ተሽጠው የነበሩ ይሁድ ከሮም ባርነት ነጻ ስለ ወጡ ሌሎች ኣይሁድ ተለይተው ሊቤርቲኖሩም ተብለዋል ምኵራብ እንተ ስማ ሊቤርጢኖን -(ግብ፮ -)

ሊተ -ለኔ የኔ እኔን

ሊቶስጥሮስ -(ጽር ሊቶስትሮቶስ) የቦታ ም፤ ጸፍጸፍ ማለት ነው መካን ዘስሙ ሊቶስጥሮስ -(ዮሐ፲፫ -፲፫) ኛም፤ ሊቶሶርቶን፤ ሊቶስትሮቶን ይላል ፍችው አንድ ነው -(፪ዜና - -)

ሊጦን -(ጽር ሊታኒያ) መስተብቍዕ ልመና ምልጃ ዝብዘባ ልምጫ ሊጦን ዘሰኑይ ወካዕበ ናስተበቍዕ -(ቅዳ)

ላሓዊ [1]-(ላሐወ) የሚያለቅስ የሚያዝን፤ አልቃሽ ዐዛኝ

[2]-(ላሕ) ልቅሶኛ ሐዘንተኛ የልቅሶ እንባም።

ላሐየ -ተጫወተ አጫወተላህዮ ላሀየ

ላህ -ልቅሶላሕዎ ላሐወ

ላሕ -( ላሓት) ልቅሶ፤ ዘን ቤተ ሕ። ልባሰ ላሕ መዋዕለ ሕ። ገብሩ ዝንቱ ሠለስቱ ላሕ -(ሢራ፳፪ -፮። ፪ነገ -፲፬ - ዘፍ፶ - - ኩፋ)

ላህልህ [1]:-ራሰ ለመሸቀላሕልሕ

[2]:-ላላ ረገበላኅልኀ

ላሕልሐ [1]-(ለሕሐ ሱር ሂትላሕላሕ) ራሰ ረጠበ ልሕሉሕ ኾነ ሎክ ሎክ አለ በሰለ የፍሬ የዕበጥ ዘይሜህር ወኢይገብር ይመስል ገብላ ዘውስቴቱ ማይ ምኔሁ ይሰትዩ ብዙኃን ወይትኀፀቡ ወቦቱ ይላሐልሕ ብር ወለሊሁሰ ይሰቲኒ ወኢይነጽሕኒ ጽሕኒ ምርስሐታቲሁ ወኢይላሐልሕሂ -(ፊልክ -፻፬)

 [2]:-ራሰ ረጠበልሒሕ ለሕሐ።

[3]:-ላላ ረገበላኅልኀ

ላኅልኅ [1]-ራሰ ረጠበ፤ለሒሕ ለሕሐ። [2]- (ራኅርኀ) ላላ ረገበ የገመድ የአውታር የኅሊና። ትዐቀብ ከመ ኢይላኅልኅ መዝርዐ ሐመርነ በአፍቅሮ ውሉድ (አፈ ተ፴፬) ላዕልዐንና ራኅርኀን እይ የዚህ መንቲያ ነው

ላህም -በቁሙ ላምልሕመ።

ላሕም [1]-( አልሕምት ዕብ ልሖም ሥጋ ዐረ ለሕም፤ ሥጋ) በቁሙ ላም ቁም፤ የቀንድ ብት የላም መንጋ የቤት እንስሳ ታርዶ የሚበላ ታልቦ የሚጠጣ ተጠምዶ የሚያርስ። ለዱር እንስሳትም ለጐሽ ላጋዘን ይነገራል፤ ላሕም ያንድነት ስም ነው፤ ተባቱም እንስቱም ታላቁም ታናሹም ላም ይባላል። ዘይቤው ሥጋማ ሥጋም ተዋጊ ቀንዳም፤ በላተኛ ሆዳም ማለት ነው የጠጕሩን ልመት የጠባዩንም ልዝብነት ገርነቱን ገራምነቱን ምሮ ያሳያል ላሕም አእመረ ዘአጥረዮ ሕም ወለደት በግዐ ባግዐኒ ወአልሕምተ። አልሕምት ይመክና ልሕምተ ገዳም -(ኢሳ፩ -፫። ዮሴፍ መዝ -፰። ኢዮ፳፩ - - -፵፬ -) ቁም ማለት ደግሞ ቀዋሚ ቅዉም ቁም ነገራም ደግ ደገኛ ማለት ነው -(ሙሾ ሴቶች ስላ፩ ወንድማቸው) ቁም ናውራው ጥተው ቢድሩት እሸቴ ቀጸላ ይበላል አንዠት። መቼ አየሽውና አንችም እንደ ሌላ የት አንዠት ይበላል እሸቴ ቀጸላ

[2]-የባሕር ጐሽ እንደ ዲኖ ያለ ወሀሎ አሐዱ ላሕም ዘይወፅእ እምአሐዱ ባሕር ጽዮእ በሀገረ ከሪክ ወይቤሉ እስመ የዐርግ ሐዱ ሕም በበ ዓመት ወሶበ የሐውር በሐይቀ ባሕር ይትከፈል ወይከውን ፒሳ ወይሠይጥዎ ለሰብአ ፍራጊያ ይቅብዑ ኪያሁ ቦቱ ሕማሮሙ -( - - -ገ፳፪)

ላህቅ -(ቃን) ዝኒ ማሁ። ወሶበ ሞኦሙ ጸላእቱ ብረ ብልጣሶር ምሳሐ ዐቢየ ለላህቃነ መንግሥጉቱ -( - - -ገ፻፯)

ላህብ -(ባት) ነበልባል ወላፈን ሙቀት ትኵሳት ለብታ ላብ ላበት ወዝ መከራ ጭንቅ ላህበ ነድ ህበ አሳት ህበ ፀሓይ ህበ መዓልት ወሶበ ፈትሖ ማእሰሪሁ ወጠፍኦ ህቡ ቆመ ቅድመ እግዚእነ እንዘ ይገርር -(ጥበ፲፮ -፲፰። ሔኖ ኢሳ፵፱ - ኤር፵፫ -፴። መቅ -ወን)

ላሕዎ ዎት -(ላሐወ ይላሑ ዐረ ናሐ ዕብ ናሃህ ሱር ንሃእ) ማልቀስ ማዘን ማሞሽ መጮኽ መንሰቅሰቅ። ጊዜ ለላሕዎ ወጊዜ ዘፈን ወላሐዉ ሕዝብ እለ ይላሕውዋ ጽዮን። ላሑ ምስለ ዘይላሑ -(መክ፫ -፬። ነገ - -፲፱። ኢሳ፷፩ -፫። ራ፯ -፴፬)

ላሕይ -(ያት) ገጽ ፊት በገጽ ላይ ያለው መልክ ውበት ወዝ ደም ግባት፤ ግርማ ሞገስ። ኢታድሉ ሰብእ እንበይነ ሕዩ። ኢያስሕትከ ሕያ ብእሲት ተደሙ ምነ ሥና ወላሕየ ጻ። ላሕያ ጼወዋ ነፍሱ -(ሢራ፲፩ - ፳፭ -፳፩ ዮዲ፲ -፳፫ ፲፮ -፲፩)

ላህዮ ዮት -(ላሀየ ይላሂ ይላሂ ዐረ ለሃ ለሂየ) መጫወት ማጫዎት ዎታ ማድረግ፤ በእጅ በቃል ማጸናናት አይዞኽ አይዞኽ ማለት። ኀጥአት ዘይላህያ ወአልቦ ዘይላህተኒ -(ሰቈ፩ -፲፯ -፳፩) በላሀየ ፈንታ አልሀየ ተለሀየ ይላል ስሕተት ነው ዐራትየኑ ንጋ ይናዝዘኒ ወያላህየኒኑ ምስካይየ ስመ ዮጊ ይትለሀይ -(ኢዮ፯ -፲፫ ፫ነገ -፲፰ -፳፮)

ላማ -(ዕብ) ለምነት፤ ለምን ስለ ምን -(ማቴ፳፯ -፵፮። ቅዳ -አት)

ላሜዳ -በቁሙ ላይዳ ታላቅ የንጨት መንካ ያውድማ መሣሪያ ነዶው ተበራይቶ ከተመሸነ በኋላ ምርቱን ግርድና ብቅ የሚለዩበት ላዳንም ይህን ይመስላል።

ላሜድ  -(ዕብ ጽር ላምዳ) ስመ ፊደል የአሌፍ ፲፪ኛ -(መዝ -፻፲፰ -፹፬፺፮። ሰቈ፩ -፲፪ - -፴፫። -፲፪) ፍችው ትምርት ወይም ምሁር ማለት ነው

ላባን -(ዕብ) የሰው ስም፤ ጸዐዳ ጽዕድው -(ዘፍ፳፭ -)

ላዕለ -ላይ ወደ ላይ አንበሮ ላዕለ ትኔጽሩ ላዕለ -(አስቴ፫ -፩። ኢሳ፰ -፳፩) ተጽዕነ ዕለ ኪሩቤል። መጽአ ሞት ላዕለ ኵሉ ሰብእ -(መዝ -፲፯ ሮሜ፭ -፲፪) ሲዘረዝርም በጥሬነቱ ዕሉ ልከ ልየ ሎሙ ልክሙ ልነ፤ እያለ በዘመድነት ይረባል። ፪ኛም ደቂቅ አገባብ ስለ ኾነ እንደ ዲበ፤ ዕሌሁ እያለ በባዕድ ይዘምታል -(ዕር፳፩ -፻፱)

ላዕላዕ -(ላኅልኀ) ለነበደ ኰለተፈ ድዳ ኾነ። -(ተረት) አፈ ድዳ ቀንደ ጐዳ መጽሐፍ ግን ተላዕልዐ ይላል ስሕተት ነው እንዘ ይትላዐላዕ በልሳን ወይድሕክ በኒቢበ ደላት -(አፈ ተ፳፯ ያዕ ዘእል)

 -(ዓን ዓት) ድዳ ፍዳዳ ለንባዳ ልታፋ ክቡደ ልሳን። ጸያፍ ወላዕላዐ ሳን አነ። በሃማን ወለጸያፋን ወለላዕላዓን ረሰዮሙ ይትናገሩ ርቱዐ -(ዘፀ፬ -፲። ቀሌ። ኪዳ ያዕ -ዘእል)

ላዕሉ -ላይ ላዩ ላይኛው በላይ ያለው። ዘወረደ ምላዕሉ በሰማይ በላዕሉ ኅሡ ዘላዕሉ -(ድጓ። ዮኤ፫ -፫። ቆላ፫ -)

ላዕላይ -(ዪት ሊት ዊት) የላይ ላይኛ ታላቅ ላዕላይ ማኅደር። ላዕላ ቀመር ሀገር ታሕታዪት ወላዕላዪት ላዕላይ ደወለ ግብጽ -(ቀሌ። መር -ዕዉ ፩ዜና - -፳፬ ጦቢ፰ -)

ላዕል -(ላት) ላይ ላይኛ መጨረሻ ቁመት ላዕል ወታሕት -(ቅዳ። ኤፌ፫ -፲፰) ሲናበብና ሲዘረዘር አገባቦችም ሲጫኑት እንዳወራረዱ ይፈታል፤ ስልቱ ብዙ ነው

ላዕልዐ -(ላኅልኀ) ለነበደ፤ ኰለተፈ ድዳ ኾነ። -(ተረት) አፈ ድዳ ቀንደ ጐዳ መጽሐፍ ግን ተላዕልዐ ይላል፤ ስሕተት ነው እንዘ ይትላዐላዕ በልሳን ወይድሕክ በኒቢበ ደላት -(አፈ -ተ፳፯ ያዕ -ዘእል)

ላእክ -(ክት ካን ) መልክተኛ ገልጋይ ሎሌ። ብድሰ ይሬሲ ርእሶ ላእከ ላእካነ እግ -(ምሳ፲ -፬። ሮሜ፲፫ -)

ላእክት -ገረድ፤ ደንገጥር። ወሀበት ላእክታ ያዕቆብ -(ኩፋ -፳፰)

ላእፍ -ለስላሳ ምግብ የላመ የጣመ ዋጡኝ ዋጡኝ የሚል ወሶበ ተፍእማ ለላእፈ ትስብእቱ ረከበ መቃጥነ መለኮት ዘይሰቍር አንቀሮ -(መጽ -ምስ) ባለመጣፎች ግን ወላፍ ይሉታል።

ላኵዮ ዮት -(ላኰየ ይላኵ) መለጐጥ መጓጐጥ መተንኰስ

ላኳ -(አው ላኴ) ጠብ ክርክር ንዝንዝ ጭቅጭቅ፤ ስድብ። ማእከለ ወላኳ ደም ይቀድሞ ላኳ ወጋእዝ ላኳሆሙ ለአብዳን ያጸምም እዝነ ብድ ምከመ ሰትየ ያበዝኅ ላኳ -(ዘዳ፲፯ -፰። ራ፳፪ -፳፬ ፳፯ -፲፬ ፴፬ -)

ላዊ -የፊደል ስም ለወየ

ላዊ ላውይ -ስመ ፊደል የአልፍ ፲፪ኛ። ጠማማ ቈልማማ ጐባጣ ቅልስ ማለት ነው፤ ጠማምነቱም በኹሉ ነው።

ላይዳ -በቁሙ ላሜዳ፤ለመደ

ላጽቂት -(ዕብ ልጣኣ) ሸለሊት፤ እንሽላሊት የገበሎ ዐይነት ወይም ሣሬት ሸረሪት። ጽቂት ዘበእዴሁ የሐውር -(ምሳ፴ -፳፰)

ላጽዮ ዮት -(ላጸየ ይላጺ። ዕብ ወሱር ጋላሕ ዐረ ማሰ) መላጨት መለጫጨት፤ ጠጕርን ሥጋ መለየት ሥሩ መቍረጥ መጋጠጥ፤ ቈርበቱ እስኪታይ እስኪገለጥ ላጸየ ሥዕርተ ርእሱ ላጸዮሙ መንፈቀ ጽሕሞሙ። ርእሶ ይላጺ -(ኢዮ፩ - ፩ዜና -፲፱ -፬። ሌ፳፩ -)

ሌለየ -ሌሊት ተነሣ ነቃ ተጋ ማለደ ለሥራ ለመንገድ። ለለንና ለልን እይ የዚህ ዘሮች ናቸው።

ሌሊት -( ለያልይ ዕብ ላይል ላይላ ሱር ሌልያ ዐረ ለይል፤ ለይለት) በቁሙ፤ ሌት ሊሉይ እመዓልት ለማ የጨለማ ጊዜ ከሠርክ እስከ ነግህ ከማታ እስከ ጧት ኮከብና ከጨረቃ በቀር ፀሓይ የማይታይበት የዮም እኩሌታ መንፈቀ ዕለት ፲፪ ዓት -(ዘፍ፩ -፭። መዝ፻፫ -፳፩) ዓልተ ወሌሊተ ወአርብዓ ያልየ -(ኢሳ፳፩ -፲፪ ማቴ፬ -)

ሌልዮ ዮት -(ሌለየ ይሌሊ ለፈየ ፈለየ) መለየት መነጠል፤ መነጣጠል ይሌሊ ሥርወ አመሌሊት ፈለጠ ወኢሌለየ ሌለዮሙ ሰራዊት። ይሌሊ ዕርክተ -(ዕብ፬ -፲፪ ሮሜ፫ -፳፫ ፪ዜና -፳፭ - ምሳ፲፮ -፳፰)

ሌዊ [1]-የሰው ስም፤ለየወ።

[2]-(ዕብ) የሰው ስም፤ ኛው የያዕቆብ ልጅ ተላዊ መትልው ልጹቅ መስተላጽቅ ማለት ነው -(ዘፍ፳፱ -፴፬። ኩፋ ፴፩)

ሌዋታን -(ዕብ ሊውያታን) የባሕር ውሬ እንስሳ ዘንዶ፤ ታላቅ ዓሣ ማናቸውም። እንስት ንበሪ ምድርን እንደ ዝናር እንደ ጋን ንበር ወይም እንደ ቀለበት እንዳንባር ዙራ ተጠምጥማ ቅፋ የያዘች የብሄሞት ዘውግ ጣምራው ኹለተኛው ለወየ ነው ሌዋ ዐቃፊ ተጠምጣሚ ታን ዘንዶ ወይም ወርድና ቁመት ግዘፈ ምድር። በተገናኝ የምድር መታጠቂያ  ቅናት መቀነት ማለት ነው፤ ብሄሞትንና ዐንበሪን እይ ወዐቀብከ ደእተ አሚረ ክልኤተ እንስሳ ወሰመይካሁ ለአሐዱ ብሄሞት ወለካልኡ ዋታን ወፈለጥኮሙ በበይናቲሆሙ፤ እስመ ኢይክል ዝኩ ሳብዕተ እድ ሀሎ ማየ ናጌብ ጸዊሮቶሙ ወወሀብካሁ ብሄሞት ሐደ እደ ብስ ወለሌዋታን ሳብዕተ ዴሁ ለርጡብ -(ሱቱዕዝ - -፵፱፶፪)

ሌዋዊ -(ውያን) የሌዊ ወገን፤ ካህን -(ሉቃ፲ -፴፪። ግብ፬ -፴፮)

ሌዋውያን -የመጽሐፍ ስም፤ ኛው ሔረ ኦሪት የሌዋውያንን ሕግና ሥርዐት የሚናገር በዕብራይስጥ ግን ዋይቅራእ ይባላል፤ ጸውዐ ማለት ነው ወጸውዖ እግዚ ለሙሴ ያለውን መዠመሪያ ቃል ያሳያል

ሌዌን -ሌዌን፤ -(ዕብ ዊሎን) ስመ ኃምስ ሰማይ ኢዮር ወይም ጠፈር ኛነቱ ከላይ ወደታች ነው -(አዋል) ማይንና ምጽናዓትን እይ

ሌውቄን -(ጽር ሌፍኪ) ዕፀ ይት ወይራ -(ኢሳ፵፩ -፲፱ ሌዊቄን ኤሌዊቄን ይላል ኹሉም ሕተት ነው።

ሌዎጴጤርያ -(ጽር ሌዎፔትሪያ) ሙጽ ንጊያ ሰፊ ዝርግ ንጥፍ -(ሕዝ፳፬ - -)

ሌጌዎን -(ጽርእ) ሰራዊት ጭፍራ የጦር አበጋዝ፤ የጭፍራ አለቃ። ስድስቱ ሺሕ ጭፍራ ከናለቃው አንድ ሌጌዎን ይባላል -(ማቴ፳፮ -፶፫። ማር፭ -፮። ሉቃ፰ -)

ልሑም -(ማን ማት ሕምት) የላመ የለዘበ ልም ልዝብ የከፋ የባሰ

ልሁብ -(ባን ባት ህብት) የተቃጠለ የጋለ የጋመ፤ የሞቀ ሙቅ። የላበ የወዛ ለብ ያለ ኮነ ሁበ ውስተ ፍቅሮተ እግዚ ዐራተ ኀጺን ልሁብ -(ፊልክ -፹፬። ስንክ -ታኅ፱)

ልሑኵ -(ኳን ኳት ሕኵት) የተሠራ የተፈጠረ፤ ሥር ፍጡር

ልሑይ -(ያን ያት ሒት) በቁሙ ወዛም ደመ ግቡ፤ ያማረ ያጌጠ ውብ ግሩም መልከ መልካም። ብእሲ ልሑይ። ወኮኑ ልሑያነ በብርሃ ቢይ -(ዮሴፍ። አቡሻ) በልሑይ ፈንታ ለሓዪ -(ዪት ይያን ያት) እንደ ማለት ኹሉ ላሕይ ይላል የጣፊና የመላሽ ስሕተት ነው ገጽከ ሕይ ሕይ ዕይንቲሁ ሕይ ጥቀ ራእያ። ሶስና ሕይት ጥቀ ደናግል ላሕያት -(ማሕ፪ -፲፬ ፩ነገ -፲፮ -፲፪ ኩፋ -፳፰ ዳን፩ -፴፩። ዓሞ፰ -፲፫)

ልሑድ -(ዳን ዳት ሕድ) የለደለደ ወፍራም ድልድል ቅምጥል፤ ሥራና መከራ የማይችል ኢትሰመዪ እንከ ልሕደ ወሥብሕተ ንቲ ልሕድ -(ኢሳ፵፯ - -፰። ሚክ፩ -፲፮)

ልሑጽ -(ጻን ጻት ሕጽት) የተላጠ የተመለጠ። ስልብ ጐማዳ

ልሒሕ ሖት -(ለሕሐ ይለሕሕ ይልሐሕ ዕብ ሌሐ ሱር ላሕላሕ) መርጠብ መለዘብ መራስ መለስለስ የገላ የንጨት የቍርበት።

ልሂቅ ቆት [1]-(ልህቀ ይልህቅ ይልሀቅ ዕብ ላሀቅ ሰበሰበ) ማደግ መጐልመስ አካለ መጠን ማድረስ። ብእሰንና ብየን መልከት የዚህ ጎሮች ናቸው ልህቀ ሕፃን ወኀደገ ጥበ ስከ ይልህቅ ወልድየ ሴሎ። ይድዐቶ አስቴር ለንጉሥ በቤቱ ልህቀት -(ዘፍ፳፩ -፰። ፴፰ -፲፩ አስቴ፰ -)

 -መላቅ መብለጥ ላቅ መኾን፤ በኀይል በመጠን በብዛት በዘመን እኁሆሙ ዘይልህቅ ኅትክን እንተ ትልህቅ ለሀቁ ውብዝኁ -(ኢዮ፩ -፲፫ ሕዝ፲፮ -፵፮። ኩፋ -)

 -ማርጀት መሸምገል፤ አሮጌ መኾን። አብርሃኘምስ ወሳራ ልህቁ ጥቀ ወኀለፈ መዋዕሊሆሙ -(ዘፍ፲፰ -፲፩ ፳፬ -፩። ፳፯ -) በልህቀ ፈንታ ተልህቀ ይላል፤ ሕተት ነው እለ ይትለሀቁ ምኔክሙ -(፩ጴጥ - -፩። ኪዳ)

[2]-(ቃን ቃት ህቅት) ኦሮጌ ማግሌ፤ ታላቅ። ይትረከብ ሂቅ ውስተ ቤትከ ልሂቃን ወልሂቃት -(፩ነገ - -፴፪። ዘካ -)

 -ቄስ ካህን መስፍን መኰንን። ላዕለ ሂቅ ትስማዕ ውዴተ ልሂቃነ መንግሥቱ። ምውሉደ ልሂቃነ ገረ ሮሜ -(፩ጢሞ - -፲፬ ስንክ -መስ፪ ፲፯)

ልሂብ ቦት -(ልህበ ይልህብ ይልሀብ ዐረ ለሂበ ዕብ ላሀብ) መንደድ መቃጠል መንበልበል መሞቅ መተኰስ መላብ መውዛት ለብ ማለት ወእምዝ ልህበ ልህበተ ምኔሁ -(መቅ -ወን)

ልሒኵ ኮት -(ለሐኰ ይልሕኵ ይልሐኵ ዕብ ላሐኽ ላሰ ያጻር ሠራ) መሥራት መፍጠር፤ መሣል መቅረጽ የጭቃ የማዕደን። ይልሕኵ እምውስተ ውእቱ ጽቡር አምላከ በአርኣያሁ ለሐኰነ ደዊከ ብራኒ ወለሐኳኒ። ንልሐኵ ውስተ አልባቢነ ተዘክሮ እግ ወፈሪሀ ስሙ -(ጥበ፲፭ -፰። መቃ -ገ፳፪ መዝ -፻፲፰ -አፈ -ተ፳፮)

ልሔም -(ማት ዕብ ሌሔም) ኅብስት እንጀራ ከላመ ለለዘበ ቄት የሚሠራ ሲበሉት የሚልም የሚጥም ፍራታ እን ይእቲ ቤተ ልሔም -(ዘፍ፴፭ -፲፱) ወአምጽኡ ልሔምሙ

ልሔምት -(ታት) ሌማት መሶብ የንጀራ መዝገብ።

ልሕሉሕ -(ሓን ሓት ልሕት) ቁሙ፤ የራሰ ርጥብ፤ ለስላሳ ልዝብ። አብሰሎ ኅቡረ ወገብሮ ሕሉሐ ወአፍአሞ ለከይሲ -(ዳን፲፫ -፳፮)

ልኅሉኅ -(ኃን ኃት ልኅት) የላላ የረገበ ልል ሶበ ይከውን ውታረ መሰንቆ ልኅሉኀ ይጠፍእ ቃናሁ ኢተስሕበ ዘከመ ይደሉ እሉ አኀ ኮኑ ልኅሉኃነ -(አፈ -ተ፳፱ ፊልክ -፶፱)

ልኅላኄ -መላላት መርገብ መድከም መዛል፤ መስነፍ መዝለፍለፍ። በእንተ ልኅላኄ ኅሊናሁ ወአኮሰ በእንተ ድካመ ሥጋሁ ምሀኬት ወልኅላኄ ባል ልኅላኄ ፍረተ ሥጋሁ ብእሲ -(ፊልክ -፪። ፶፬ - - -)

ልኅልኅና -ልልነት ደካምነት፤ ስንፍና። ወይቈርር እንከ ርስነ ጥብዐቶሙ በእንተ ልኅልኅናሆሙ። ዝኬ ውእቱ ልኅልኅና ወአኮ ተቃትሎት -(ፊልክ -፬። ፸፩)

ልሕመ [1]-(ዕብ ላሐም፤ በላ ወጋ ሱር ልሓም፤ ላሰ። ዐረ ለሂመ፤ በላ አጓመጠ) ላመ ደከመ፤ ለዘበ ለሰለሰ የዶቄት የዐይን የጠጕር የቈርበት ቀጥቅጥ ወሕርጽ እስከ ይልሕም -( -)

[2]-ላመ ጸና ባሰ ሰብእሰ አኩይ ወአርዌ ምድር ይልሕም ከየ(ቄር)

ልህሰ -(ልሒስ ለሐሰ) ተጠረገ ጠፋ ታጣ። መሐወኒ እን ኵለሄ ወእልህስ። ወይልህስ እመንበሩ። ትፍህቅ ፍስየ ወትልህስ -(ኢዮ፲፱ - ፳፯ -፳፩ -፲፭)

ልሕሰ -ጠፋ ታጣልህሰ

ልሕቀ -ላቀ አደገልሂቅ ልህቀ

ልህቀት -ማደግ እድገት፤ አስተዳደግ። በእንተ ልደቱ ወልህቀቱ በበ ሕቅ ወሕማማቲሁ ወሞቱ ልህቀቱ በበ ሕቅ ስከ ወርዘወ። ተወክፈ እሙነ ልህቀት ዘበበ ሕቅ -(አፈ -ድ፭። አርጋ። ሃይ -አበ)

 -ማርጀት መላቅ፤ እርጅና፤ ላቂያ ልቅና ብኵርና ረከበት ወልደ በልህቀቲሃ አግብእ ልህቀተከ ዘቅድመ ልደት -(ሉቃ፩ -፴፮። ኩፋ -፳፬)

ልህቃን -ዝኒ ማሁ እድገት እድጊያ እድግ ልህቃነ ልህቀ ዘትስብእት ውእቱ ልህቃን -(ቄር -ጰላ)

 -እርጅና፤ የድሜ ብዛት። ውስተ ልህቃነ ዓመታቲሁ -(ፊልክ)

 -ላቂያ ልቅና፤ ብኵርና። ወሀበኩ ልህቃንየ ያዕቆብ -(ኩፋ -፴፮)

ልህቅና -ልቅና፤ እርግና፤ ብኵርና ታላቅነት። በልህቅናሁ ብደ። ነጺሮ በናእሰ መዋዕሊሁ ወልህቅናሁ -(ፊልክ -፴፩። - - -፫። ኩፋ -፴፮ -፴፯)

ልህኵት -ክላልሒኵ ለሐኰ

ልሕኵት -(ታት) የተሠራች፤ የተፈጠረች ሸክላ ሥጋ ያሙስና ያርብ ፍጥረት ልሕኵት ዘቦቱ ብሰልዎ ሕኵት ንጽሕት። ልሕኵተ እግዚአብሔር። ከዐ ደሞ በሥምረቱ ዕለ ልሕኵቱ -(ዘሌ፮ -፳፩ ውዳ -ማር፯ መቃ -፳፪ ቅዳ) ልኵንትንና ልኵትንትን እይ የዚህ ዘር ነው

ልሕው -(ዋን ዋት ሑት) ያዘነ ያለቀሰ እንብ የፈላበት ሐዘን የመላበት። ለልሕዋን ይናዝዞሙ -(ኪዳ)

ልህየ -ወዛ አማረልሕይ ልሕየ

ልሕይ ዮት -(ልሕየ ይልሒ ይልሐይ ዐረ ላሐ ሱር ልሓእ) መውዛት መቅለጥለጥ፤ ማማር ማሸብረቅ እስመ ትልሒ ይእቲ በሥን እምፀሓይ ሰላም ለገጽኪ ዘጥቀ ይልሒ -(ጥበ፯ -፳፱ ደራሲ)

ልህደ -ተቀማጠለልሕደ

ልሕደ -(ልሕየ) ለደለደ ወፈረ የተልባ ያብሽ የምራቅ፤ የመሰለው ኹሉ አማረ ወየዘረ ተደላደለ ተቀማጠለ። አሟረተ ጠነቈለ በሾኽ በንቅፋት በድምፀ አራዊት በማናቸውም።

ልኅደ -ለደለደልሕደ።

ልሕጽ -(ጻት) ልጥ ቅርፍት፤ ጭረት። -(ተረት) የሺ ፍልጥ ማሰሪያው ልጥ። ልሕጸ ዕዋም። ብሱ ለአ ሙሴ እምልሕጸ ሆሳዕና ወቈጽሉ -(ስንክ -ሐም፲ መስ -)

ልሙዕ -(ዓን ዓት ምዕት) የለማለም ንጹሕ ብሩህ ጽሩይ

ልሙድ -(ዳን ዳት ምድ) የለመደ ማዳ ምሁር ሊቅ ስመ ህበ ኮነ ልሙደ ያውዒ ንስሳ ስመ ኮንኩ ልሙደ ብእሲ ልሙደ ሥላቅ። ኮነ ሙደ በሰኪር -(ጥበ፲፮ -፲፰ ፩ነገ -፲፯ -፴፱። ሢራ፳፫ -፲፭ - -፵፯)

 -የተለመደ የታወቀ ዕውቅ። ካልእሪድእዘ ልሙድ:በንበ፣ሴቀካህናት -(ዮሖ፲ቿ2 ፣፲ቹኛ፣፻5)

ልሙጽ -(ጻን ጻት ምጽት) ለምጻም በራ የለዘበ ልዝብ ለስላሳ ልሙጥ ቀጥ ያለ የተካከለ ባጣ ጐባጣ ሸካራ የሌለው። ኰኵሕ ልሙጽ ፍናወ ጽድቅ ልሙጻት ርዌ ምድር ልምጽት -(ሕዝ፳፮ -፬። ምሳ፪ - ገድ -አዳ)

ልማድ -(ዳት) [1]-በቁሙ ልምድ መል የተለመደ ግብር ኮነ ሎቱ ልማድ ምቅድመ ዝንቱ ትኅድግ ልማደከ ወልማዶሙ ሕዝብ የዐርጉ መልዕልተ ደብር እኩያነ ልማድ ወግዕዝ -( - - -፪። ዮሴፍ ቀሌ ሮሜ፩ -፳፱)

 -ምርት ሕግ ሥርዐት። ወላዲተ አምላክ ኮነት ልማደ ሀለዉ እለ በልማደ ማልክት በእንተ ሥነ ማዳቲሁ በከመ ልማዶሙ -(ቄር - -፯። - ፳፬ -፩። ስንክ -መስ፰) አልብነ ልማድ በማለት ፈንታ ኢንለምድ ይላል -(፩ቆሮ -፲፩ -፲፮)

[2]-የግስ ተውሳክ በቀዳማይ አንቀጽ እየገባ አራቱን አዕማድ የሚለይና የሚያስለይ ተጨማሪ ፊደል እሊሁም ናቸው አስተ አገባባቸውን በየቦታቸው እይ

ልምሉም -(ማን ማት ልምት) የለመለመ፤! የረጠበ የለሰለሰ፤ ልሕሉሕ ርጥብ፤ ደካማ ለስላሳ ልዝብ ዕፅ ምልምት እንተ ትውዒ ደወየ ወፈተወ ኅብስተ ልምሉመ። ናላ ምሉም ውእቱ በግዕዘ ጠባይዕ ሎሰ ጽቡረ ልምሉመ ፈውሳት ልምሉማት ቃቤ አንቀጸ ምኔት ይኩን ምሉመ ቃል ለርሑቃን ወለቅሩባን ወትሑተ ጥቀ -(ስንክ -ታኅ፳፱ ፊልክ -፻፴። አፈ -ተ፭ ጥበ፲፭ -፯። - - -፫። - -)

ልምላሜ -(ያት) ቁሙ፤ መለምለም መለስለስ፤ አለሳለስ ልስላሴ ርጥበት ርጥብነት ለምለምነት ውስተ ገነ ይየብስ ልምላሜሁ ልምላሜ ኅብስት። ምላሜ መባልዕት -(ኢዮ፲፰ -፲፮። ቅዳ - -፳፫)

ልሱሕ -(ሓን ሓት ስሕት) የላሸ ያለጠ ልጫ ሕጹጽ ምኑን ልሱሕ ገሮሙ ለአብዳን። ጼው ዘአጥዐሞ ለልሱሕ ሱሐ ይል -(ሢራ፳ -፳፬ ቅዳ -ዮሐ ገድ -)

ልሱን -(ናን ናት ስንት) የተለሰነ ስን ምርግ።

ልሳነ  ሰብእ -የድርሰት ም፤ መልክአ ልሳን የልሳንን ባይ የሚናገር

ልሳነ መድሎት -የሚዛን ቀንበር ጋድሙ ወይም ላንሴታው -(ጥበ፲፩ -፳፫)

ልሳነ ባሕር -የባሕር ሾለቅ ሞጥሙጦ ወደ የብስ ማኽል የሚገባ -(ኩፋ -) ወደ ባሕርም የሚገባ ወንዝ ልሳን ይባላል -(ኢሳ፲፩ -፲፭)

ልሳነ እሳት -የእሳት ንቃ ነበልባል -(ሔኖ፲፬ -)

ልሳነ ዕፍረት -ምዑዘ ቃል ነገሩ እንደ ሽቱ ደስ የሚያሰኝ -(ስንክ -ጥቅ፲፫)

ልሳነ ወርቅ -ጽሩየ ቃል ነባቤ ቃል ጽሩይ፤ አንደበተ ጥሩ -( - - -)

ልሳናዊ -ነዊኀ ልሳን ምላሰኛ ለፍላፊ አሳባቂ፤ ወይም ቋንቋ ዋቂ።

ልሳን -(ናት ዕብ ላሾን ሱር ሊሽና ዐረ ሊሳን) ቁሙ ምላስ ንደበት የአፍ ውስጥ ሕዋስ የመብል የነገር መሣሪያ -(ያዕ፫ - -፮። ሢራ፳፰ -፲፭ -፲፱ -፳፮። መዝ -፭። ፲፩) በርሱ መሣሪያነት የሚነገር ቃልና ቋንቋም ርሱ ስም ሥቶ ልሳን ይባላል ዘክልኤ ልሳኑ ልሳን ጥዑም ጥዑመ ልሳን ቃል ነገር -(ሢራ፮ -፩። -፳፩። ድጓ) ሕዝብ ዘኢተአምር ልሳኖሙ እለ ካልእ ልሳኖሙ በካልእ ልሳን ይትናገሩ ሰብዓ ወክልኤቱ ሳናት ዘሴም ሠርቱ ወሰብዐቱ ዘካም ሠላሳ ዘያፌት ዕሥራ ወኀምስቱ -(ኤር፭ -፲፭ ሕዝ፫ -፮። ማር፲፮ -፲፯። ትርጓ -ፊደ)

 

ልሳን እንተ ወርቅ -የወርቅ ገንዘብ በልሳን አምሳል የተሠራ -(ኢያ፯ -፳፩)

ልስሐት -መላሸት ማለጥ ልጫ መኾን ልጫነት አለመጣፈጥ። ልስሕተ ግዱፍ ልስሐተ ልሳንየ -(ስንክ -ጥቅ፲፪። ደራሲ)

ልቁሕ -(ሓን ሓት ቅሕት) የተለቃ የተበደረ ተቀባይ፤ ወይም ተሰጭ

ልቃሔ -(ሕያት) ማበደር መበደር በዳደር ብደራ ልቆ የብድር ሥራ። እስመ አፍቅሮቱ በላዕሌከ ልቃሔ። ፍትሐ ልቃሕያት -(ማር -ይሥ፴፫ -፫። - -፴፬)

ልቃሕ -(ሓት) ልቆ ብድር ዕዳ ዘየሐንጽ ቤቶ በንዋየ ልቃሕ ምጽዋትሰ ልቃሕ ምላካዊት። ወልቃሕሰ ይደሉ ይኩን በአኅዝ በትሕቢት -(ሢራ፳፩ -፰። - -፲፮ ፳፯)

ልቅላቄ -መለቅለቅ፤ አለቃለቅ ልቅለቃ ልቅልቃት መጨረሻ ዕጥበት

ልበ ሰብእ -አስተዋይ ተመልካች የነፍስ ዕውቀት ያለው -(ዳን፯ -)

ልበ ሥጋ -ልሕሉሕ ርኅሩኅ ገር የዋህ -(ሕዝ፲፩ -፲፱)

ልበ አርዌ -ቍጡ ብስጩ የደመ ነፍስ ዕውቀት ያለው -(ዳን፬ -፲፫)

ልበ አንስት -ደካማ ሕጹጽ ፈሪ ብቡ -(አዋል)

ልበ እብን -ጥኑ ካኝ ፈዛዛ፤ ድፍን ደረቅ -(ሕዝ፲፩ -፲፱)

ልበ ወበልብ -(ዕብ ብሌብ ዋሌብ) በልብ ወልብ ልብ ሐሳብ -(መዝ -፲፩) ልብ በነገር ኹሉ እየተናበበ እንደ ዘርፉ ስልት ይፈታል፤ ለዳቦም ሳይቀር ውስጥ ላለው ኹሉ ይነገራል -(ተረት) በገዛ ዳቦዬ ልብ ልቡን ጣኹት

ልበ ፀበርት -(ዕብ ሉላብ) ለጋ ቀንበጥ ሙሽራ፤ ከውስጡ ልቡ የሚወጣ -(ሕዝ፲፯ -፳፪)

ልቡስ -(ሳን ሳት ብስት) የለበሰ የተከደነ ሽፍን። እን ልቡስ አልባሰ መንግሥት ካህናት ቆሙ ልቡሳኒሆሙ ይእቲ ሥዕል ትመስል ብስተ ሥጋ -(አስቴ፰ -፲፭። ዕዝ፫ -፲። ታምር)

 -የተለበሰ ልብስ ውራጅ ዝንቱ ልብስ ልቡስ ወአኮ ሐዲስ -(ዘረፋ)

ልቡባዊ -የልብ የውስጥ፤ ውሳጣዊ። ንጸውዖ ለእግዚእነ ረድኤት በዐውያት ልቡባዊ -(ፊልክ -፻፲)

ልቡብ -(ባን ባት ብብት) ልበ ቅን ገር ልዝብ ገራም ጭምት ምስለ ኖኅ ቡብ ወኵሎሙ የዋሃን ወአሐዱ ምኔሆሙ ኮነ ልቡበ ፍጹመ ወየዋሀ ወይኤምሮሙ ፍኖተ ልቡባን -(ቅዳ -ዮሐ ፊልክ -፳፯ መዝ -፳፬)

ልቡና -(ናት) በቁሙ፤ ውቀት ሐሳብ ማስተዋል ልቡና ረሰየተከ መካና ጸግወነ ጥበበ ወኀይለ ልበ ወልቡና። ወሀቦሙ እግዚ ጥበበ ወአእምሮ ወልቡና በኵሉ መጽሐፍ። ይበጽሕዎ ልቡናት -(ድጓ ቅዳ። ዳን፩ -፲፯ ያዕ እል) ልብ ልቡና አእምሮ እሊህ ሦስቱ ባይን ይመሰላሉ ልብ በጥቍሩ ልቡና በብሌኑ እእምሮ በብርሃኑ ወይም ልብ በነጩ ልቡና ጥቍሩ አእምሮ ብሌኑ ይመሰላል ሊትና ልብም ከናላ ጋራ በሚዛን ይመሰላሉና ናላን ተመልከት።

ልቡይ -(ያን ያት ቢት) ልቡና የሌለው ዝንጉዕ ስሑት ግብዝ መጥፎ እነግር ልቡይ ወህጉል ከፊል ክልኤ ወረስዮ በዘዘ ዚኣሁ ሰብአ ወአምላከ -(ቄር -እስት)

 -ሐስት ስሕተት ጸያፍ፤ ከስሑታን አፍ የሚወጣ ከንቱ። እቡሰ ወልቡየ በዑ ልቡይኬ ይእዜ ኀቤነ ወዕቁፍ ከመ ሚን ይብሉ ንኤብስ ዐቢየ እመ ንቤ ሐመ ቃል፤ ወኵሎ ብረ ምስጢር ልቡየ ንሬሲ -(ቄር -)

ልቡጥ -(ጣን ጣት ብጥ) የተለበጠ ልብጥ ፍን። ልቡጥ በወርቅ ወእሱር በወርቅ ልቡጣን ወቅቡዓን በወርቅ ደሙ ልቡጥ ውስቴቱ ልቡጥ በቅድስና። -(ዘፀ፳፰ -፳። ፪ዜና - -፲፰ ዮሴፍ ስንክ -ኅዳ፳፩)

ልባብ -( ልባባት) በቁሙ ፉሎ ሕሳልን እይ -(ዐማርኛ)

ልባዊ -(ዊት) የልብ የውስጥ ጥልቅ ረቂቅ ኅቡእ። ብያኔ ልባዊ። ስፍጠታተ ሰይጣን ልባዊ ጸሎት ልባዊት -( - -ፊልክ -፬። ፻፷፩)

ልባዌ -ልብ ማድረግ ማስተዋል። ዕውቀት የልብ አስተያየት ቅዱሳን ሲበቁ ከሚያገኟቸው ካሥሩ ማዕርጋተ ጽሕ አንዱ ልባዌ ይባላል፤ ስማቸውና ተራቸው ቍጥራቸውም ይህ ነው የንጽሐ ሥጋ መዓርግ ጽማዌ ልባዌ ጣዕመ ዝማሬ የንጽሐ ነፍስ መዓርግ አንብዕ ነኔ ፍቅር ሑለት የንጽሐ ልብ መዓርግ ንጻሬ መላእክት፤ ተሰጥሞ ከዊነ እሳት ለነዚሁ ደግሞ ብዙ ዘርፎችና ቅጥዮች አሏቸው -(አረጋ -መል፵፰) እምአበድ ልባዌ። በአጽባዕተ ጥበብ ወልባዌ ልባዌሁ -(ጥበ - ደራሲ - -፵፬ -)

ልብ -( አልባብ ዕብ ሌብ ሌባብ ሱር ሊባእ። ዐረ ) በቁሙ የታወቀ ሕዋስ ንዋያተ ውስጥ አንዱ በሕያው ፍጥረት ውስጥ በየደረቱ የሚገኝ፤ የደም መሰብሰቢያ ደም ርሱ እየመነጨ ወደ ገላ ኹሉ የሚገናኝበት የሚሠራጭበት ውስጥ ውሳጣዊ ገላ የሐሳብ የፈቃድ የውቀት ምንጭ ወይም ከልብ የሚወጣ ሐሳብ ፈቃድ ዕውቀት ልብ እን ወልድ ኅሊና እኩየ ዘክልኤ ልቡ ወገብኦ ልቡ ምንት ትኄልዩ እኩየ በአልባቢክሙ -(ምሳ፮ -፲፰ ያዕ፩ -፰። ሉቃ፰ -፴፭። ማቴ፱ -) ልበ ምድር ልበ ባሕር ቢል ውስጥ ማለት ነው

ልብሰት -መልበስ መለበስ አለባበስ ልብስነት። ምልብሰቱ ለሰበእ ወሑረቱ። ብሰ ማኑኤል ብሰተ ሥጋ -(ሢራ፲፱ -፴። ቅዳ) በልብስ ፈንታ ልብሰት ይላል ያሰኝም። ግሩም በልብሰቱ -(ኢሳ፷፫ -)

ልብስ -( አልባስ ሳት) በቁሙ የገላ መክደኛ መሸፈኛበየስሙና በየመልኩ ታላቁም ናሹም ድንኳንና መጋረጃ ይቀር ልብስ ንዱሕ። አልባሰ ወርቅ -(ራእ፫ -፭። መዝ -፵፬)

ልብብና -ልበ ቅንነት፤ ገርነት ገራምነት -(ፊልክ -፻፺፬)

ልብን [1]- -(ዕብ ሊብኔ ዐረ ሉብነ) ነጭሎ ነጭ ዛፍ ቅጠሉም ቅርፍቱም ነጭ የኾነ በትረ ልብን -(ዘፍ፴ -፴፯። ኢዮ፵ -፲፯)

[2]-ልብን -(ዕብ ልቦና ሔልብና። ዐረ ሉባን) ነጭ ጣን ልባንጃ ሽቱ ርቤ ወተታ ዕንጨት የሚወጣ ማየ ልብን -(ኩፋ -፲፮ ዘፀ፴ -፴፬። ማሕ፩ -፲፫) በልብን ፈንታ ሊባኖስ ይላል፤ ስሕተት ነው -(ኤር፲፯ -፳፮)

ልብው -(ዋን ዋት ቡት) ልበኛ ልባም ዋቂ ልብ ያደረገ ያስተዋለ። ብእሲ ጠቢብ ወልብው ንጉሥ ብው። ዘምሩ በወ ምሁራን ወልብዋን -(ዘፍ፵፩ -፴፫። ጥበ፮ -፳፮ ዜና -፳፭ -)

ልብውና -ልባምነት አስተዋይነት።

ልብጠት -መለበጥ -(ጥለ) መለበጥ አለባበጥ ልበጣ ልባጥ ልብጣት

ልቱም -የተለተመ፤ ውግጥ ፍትግ -(ዘፀ፳፱ -፵። ዘሌ፪ -፲፬) ሐሪጽ ልቱም፤ ታጥቦ ተፈትጎ የተፈጨ ንዳሌ -(፫ነገ - -፳፬)

ልቱት -(ታን ታት ትት) የለተተ ድኩመ ልሳን ድዳ ለንባዳ፤ ወይም በጭራሽ መናገር የማይችል በሃም። አስተርአየ መድኅኒነ ያርትዕ ልሳነ ልቱተ ወያሩጽ ሐንካሰ -(መዋሥ)

ልታቴ ልተት -ልቱትነት፤ ድካም ልስላሴ

ልት -ልት፤ ቁሙ የቅጠል ስም የደጋን መሟዣ ደካማ ለስላሳ የወጥ ቅጠል -(ግጥም) የዚህ ቤት ቶች ትቅበጡ ልቶጡ ናችኹ ልቶጡ -(ልት ወጡ) ስልም ሲለግምና ያቀብር ልት ቀጥቅጦ ቢያስሩበት ነፍርቆ ይሽራል።

ልዑል -(ላን ላት ልት) በቁሙ ያለ የበለጠ በላይ ያለ ታላቅ ረዥም ምጡቅ ልዑል ውእቱ ዕለ ኵሉ። አእምር መጠን ልዑል እምኔከ ደመና ሰማይ ልዑል መንበር ልዑል -(መዝ -፺፰። ኢዮ፴፭ -፭። ምሳ፳፭ -፫። ኢሳ፮ -)

ልኡክ -(ካን ካት እክት) የተላከ መልክተኛ አገልጋይ። ልኡከ እግዚእነ ግብረ ልኡካን -(፩ጴጥ - -፩። ግብ -)

ልዒት ቶት -(ለዐተ ይልዕት ይልዐት) መላት፤ ላት ማውጣት። መትከል ማግባት፤ ማዋደድ መሰካት ማሰማማት ንጨትን ከብረት ብረትን ከንጨት

ልዒል ሎት -(ለዐለ ይሌ() ዕል ይልዐል ዕብ ወዐረ ዐላ) ላይ ላይ ማለት ከፍ አፈፍ አፈፍ ማለት መነሣት ማረግ ወደ ላይ መውጣት፤ መርዘም ብለጥ መክበር ልዕልና ማግኘት በላይ መኾን ደየበን እይ ልቦ ባዕድ ዘይሌዕል ምኔሁ። ንዘ ሊሁ ይልዕል ምሰማይ። ጽባእ ዕጽብት ዘትልዕል እምኀይሉ በእንተ ውስቦ ራብዕ ዘይልዕል እምኔሃ። ዝንቱሰ ራእይ ይሌዕል ፈድፋደ ምጠባይዕ -(አፈ -ድ፲፩ ተ፲፮ ፊልክ -፻፵ - -፳፬ - አረጋ መል፵፬ ማር -ይሥ፩ -፲፩) ዳግመኛም ላዕሎ ዐለ ይላዕል ብሎ እንደ ሐወ በባረከ ቤት ሊገሰስ ይቻላል። አንዳንድ መጽሐፍ ግን በለዐለ ፈንታ ተልዕለ ተለዐለ ይላል፤ ባለቅኔዎችም በዚሁ አካኼድ ይገሱታል ፍጹም ስሕተት ነው ተለዐለ ማይ ዲበ ኵሉ ድባር ዋኃት። ተለዐለት ታቦት እምነ ምድር። ዕፀ ቄድሮስ ተለዐልኩ። ተልዒልየ ተትሕትኩ ወተለዐለ ዕለ ሎሙ ሰበእ በልቡናሁ ወበጥበቡ -(ኩፋ -፭። ዘፍ፯ -፲፯። ሢራ፳፬ -፲፫ መዝ -፹፯። ስንክ -ጥቅ፮)

ልኢክ ኮት -(ለአከ ይልእክ ይልአክ) መላክ መስደድ። ደገመ ልኢከ ቤሁ ለአከ መጻሕፍተ ወተናብልተ ወአምኃ ሕዝቅያስ ለአኩ ኀቤሁ አይሁድ። ለአከ ወነሥኣ -(፫ነገ - -፭። ኢሳ፴፱ -፩። ዮሐ፩ -፲፱ ፍ፳ -)

ልኢፍ ፎት -(ለአፈ ይልእፍ ይልአፍ ዐረ ላፈ ለአፈ) መላፍ መማግ የሙቅ ያጥሚት። መብላት መዋጥ መሰልቀጥ፤ የጥሕሎ  የፍትፍት።

ልዕልና -በቁሙ ልዑልነት ታላቅነት፤ ከፍታ ምጥቀት ርዝመት። ልዕልና መዝራዕትከ የኀስር ልዕልና ዕጓላ መሕያው የአምር ይለ ልዕልና ሰማያት ገነትሰ በእንተ ልዕልናሁ ምድር ይሰመይ ሰማየ ልዕልናሁ ውእቱ ማይ ምድር ለምጽናዕ -(ዘዳ፫ -፳፬ ኢሳ፪ -፲፩ ሢራ፲፯ -፴፪። ፊልክ -፯። ዕር -ኢሳ፯ -፲፰)

ልኵትንት ልኵንት -(ለሐኰ ልሒኵ) ልሕኵት ልጕን፤ የሸክላ የዘይት ማሰሮ ገንቦ ማድጋ። ልኵንትኪኒ ዘቅብዕ -(፫ነገ -፲፯ -፲፪ -፲፬ -፲፮። ነገ - -) ልኵንትና ልኵትንት በልሕኵት ፈንታ የገባ የጣፊ ስሕተት ኾነ አንዳንዱ መጣፍ ልሕኵት ይላል

ልኵንት -ልሕኵትልኵትንት

ልኩእ -(ኣን ኣት ክእት) የተለካ የተላከከ የተጣበቀ የተቸነከረ። ወልኩእ ዲበ መሳክዊሃ ሰሌዳ መጽሔት። መልክ ሥጋሁ ልኩእ ዕለ ዕፀ መስቀል -(አዋል ስንክ -ጥር፳፯)

 -የታተመ የተጻፈ። ጽሑፍ ተዝካር ውስቴቱ ወልኩእ በአምጣነ ልቆሙ ናሁ ኩእ ውስተ መጽሐፈ ፋርስ ወሜዶን ተዝካር። ወነገሩ ዘተርፈ ልኩእ በመጽሐፉ -(ሢራ፵፭ -፲፩ አስቴ፲ -፪። ዮሴፍ)

ልኩፍ -(ፋን ፋት ክፍት) የተለከፈ የተነካ ንክ ኢልኩፋን ግሰት አጻብዕ -(መጽ -ምስ)

ልክአት -መለካት መጣፍ ማተም፤ መታተም -(አርጋ)

ልክፈት -መንካት መነካት አነካክ ንኪት ልክፊያ ቅምሻ

ልዉስ -የተለወሰ የተቦካ የታሸ። ልዉስ በቅብዕ ሐሪጽ ልዉስ -(ዘፀ፳፱ - ሆሴ፯ -፬። ኩፋ -)

»ልደት -(ታት) [1]-በቁሙ፤ ውልደት መውለድ መወለድ ወላለድ፤ ትውልድ። ዕለተ ልደቱ በልደቱ እምብእሲት  ከመ ውእቱ ልደቶሙ ለደቂቀ ኖኅ -(ማቴ፲፬ -፮። ቄር። ዘፍ፲ -)

 -መውጣት መብቀል፤ መገኘት መፈጠር ፍጥረት ልደተ ወርኅ። ከመ ልደተ ንጻሬ ምዐይን ወከመ ልደተ አምሳለ መልክእ እመጽሔት ወልደተ ዓለም ለድኂን ኦሪት ዘልደት -(መር -ዕዉ ያዕ -ዘእል ጥበ፩ -፲፬ ዘፍ -)

 -ዘር የትውልድ ሥር ሐረግ መጽሐፈ ልደት። ኍልቈ ልደት -(ማቴ፩ -፩። ፩ዜና - -)

[2]-ልጅነት ልጅ መኾን ልጅ መባል፤ መታደስ ዳግም ልደት -(ቲቶ፫ -፭። ማቴ፲፱ -፳፰) የደብረ ሊባኖስ ሊቃውንት ልደትን አምልተው አስፍተው ሲተረጕሙና ሲፈቱት እንዲህ ብለው ይዘረዝሩታል። ልደት በ፪ ወገን ነው በባሕርይ በግብር የባሕርይ ልደት የባሕርይ አባትን የባሕርይ እናትን መስሎ ተካክሎ መብለጥና ማነስ የለበትም ከዚህ የተነሣ ጌታችንም በባሕርይ ልደቱ መንቲያና ታናሽ መሳይ ተከታይ ወንድም ስለሌው ላባቱም ለናቱም ወልድ ዋሕድ እንጂ በኵር አይባልም፤ በሰውነቱም ባምላክነቱም ባሕታዌ ልደት ነውና፤ ከዋሕድና በቀር ብኵርና የለውም ብንሰጠውም እንደ ዋሕድናው የባሕርይ ገንዘቡ ስላልኾነ ዕሺ ብሎ አይቀበለንም። የግብር ልደት ግን ለባሕርይ ልደት ምሳሌ ነውና ምሳሌ ከአማናዊ እንዲያንስ እንዳይተካከል የግብር ልደትም ከባሕርይ ልደት አይተካከልም በስ ብቻ ልደት በመባል ይተካከለዋል። አወላለዱም፤ ዘእንበለ ካሕድ ዘየዐቢ ይባርኮ ለዘይንእስ እንዳለው ኹሉ -(ዕብ፯ -) ከሚበልጠውና ከሚቀድመው ተባርኮ ተሹሞ ሀብተ ወልድና ስመ ወልድና ተቀብሎ መውለዱና መወለዱ ሳይኖር በመስጠትና በመቀበል ብቻ አባትና ልጅ መባባል ነው ናታንና ዳዊት በትንቢት፤ አነ ከውኖ ባሁ ወውእቱ ይከውነኒ ወልድየ -(ወልድየ አንተ) ወአነ ዮም ወለድኩከ ውእቱ ይብለኒ ቡየ ንተ ወአነሂ በኵርየ እሬስዮ ያሉት መልአኩም በብሥራት፤ ዘኒ ይትወለድ እምኔኪ ቅዱስ ውእቱ ወይሰመይ ወልደ እግዚ ልዑል ያለው። ሊቃውንትም ከዚህ አያይዘው ወንሰምዮ ወልደ ናሁ ኮነ ለነ ወልደ በሀብት ወተሠርዐ ወልደ እግዚ በኀይል ቅብዐ መንፈስ ቅዱስ እመሰ ሰይነ ልደቶ እን ከማነ በመኑ ትመሲለነ ንከውን ውሉደ እግዚ በመንፈስ ያሉት ዚህ በግብር ልደት ነው የግብር ወይም የጸጋ ልደት ጸጋ ወንድሞች ከተወራራሾች ቢያስተካክል እንጂ ከወላዲና ከሠያሚ አያስተካክልም ይኸውም ቀደሶ ወፈነዎ። እስመ አብ የዐብየኒ ባለው ይታወቃል -(ሮሜ፰ -፲፬፲፯ ዮሐ፲ -፴፮። ፲፬ -፳፰ -፲፯) ወረሰየነ ሩያነ ምስሌሁ በመንፈስ ቅዱስ ይቤ ነግሮሙ ስመከ አኀውየ ዝኒ ከመ ያግህድ ዕበየ ክብር ዘወሀቦሙ ከመ ይትዓረይዎ ለሊሁ ርእስ ወንሕነ ባል ወሱቱፋኒሁ በተዋርሶ -(ቄር። አፈ -ድ፬ ) የግብር ልደትም የሚፈጸም ኋላ በትንሣኤ ነው እስከዚያ ረቦን ይባላል -(ሮሜ፮ -፱። ቆሮ - -፳፩ -፳፪ -) ይኸውም ሊታወቅ ሐዋርያው ዮም ወለድኩከን ኹለተኛ ስለ ትንሣኤ ጠቅሶታል። ሊቁም ወውእቱ ቅድመ ዘተወልደ እሙታን ብሎታል -(ግብ፲፫ -፴፫። ሃይ - -) ያረቦኑና የትንሣኤው ልደት ንድ  ነው እንጂ ኹለት ይባልም፤ ትርጓሜ ወንጌል ግን እየብቻው ቈጥሮ ርባዕቱ ልደታቲሁ ክርስቶስ ይላል ይኸውም ቢኾን የትንሣኤን ልደት መባል እንጂ አራተኛነትን አያሳይም ረቦን እንደ ፅንስ ትንሣኤ እንደ ልደት ነውና።

»ልድ  [1]-ውላጅ የቤት ውልድ የባሪያ ልጅ ልደ ቤቱ -(ዘፍ፲፯ -፳፫ ኤር፪ -፲፬)

[2]-(ዐረብ) ስመ ሀገር ልዳ የቅዱስ ጊዮርጊስ መቃብር ልድ ልደት -ወሊድ ወለደ

[2]-ልደት ወሊድ ወለደ

»ልገት -(ታት) [1]-ጐዦ ቅልስ መተሜታ ዋሻ ጐሬ ሾልኮ ተጐንብሶ የሚገቡበት። ልገተ ዐቃቤ ቀምሕ ወገብረ ሎቱ ልገተ -(ኢላ፩ -፰። ዮና፬ -)

[2]:-ጐዦ መተሜታወለገ

 -(ሱር ልጊና፤ ላጊና ጽር ላጊኖስ) ለገን ዋዲያት፤ ማድጋ ምንቸት፤ መንቀል ኵስኵስት ገንዐ ወልጕነ -(ገድ -ተክ)

ልግነት -ገንፎ መንካኮ እንቀት አጥሚት

ልጐት -(ታት ዐረ ሉጀት) ላይ ጥልቅ ዕመቅ የባሕር የወንዝ የጕድጓድ የዐዘቅት። ያስጥምዎ ውስተ ልጐተ ባሕር ልጐታተ ብሕርት። ልጐታተ ምድር ይሜጡ ሎሙ ንዋዮሙ ወልጐተ ምድሮሙ -(ማቴ፲፰ -፮። ኩፋ - ስንክ ጥቅ፳፫ ኅዳ፲፫)

ልጓም -(ማት፤ አልጓም። ዐረ ሊጃም ሱር ሉግማ ዕብ ልጊማ) ጕርሻ ባፍ የሚመላ ንዳፍ አንድ ቢጆ ቁሙ፤ ቀለበቃም ብረት በእንስሳት አፍ የሚጐረሥ። ለአፍራስኒ ወዲ ሎትን ልጓመ ውስተ አፉሆን ይፈትሕ ልጓማተ ጽኑዓን። በአልጓሚሁ -(ያዕ፫ -፫። ሔኖ፵፮ -፬። ቄር)

ልጕን (ሱር ልጊና ላጊና ጽር ላጊኖስ) ለገን ዋዲያት ማድጋ ምንቸት መንቀል ኵስኵስት ገንዐ ወልጕነ (ገድ ተክ)

ልጥር -(ጽር ሊትራ ሱር ወዕብ ሊጥራ ዐረ ረጥል) የሚዛን ም፤ የታወቀ ሚዛን ነጥር ፲፪ ወቄት የሚያነሣ በዱሮ ሒሳብ። ነሥአት ዕፍረተ ልጥረ። ምእተ ልጥረ። ሠለስቱ ምእት ልጥረ ወርቅ -(ዮሐ፲፪ -፫። ፲፱ -፴፱። -ተ፳)

ልጹቅ -(ቃን ቃት ጽቅት) የለጠቀ የቀረበ፤ የተጠጋ የገጠመ፤ የተያያዘ ፅሙር አዘዘ ጦስ ያንኅሉ መካነ ልጹ ቍድስ አግዋር እለ ልጹቃን ኮነት ፍስ ልጽቅተ ምስለ እግዚአብሔር -(ዮሴፍ - -፴፯ አፈ -ተ፳፯)

ልጽቀት -መለጠቅ መጣበቅ ልጥቅ ማለት እንደ ድጕስ ቅርበት ልጽቀት -(ቄር )

ልጽቅ -( ልጸቅ) ሳንቃ መዝጊያ፤ ወይም የቤት ታዛይ ጕርጅ ጓዳ። ኆኃት ውሳጥያት እለ ያበውኣ ውስተ ጽቀ ቤት -(፪ዜና - -፳፪)

ልፉጽ -የተለፈጠ ልፍጥ የታሸ የታበቀ ልዉስ ፍጹም ሊጥ ቀጭን ብጥብጥ ያይዶለ እንፍርፍር። ልፉጽ በቅብዕ -(ዘፀ፳፱ -)

ልፋፈ ጽድቅ -መንፈሳዊ ክታብ፤ የደረት መጣፍ፤ ማንበቡና መሸከሙ ብቻ የሚያጸድቅ፤ ኋላም ሞቱ ብሮ የሚቀበር። መንፈሳዊነቱ በአፍኣ ነው እንጂ በውስጡ ብዙ ጸያፍ ቃል ሐሰትና ስሕተት አለበት። ሐሰቱም ንዱ እግዜር እንዳሠርቱ ቃላት በጁ ጣፈኝ ይላል ሌላም ይህን የመሰለ ግብዞችና አታላዮች ፈልስፈው ያወጡት አርድእት ባርቶስ ኅቡእ ስም የሚሉት ልፋፍ አለ

ልፋፍ -(ዐረ ሊፋፈት) መለፈፊያ መሸፈኛ ርመዲ ምጽ ልፋፈ ከመ ይክድን አዕይንቲሁ -(ስንክ -መጋ፯)

 -የጠንቋይ ክታብ፤ ጠልሰም ዐይነ ጥላ እንደ ፊደል የሚጠቀለል። የጠንቋይም ባይኾን የሚጠቀለል ኾነ ማናቸውም ጥፈት ልፋፍ ይባላል ልፋፈ ጽድቅ እንዲሉ

ልፍጸት -ልፉጽነት እንፍርፍርነት -( -)

ሎሐ -(ዕብ ላዌሕ) ላገ ረበ አለዘበ ፋቀ ራመመ፤ የንጨት የቈርበት የደንጊያ የብረት ባለቅኔዎች ግን ጣፈ ይላሉ

ሎልዎ ዎት -(ሎለወ፤ ለውለወ ይሎሉ ይሎሉ) መውለብለብ፤ ማውለብለብ፤ ማቃጠል መለብለብ፤ የምላስ የእሳት። ለውለወ ይሲ ሳኖ ወትሎሱ ክቡተ ፍጥረተነ -(መጽ -ምስ ገድ -ተክ። ያዕ፫ -) በሎለወ ፈንታ አሎለወ አለውለወ ይላል ግስነቱ ዐጕልና ገቢር ነውና ያሰኝም። ለውላዋ ማለት ዚህ ወጥቷል

ሎሚ ሎሚን -( ለዋሚን አው ሎሚናት። ዕብ ሊሞን ሱር ሊሙን ዐረ ለይሙን) ቁሙ፤ የታወቀ ዕፅ እሾኻም መዐዛው ጥፍጥ ፍሬው የሚመጠጥ መጣጣ ሖምጣጣ ዘሩ ለምለመ ነው ሎሚ ያማርኛ

 

ሎሚን የግእዝ በትግሪኛ ግን ሎሚ ዮም ማለት ነው። ማየ ሎሚ ወይመትሩ ሎሚነ -( -)

ሎሰ -ለወሰ አቦካለዊስ።

ሎዘ -(ዕብ ላዝ ያሉዝ) መንገድ ወጣ ራቀ ምስጢሩ የለወወ ነው ክፋትና ጥመት ያሳያል

ሎዛ - ሀገር፤ ውዛም የለው በኤፍሬም ዕፃ ውስጥ ያለች ይችውም ቤቴል ናት -(ዘፍ፳፰ -፲፱)

ሎዛን -(ዐረ ላዝን) ዕጣን፤ ሙጫ ከለውዝ ወይም ከሌላ ዕንጨ የሚገኝ ከርቤ ወሜዓ ወሎዛን -(ስንክ -ም፰)

ሎግዮን ሎግዮ -(ጽር ሎጊዎን። ዕብ ሖሼን) ሴዴርያ የደረት ልብስ፤ ከአልባሰ ክህነት አንዱ ልብሰ ሎግዮን ልብሰ ክህነት ሎግዮ -(ዘፀ፴፮ -፲፭ -፲፮ -፳፪። ደራሲ) ባማርኛ መልካም ነገር ሲታይ ወሼን ወሸኔ ውሽን ማለት ሖሼን ከማለት የመጣ ነው

ሎጠ -(ወለጠ ዕብ ላጥ ያሉጥ) ሸፈነ አለበሰ አጐናጠፈ ለወጠ ዋወጠ፤ የልብስ የመልክ። ወለጠን እይ፤ የዚህ መንቲያ ነው

ሎጣዊ [1]-ሎጥማ፤ የሎጥ ይነት። የሎጥ ጎረ ቤት በግብር የሎጥን ጋብቾች የሰዶምን ዎች የሚመስል። ሎጣውያን ዘውእቶሙ እለ ይዜምዉ ተባዕተ -( - - - -)

[2]-ሎጣዊሰዶማዊሎጥ ለወጠ

ሎጥ -መሉጣ ሜላት መጐናጠፊያ የላይ ልብስ ዐጽፍ ግልባቤ የሰው ስም፤ ወልደ እኁሁ ለአብርሃም። ወሎጥሰ ይነብር ውስተ አንቀጸ ሰዶም -(ዘፍ፲፱ -)

No comments:

Post a Comment

ማውጫ

ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ