ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
የ [1]፡-፲ኛ ፊደል በግእዝ አልፍ ቤት በአበገደ፤ ስሙ የማን፤ ቍጥሩ ዐሥር፤ አኃዝ ሲኾን የ ዐሠርት ቱ ይባላል።
[2]፡-የአካል ዝርዝር፤ አነ ለሚል ብቻ። ለልየ፤ ኪያየ፤ ዚኣየ፤ነፍስየ።
[3]፡-ሥርወ ትንቢት፤ የካልኣይ አንቀጽ መነሻ ለሦስት ሰራዊት፤ ለሩቅ ለሩቆች ወንዶችና ሴቶች። ግእዙ ብቻ ስለ ተነገረ ሪብዑና ሳድሱ አይቀሩም። ይህም ዖቀ ፡-(ዖቁ ዖቃ) የዐውቅ ፡-(ቁ ቃ) ይዑቅ። አዖቀ ፡-(ቁ ቃ) ያዐውቅ ያዑቅ እያለ ሌላውን ኹሉ ያሳያል። የትንቢት አሥራው ፬ ብቻ ናቸው፤ የ ተ አ ነ።
የሂድ ዶት ፡-(የሀደ ይየህድ ይይሀድ። ዕብ ያሄድ) ይሁዲ ማድረግ፤ አሕዛብን ወደ ሕዝብ መሳብ፤ ማስጠጋት ማቅረብ፤ መግዛር በኦሪት ማሳመን፤ ከዚህ የተነሣ እግዜርን ማመስገን ማስመስገን። ገየረንና አፍለሰን እይ፤ የዚህ ጎሮች ናቸው ፡-(ማቴ፳፫ ፡-፲፭)።
የመመ ፡-(ትግ ፡-ሐባ) መላ ፈጸመ ቈረጠ ገደበ። ዘሩ ሜመየ ነው።
የመን ፡-(ዕብ ቴማን) ስመ ሀገር፤ የምድረ እስራኤል ደበብ፤ ምድረ ዐረብ።
የሚን ኖት ፡-(የመነ ይየምን ይይምን። ዕብ ያሜን፤ ዐደመ) መቅናት፤ ቅን ቀኝ መኾን፤ መጽናት መበርደድ፤ መብዛት መፈድፈድ፤ መክበር መወደድ፤ በቀኝ መቀመጥ ወደ ቀኝ መኼድ።
የማናዊ ፡-(ዪ፤ ይ) የቀኝ፤ በቀኝ ያለ ቅን፤ ቀኛም ባለቀኝ፤ ቀኝ አዝማች፤ ቀኝ ጌታ በቀኝ የሚቆም። የማናዌ ፍኖተ። ዐይኑ የማናይ። ነደፎ የማና(ዬ) የ ገቦሁ። የማና(ዪ) ይ ወፀጋማይ። እለ ክልኤሆን እደዊሆሙ የማናይ(ው) ያን ፡-(ስንክ ፡-ታኅ፭። ኪዳ። ስንክ ፡-ነሐ፲፯። ቀሌ። መሳ፳ ፡-፲፮)።
የማን ፡-(ዕብ ያሚን። ሱር ያሚና። ዐረ የሚን) ቀኝ፤ የቀኝ እጅ፤ የቀኝ ጐን ማእዝን፤ ደቡብ፤ የግራ ትይዩ የሰሜን አንጻር። ዘትገብር የማንከ ኢታእምር ፀጋምከ። ልቡ ለጠቢብ ውስተ የማኑ። ተፈለጥ የማነ አው ፀጋመ። መንገለ የማነ ምሥዋዕ ፡-(ማቴ፮ ፡-፫። መክ፲ ፡-፪። ዘፍ፲፫ ፡-፱። ሉቃ ፡-፩ ፡-፲፩)። ኀይል ጽንዕ ብዛት እጅግነት።
የሱስ ፡-መድኅን፤–ኢየሱስ።
የቢስ ሶት ፡-(የብሰ ይየብስ ይይበስ። ዕብ ያቤሽ። ሱር ዬቢሽ። ዐረ ፡-የቢሰ) መድረቅ መክረር፤ ርጥበት ልምላሜ ማጣት። ፈለግ ይነፅፍ ወይየብስ። ወውእቱ የብሰ ከመ እብን። ይየብስ ተክሎሙ። የብሰ ማእረረ ምድር ፡-(ኢዮ፲፬ ፡-፲፩። ፩ነገ ፡-፳፭ ፡-፴፯። ኢዮ፳፬ ፡-፲፱። ራእ፲፬ ፡-፲፭)።
የብስ ፡-በቁሙ፤ ደረቅ ምድር ባሕር የሌለው፤ ውሃ ያልሸፈነው። ይቤ፤ ያስተርኢ የብስ፤ ወአስተርአየ የብስ፤ ወሰመዮ እግዚ ለየብስ ምድረ። እለ የኀድሩ የብሰ። በየብስ ወበባሕር ፡-(ዘፍ፩ ፡-፬። ሔኖ፴፯ ፡-፭። ዮሴፍ)።
የብቦ ቦት ፡-(የበበ ይዬብብ ይየብብ። ዕብ ወሱር ያቤብ፤ ጮኸ አለቀሰ) እልል ማለት፤ በደስታ ቃል መጮኽ ማመስገን፤ የዘፈን የማሕሌት። ባበየን እይ፤ የዚህ ግልባጭ ነው። የበበት እሌኒ። ቦ እመላእክት ዘይዜምር ወቦ ዘይዬብብ ፡-(ድጓ። ቀሌ። መዝ ፡-፵፮። ፹፰)።
የካቲት ፡-(ከቲት ከተ፤ ከተተ) በቁሙ፤ የወር ስም፤ ፮ኛ ወር ከመስከረም። የመከር ጫፍ መካተቻ፤ የበልግ መባቻ ማለት ነው፤ ከተተን እይ። አመ ዐሡሩ ወሰዱሱ ለየካቲት በዘወሀባ ከዳነ ምሕረት ፡-(መቅ ፡-ታም)።
የዊም ሞ ት ፡-(ዮመ ይየውም ይዩም) ጊዜን መስፈር መቍጠር፤ መክፈል መተንተን፤ ቅጽበትን በካልኢት ፥ ካልኢትን በደቂቅ ፥ ደቂቅን በሰዓት ፥ ሰዓትን በዕለት ፥ ዕለትን በ፳፬ ሰዓት መወሰን መቀመር፤ የፈጣሪ የሰዓት ሠሪ።
የዋሂ ፡-(ሂት ህያን ያት) የሚያለዝብ የሚያግራራ፤ የሚያሞኝ ሸንጋይ አታላይ።
የዋህ ፡-(ሃን ሃት) በቁሙ፤ የቀና ቅን ልዝብ፤ ገር ገራም ጭምት፤ ደግ ጥሩ፤ እወነተኛ። ቅጽልነቱ ዐጕል ሕገ ወጥ ስለ ኾነ ወንድና ሴት ያስተባብራል፤ አዳምን እይ። ተመሀሩ እምኔየ፤ እስመ የዋህ አነ። ብእሲ የዋህ። በየዋህ ኵነኔ ይኴንን። ቅሩብ እግዚ ለየዋሃነ ልብ ፡-(ማቴ፲፩ ፡-፳፱። ሢራ፳፭ ፡-፳። ኢሳ፲፩ ፡-፬። መዝ ፡-፴)። ብእሲት የዋህ። እመሰ የዋህ ይእዪ ወሠናይ ቃላ ፡-(ሢራ፳፮ ፡-፲፬። ፴፮ ፡-፳፰)። ብዙ መጻሕፍት ይህም የጠቀስነው ሢራክ ሳይቀር በየዋህ ፈንታ የዋሂት ይላሉ፤ አያሰኝም። በሲት የዋሂት እምእከይ። ርግብ የዋሂት። በግዕት የዋሂት ፡-(ፍ ፡-ነ ፡-፲ ፡-፰። አፈ ፡-ተ፴፪። ስንክ ፡-ግን፳)። ለክፋ ሲኾን ሞኝ አላዋቂ፤ ያልተማረ ያሰኛል። የዋህ የአምን ኵሎ ነገረ ፡-(ምሳ፲፬ ፡-፲፭)።
የውሀ ፡-(ዐጕል። ዕብ ፡-ያኣህ) አማረ ተዋበ) ዝኒ ከማሁ፤ የዋህ ኾነ ለዘበ ቀና፤ በገዛ እጁ።
የውሀት የውህና ፡-በቁሙ፤ የዋህ መኾን የዋህነት፤ ገርነት ቅንነት። በየውሀት ተናገረኒ። ዘየሐውር በየውሀት። ይኩነኒ በከመ የውሀትየ። ርግብየ ይቤላ በእንተ የውሀታ። ከመ በየውህና ንሕዮ ፡-(ዕር ፡-ኢሳ፯ ፡-፮። ምዳ፲ ፡-፱። መዝ ፡-፯። ድጓ። ቄር ፡-ጰላ)።
የውሆ ሆት ፡-(የውሀ፤ ይዬውህ ይየውህ) ፡-(ገቢር) ማለዘብ ማለዛዘብ፤ ማግራራት ማቈላመጥ፤ ቅንነት ማስተማር፤ ገር የዋህ ቅን ማድረግ። ሀሎ ዘይጠብብ ለነፍሱ ወይዬውህ በቃሉ። አኀዘ ይየውሃ በቃል ሠናይ። እትጋነይ ላቲ ወእዬውሃ። ትዬውሆሙ ለኃጥኣገ ወትመይጦሙ በብዝኀ ምሕረትከ። መዐተ ንጉሥ ከመ መልአከ ሞት፤ ወብእሲ ጠቢብ ይዬውሆ ፡-(ሢራ፴፯ ፡-፳፪። አስቴ ፡-፭። ኢዮ፲፮ ፡-፲፯። ዲድ ፡-፴፮። ምሳ፲፮ ፡-፲፬)። ማሞኘት ማታለል፤ መደለል መሸንገል፤ የክፉ። ዘይዬውሁ ለከንቱ። ኢየዋህናክሙ በቃል ፡-(ቆላ፪ ፡-፰። ፩ተሰ ፡-፪ ፡-፭)። በየውሀ ፈንታ አየውሀ ይላል፤ ስሕተት ነው። አየውህዎ ፡-(ስንክ ፡-ሚያ፳፰)።
የውጣ ፡-(ጽር ዮታ) ስመ ፊደል የ፤ ፲ኛ፤ ዐሥር ፡-(ማቴ፭ ፡-፲፰)። ቀዳሜ ስሙ ለኢየሱስ የውጣ በኍልቈ ፡-(፲) ዐሠርቱ። ፈጻሚተ ቃላት የውጣ ፡-(ዲድ ፡-፰። ውዳ ፡-ማር፩። ስንክ ፡-ነሐ፲፮)። የሱስ በማለት ፈንታ የውጣ ይላል፤ ስሕተት ነው። መርቆሬዎስ ሰማዕተ የውጣ ፡-(ስንክ ፡-መስ፲፰)።
የዲዕ ዖት ፡-(የድዐ ይየድዕ ይይዳዕ። ዕብ ያዳዕ። ሱር ዪዳዕ) ማወቅ መረዳት፤ ልኩን ርግጡን ማግኘት፤ በጠባያዊ ዕውቀት ፈልጎ መርምሮ ተመራምሮ፤ እንደ አብርሃም እንደ ሙሴ ጸሊም።
ዩ ፡-የቅጽል ምእላድ፤ ወይም የስም አርቲክል፤ በሴት አንቀጽ ለሚነገር ቃል። ሐዳስዩ ፥ ድንግልዩ ፥ ብሊትዩ ፥ ዕቤርዩ እያለ ይህን በመሰለ ይገባል። ሲፈታም ዐዲሷ ዐዲሲቱ፤ ባልቴቷ ባልቴቲቱ ያሰኛል። ይዌድስዋ መላእክት ለማርያም በውስተ ውሳጤ መንጦላዕት ወይብልዋ በሓኪ ማርያም ሐዳስዩ ጣዕዋ ፡-(ሳታት)።
ዪ-ዬ ፡-የሣልስና የኃምስ ሥረዮች፤ ዪ የሣልስ ፥ ዬ የኃምስ። የሣልስ የኃምስ ድምፅ ኹሉ ከዪና ከዬ ወጥቷል፤ ቅጥላቸውም ኢ ኤ የዪና የዬ ምልክት ነው። ፊደል ኹሉ አለየ መሪነት ሣልስና ኃምስ አይኾንም።
ዪ–ይ ፡-የጥሬና የስም ምእላድ፤ ወገናዊ ቅጽል የ ኛ። ዊና ይን ተመልከት።
ያ [1]፡-የጥሬና የስም ምእላድ፤ ፍችው ኛ የ። ኬንያ ሐዋርያ፤ ብልኀተኛ መንገደኛ። ኢትዮጵያ እስክንድርያ፤ የኢትዮጲስ የእስክንድር አገር ወይም ኢትዮጳዪት እስክንድራዪት ያሰኛል፤ ይኸውም በተጸውዖ ስም ሲገባ ነው።
[2]፡-ያ፤ አብዢ ምእላድ፤ ከንና ከት እየተደረበ በሣልስ ቅጽል በሣልስ መስም ይገባል። ቀታሊ ልያን ያት፤ መምለኪ ክያን ያት። ብዙዎቹን ወንዶችና ሴቶች በሚያስተባብር በመድበል ቅጽል ግን ተውጦ ተጐርዶ ይቀራል። ቀተልት፤ መምለክት።
ያህ ፡-(ዕብ። ሱር ይያ) ዐጭር ስመ አምላክ፤ የይሆዋ ክፋይ። ዘይቤው እግዚእ፤ ምስጢሩ ምላትና ስፋት ልዕልናና ርቀት ያሳያል። ዕብራውያንም ሲፈቱ፤ ዐቢይ ወጽኑዕ ስፉሕ ወምሉእ፤ እግዚእ ዘበአማን ዘያገምር ኵሎ ወኢያገምሮ መካን፤ ይሉታል። ሃሌ ሉያ ፡-(ዕብ ፡-ሀልሉ ያህ) የሃሌ ሉያን ፍች እይ።
(ጥ) ያም ፡-(ዕብ) ባሕር ኵሬ፤ ዐዘቅት ምንጭ፤ ጕድጓድ፤ ታላቅ የውሃ ዕቃ። ምዕራብ፤ የፀሓይ መግቢያ መጥለቂያ። ባሕርንና ማርያምን እይ።
ያሬድ ፡-(ዕብራ) የሰው ስም፤ ፮ኛው ትውልድ የሔኖክ አባት። ወሪድ ርደት ማለት ነው፤ በርሱ ዘመን የደቂቀ ሴት ከደቂቀ ቃየል መጋባይና መዋለድ፤ ከደብር ቅዱስ ወደ ምድረ ፋውድ መውረድ ተዠምሯል። የወረዱበትም ምክንያት አዋልደ ቃየል እንደ የጁ አርኾ ስለ ኾኑ በመልካቸው ውበት በድምፃቸውና በዘፈናቸው ጣዕም ተመሥጠው ነው። ወለደት ሎቱ ዲና ወልደ፤ ወጸወዐ ስሞ ያሬድሀ፤ እስመ በመዋዕሊሁ ወረዱ መላእክተ እግዚ ውስተ ምድር እለ ተሰምዩ ትጉሃነ። በእማንቱ መዋዕል ተወልዳ ሎሙ አዋልድ ሠናያት ወልሑያት፤ ወርእዩ ኪያሆን መላእክት ውሉደ ሰማያት ወፈተውዎን፤ ወይቤሉ በበይናቲሆሙ፤ ንዑ ንኅረይ ለነ አንስተ እምውሉደ ሰብእ፤ ወንለድ ለነ ውሉደ ፡-(ኩፋ ፡-፬። ሔኖ ፡-፭። ዘፍ፮ ፡-፩ ፡-፪)። በኢትዮጵያም በሳድሳይ ምእት ፡-(ሴክል) ተነሥቶ ፭ቱን ጸዋትወ ዜማ የደረሰ የድጓና የማሕሌት አባት፤ አሮድዮን እንደሚባለው ወፍ ዜማው ልብ የሚመሥጥ እጅግ ድምፀ መልካም ስለ ኾነ፤ ሰውየው ያሬድ ወፉም ዖፈ ያሬድ ተብሏል፤ ምስክሩን በአሮድዮን ፍች ተመልከት። አእመርነሂ ከመ ሀሎ በቀራንዮ ገነት፤ ያሬድ ዘወለዶ ሔኖክ ማሕሌት ፡-(ጐዣማዊ ቅኔ)።
ያርብሓዊ ፡-ዝኒ ከማሁ። ዔናቃዊ፤ የዔናቅ ወገን፤ ሐርበኛ። ወናሁ ያርብሓዊ ፡-(፩ነገ ፡-፲፯ ፡-፳፫)።
ያርብሕ [1]፡-ዐርበኛ፤–ረብሐ።
[2]፡-(ሓን) ሐርበኛ፤ ኀይለኛ፤ የወንዶች ባል፤ ዠግና ስሙዐ ዜና፤ መጠኑ ቁመቱ ኀይሉና ጕልበቱ ከሰው ልክ ያለፈ የተረፈ፤ እንደ ዔናቅ ልጆች ያለ። ጢጣኖስንና ናፊልን ተመልከት። ኀይለ ያርብሕ። ሥጋ ያርብሕ። በንእሱ ቀተለ ያርብሐ። ከመ ያርብሕ ዘይሜርድ ፍኖቶ ፡-(ኢሳ፫ ፡-፪። ሕዝ፴፱ ፡-፲፰። ሢራ፵፯ ፡-፬። መዝ ፡-፲፰)። ኀያላን ያርብሓን በማለት ፈንታ እለ ያርብሕ ይላል፤ አያሰኝም ፡-(ዘፍ፮ ፡-፬። ፲፬ ፡-፭። ዘኍ፲፫ ፡-፴፬)።
ያቁም [1]፡-የዐምድ ስም፤–ቀዊም ቆመ አቀመ።
[2]፡-(ጽር ያኹም። ዕብ ያኪን) የዐምድ ስም፤ በበለዝ አንጻር በስተቀኝ የቆመ። ቀዋሚ ቅዉም፤ ርቱዕ ድልው ማለት ነው፤ በለዝን እይ ፡-(፫ነገ ፡-፳፩)።
ያክንት ፡-(ጽር ኢያኪንቶስ። ዕብ ሌሼም) ክቡር ደንጊያ፤ ዕንቍ የቀይ ጥቍር ደምማ፤ ቅላቱ የሮማን ፍሬ ደረቅ በርበሬ የሚመስል፤ ደባባ ፡-(ራእ፳፩ ፡-፳። ሔኖ፸፩ ፡-፪። ሕዝ፳፰ ፡-፲፫)።
፡-ቀይ ቀለም፤ የደም ዐይነት። ዘሢረቱ ሕብረ ያክንት። ወእምሕብረ ያክንት ወሜላት ፡-(ዘፀ፳፭ ፡-፭። ፳፮ ፡-፩)።
ያፌስ ፡-(ዕብ ኤፌስ) ባዶ ደካማ ልምሾ። ባለብሉዮች ግን ፋስ ምሣር ይሉታል። ዕብራይስጡ፤ ውብኤፌስ ያድ ይሻቤር ያለውን ፥ ወበድክምት እድ፤ ወይም ፅብስት፤ ፅውስት ዘእንበለ ኀይል በማለት ፈንታ፤ ወበያፌስ ይቀጠቅጥ እደ ይላል፤ አንዳንዱም መጣፍ ዘእንበለ እድ ይላል ፡-(ዳን፰ ፡-፳፭)።
ዬ [1]፡-ቃለ ብካይ ወሰቈቃው፤ በቁሙ፤ ዮ ወዮ ወየው፤ ይብላኝ። ብክይዎ ወላሕውዎ እለ ታፈቅርዎ፤ ዬ ዬ ዬ ዐማኑኤል አምላክነ ፡-(ቅዳ ፡-አፈ)።
[2]፡-ቃለ ትፍሥሕት ወአንክሮ፤ ዕሦ ዕሠይ ኢዮሃ፤ እንሆ። ዬ መስቀል ጸገየ። ዬ ዬ ዬ መንክር፤ እንሆ ድንቅ ፡-(ድጓ)። ፡-(ዕር፳ ፡-ቍ፺፬)።
ዬም ፡-ማዎት፤ ማየ ሕይወቅ ፍል ውሃ።
ይ–ዪ ፡-የቅጽል ምእላድ፤ እንደ ዊ በጥሬና በስም እየገባ ወገን የሚያሳይ። ቅድም ቀዳማይ–ዪ፤ ፡-(ዪት ይያን ያት) ፊተኛ፤ የፊት። ፈያታይ፤ የወንበዶች ወገን፤ ቀማኛ። ላዕላይ ታሕታይ፤ ላይኛ ታችኛ፤ የላይ የታች፤ በላይ በታች ያለ። ግብጻይ ግብጻዪ፤ የግብጽ ሰው። ቀርናይ–ዪ፤ ቀንደኛ ቀንዳም ባለቀንድ፤ የቀንድ ከብት ተዋጊ እያሰኘ እንደ ሙሻዛር እንደ ሣልስ ቅጽል በሚያምርለት ስልት ይፈታል። ምክንያቱም ዊና ዪ ሣልሶች ስለ ኾኑ ነው፤ በዪ ፈንታ ግን ይ መጣፉ ስለ ተለመደ ነው እንጂ ፥ የሚገባው ኹኖ አይዶለም፤ ሣልስና ሳድስ ምን ገጥሞት። ባማርኛ ግን ሳድሱን ሲጫኑት ድምጡ እንደ ሣልስ ስለ ኾነ ሣልስና ሳድስ ይዋረሳሉ፤ ሰጪ ገዢ፤ ሰጭ ገዥ፤ የመሰለው ኹሉ፤ የዊን ፍች እይ።
ይሁዳ ፡-(ዕብራ) የሰው ስም፤ ምስጋና እምነት፤ ወይም አማኒ ምእመን ማለት ነው ፡-(ዘፍ፳፱ ፡-፴፭)። ስመ ነገድ፤ ስመ ሀገር፤ ይሁዳ የወለደውና የወረሰው የይሁዳ ዘር የይሁዳ ምድር። ወኮነ ይሁዳ መቅደሶ ወእስራኤልኒ ምኵናኖ። በእንተ ይሁዳ ወኢየሩሳሌም ፡-(መዝ ፡-፻፲፫። ኢሳ፩ ፡-፩። ማቴ፪ ፡-፳፪። ፫ ፡-፭። ፬ ፡-፳፭)።
ይሁድና ፡-ይሁዲነት፤ ይሁዲ መኾን መባል፤ እምነት። ይሁድና ዘአይሁድ። ጾረ ኀጢአት ዘአመ ይሁድና ፡-(ቄር ፡-ጰላ። ተረ ፡-፲፱)።
ይሆዋ ፡-(ዕብ ይሆዋሀ) ስመ ኦምላክ፤ ከፍጡራን ስም የተለየ፤ ከፈጣሪ በቀር ለማንም ፍጡር የማይሰጥ፤ ፍጡራን የማይጠሩበት። መጽሐፍ ግን በይሆዋ ፈንታ ይሆባ ይላል። ይሆባ ጸባኦት አዶናይ ፡-(ድር ፡-ሚካ)። ፍችውም እግዚአ ኵሉ፤ አምላክ ኵሉ፤ ፈጣሬ ኵሉ ዓለም፤ ንጉሠ ኵሉ ዓለም ያሰኛል። እግዚአብሔርን ተመልከት፤ ከዚህ ጋራ አንድ ነው።
ይሙነ ፡-(ንኡ አገ) እጅግ በጅግ፤ ብዙ በብዙ፤ አካቶ ፈጽሞ፤ ጭራሽ። እስመ አኅሰርዎሙ ይሙነ። አበስኩ ይሙነ። ይከብደኒ ይሙነ። ብዙኀ ይሙነ ፡-(፩ዜና ፡-፲፱ ፡-፭። ፳፩ ፡-፰። ፪ዜና ፡-፬ ፡-፬)። አንዳንድ መጻሕፍት በይሙነ ፈንታ እሙነ ይላሉ፤ የጣፊ ስሕተት ነው።
ይሙን ፡-(ናን ናት ምንት) የማናይ፤ የቀና የጠና፤ ብርቱ በርዳዳ።
ይምን ፡-ዝኒ ከማሁ፤ ቀኝ የቀኝ ክፍል ወገን፤ በስተቀኝ ያለ ቦታ ማእዝን፤ እጅ ሕዋስ። ኀበ ይምነ ሐመር። ዘይምኖሙ። እንዘ ይሰርር ይምነ ወፅግመ። ይምና ለበድነ ሥጋሁ። ነዲፍ በይምን ወበፅግም ፡-(ዮሐ፳፩ ፡-፮። ዘካ፲፪ ፡-፮። ቀሌ። ስንክ ፡-ጥቅ፮። ፩ዜና ፡-፲፪ ፡-፪)።
ይበስ ፡-ድርቅ፤ ድርቀት። ይበሰ ኅብስት ፡-(ስንክ ፡-ነሐ፲፱)።
ይቡስ ፡-(ሳን ሳት ብስት) የደረቀ የከረረ፤ ደረቅ ከራራ። ይብስት ባሕር። አዕፅምት ይቡሳት። ይቡሳነ ልብ። ዕፅ ይቡስ። ኅብስት ይቡስ። ክሣድ ይቡስ ፡-(ዘፀ፲፬ ፡-፳፬። ሕዝ፴፯ ፡-፬። ሔኖ፭ ፡-፬። ሢራ፮ ፡-፫። ቄድር። ኩፋ ፡-፩)።
ይባቤ ፡-(ብያት) በቁሙ፤ እልልታ ጩኸት፤ ምስጋና መዝሙር በደስታ ቃል የሚነገር። ወአልቦ ብዝኅ ለይባቤነ። ዐርገ እግዚ በይባቤ። ማርያም በይባቤ ትዘብጥ ከበሮ ፡-(መዝ ፡-፵፫ ፡-፮። መዋሥ)።
ይቤ ፡-(በዪል፤ ሎት፤ ቤለ ይበይል ይቢል። አው ቤለ ይቤ ይበል) የቤለ ካልኣይ፤ ትንቢት አንቀጽ። ፍችው፤ ይል፤ ይላል፤ ይል ነበር። የቤለ ትንቢቶች ካልኣዮቹ ይቤና ይበይል ኹለት እንደ ኾኑ አስተውል። መምህራን ግን በቤለ ፈንታ ይቤን ከብህለ ደርበው ቀዳማይ አንቀጽ ያደርጉታል፤ ፪ኛም ዘሩና አርእስቱ በዪል ሲኾን አርእስት የለውም፤ ነባር አንቀጽ ነው ይሉታል፤ ብሂልን እይ።
ይብሰት ፡-መድረቅ አደራረቅ፤ ድርቀት ድርቅና ደረቅነት። ሐዘንከኑ በእንተ ይብሰት ሐምሐም። ይብሰት ኅብስት ፡-(ስንክ ፡-መስ፳፭። ፊልክ ፡-፸፬)።
ይንዋርዮስ ፡-(ሮማይ ዠንዋሪዉስ) ስመ ወርኅ፤ ጥር የኤውሮፖች መዠመሪያ ወር። ዘይንዋርዮስ ፡-(ተረ ፡-ቄር፳፭)።
ይእቲ ፡-ያች ርሷ፤ ነች ናት፤–ውእቱ።
ይእዜ ፡-(ይእቲ ጊዜ) አኹን በዚች ሰዓት፤ ዛሬ ዘንድሮ። አኹን ማለት ቅጽበት ደቂቃ ሳይቀር የጊዜን መቅረብና ማጠር፤ ያሉበትን ክፍል ያሳያል። ይእዜ ትስዕሮ ለገብርከ። ይእዜኒ ወዘልፈኒ። እምንእስየ እስከ ይእዜ። እምይእዜ ወእስከ ለዓለም ፡-(ሉቃ፪ ፡-፳፰። ይሁ ፡-፳፭። መዝ ፡-፸። ኤፍ ፡-፭)። አንዳንድ ጊዜም በእንከ ዘይቤ ይፈታል፤ ዮምን ተመልከት፤ የዚህ መንቲያ ነው።
ይዋሄ ፡-ዝኒ ከማሁ። በፍርሀት ወበይዋሄ። ይዋሄ ወህድአት ወስርምሞ ፡-(አፈ ፡-ድ፪። ዮሴፍ። አርጋ ፡-፩)።
ይዱዕ ፡-(ዓን ዓት ድዕት) የታወቀ የተረዳ፤ የተነገረ።
ይዶን ፡-(ሮማይ ይዱስ) ክፍል ወርኅ፤ የወር እኩሌታ፤ በዱሮ አከፋፈል የየካቲት ፲፫ኛ ወይም በሠግር ጊዜ ፲፭ኛው ቀን። ወበወርኀ ሮሜ ቅድመ ሰማኒቱ ይዶን ፍርፍርዮን ፡-(ተረ ፡-ቄር፳፭)።
ዮ ፡-(ያ ዮሙ ዮን) ድርብ ዝርዝር፤ የገቢር ዐጸፋ ባራት ሰራዊት በሩቅ በሩቆች የሚነገር። ኪያሁ ፡-(ሃ ሆሙ ሆን) በማለት ፈንታ፤ እየገባ፤ ያን ያነን ርሱን ያሰኛል። ሀበኒዮ እምውእቱ ማይ። ከመ የሀበኒያ ለይእቲ መጽሐፍ። ወሊተ ወሀብከኒዮሙ። አልቦ ዘየሀይደኒዮን፤ እስመ አቡየ ዘወሀበኒዮን ውእቱ የዐቢ እምኵሉ ፡-(ዮሐ፬ ፡-፲፭። ራእ፲ ፡-፱። ዮሐ፲፯ ፡-፮። ፲ ፡-፳፰ ፡-፳፱)።
ዮም ፡-(ዕብ ዮም። ሱር ያውማ። ዐረ የውም፤ ዕለት፤ መዓልት) ዛሬ አኹን፤ ዘንድሮ፤ የተወሰነ ክፍል መዓልትና ሌሊት፤ ዕለት ወርኅ ዓመት፤ ቀመር። ያሉበትን ቀን ወራትና ዘመን ከመባቻው እስከ መካተቻው ያሳያል። የሰውም ዕድሜ ተወልዶ እስኪሞት ፥ ተሹሞ እስኪሻር የሚኖረው ዮም ይባላል፤ ይእዜንና ዕለትን ተመልከት። ዘትማልም ወዮም። ዮም ወለድኩከ፤ ወዮም ብሂል አኮ ዘኀለፈ መዋዐለ ዘይነግር አላ ዘሀሎ። ዮምኬ ሰብእ ወጌሠመ መሬት። ንጉሥ ለዮም ወጌሠመ ይመውት ፡-(ዕብ፲፫ ፡-፰። ቄር። ድጓ። ሢራ፲ ፡-፲)።
ዮማዊ ፡-ሙያተኛ፤ የዕለት ምንደኛ ከጧት እስከ ማታ የሚሠራ። የዕለት መፍቅድ በየቀኑ የሚወጣ ወጪ፤ ወይም ገቢ ገንዘብ። ዮምዬ እንዲል። ፡-(ዐረብ)። ዘመናይ፤ ሹም ባለጊዜ፤ ዐፍለኛ ጐበዝ፤ ወጣት ልጅ እግር።
[2]፡-(ዕብ ዮም። ሱር ያውማ። ዐረ የውም፤ ዕለት፤ መዓልት) ዛሬ አኹን፤ ዘንድሮ፤ የተወሰነ ክፍል መዓልትና ሌሊት፤ ዕለት ወርኅ ዓመት፤ ቀመር። ያሉበትን ቀን ወራትና ዘመን ከመባቻው እስከ መካተቻው ያሳያል። የሰውም ዕድሜ ተወልዶ እስኪሞት ፥ ተሹሞ እስኪሻር የሚኖረው ዮም ይባላል፤ ይእዜንና ዕለትን ተመልከት። ዘትማልም ወዮም። ዮም ወለድኩከ፤ ወዮም ብሂል አኮ ዘኀለፈ መዋዐለ ዘይነግር አላ ዘሀሎ። ዮምኬ ሰብእ ወጌሠመ መሬት። ንጉሥ ለዮም ወጌሠመ ይመውት ፡-(ዕብ፲፫ ፡-፰። ቄር። ድጓ። ሢራ፲ ፡-፲)።
ዮርዳኖስ ፡-(ጽር ዮርዳን። ዕብ ያርዴን። ሱር ያርድና) ስመ ፈለግ፤ የከነዓን ወንዝ፤ ታላቅ ዠማ፤ ከምድረ እስራኤል ዳርቻ ከነገደ ዳን ክፍል እንደ የወልና እንደ ዳሸን ካለው ደብረ ሔርሞን ከሚባለው ከደቡብ ወገን ከተራራው እግር ከሔርሞን ሥር ተነሥቶ ወደ ደቡብ ወደ ባሕረ ጼው የሚፈስ። ዮር፤ ወራጅ ፈሳሽ። ዳን፤ ደየነ ዳኘ ፈረደ፤ በተገናኝ ፈለገ ዳን ማለት ነው፤ በዳኖስ ዘይቤ ሲፈቱት ግን ዳናዊ ፈለግ ፥ ወይም በጠቅላላው ዮርዳናዊ ያሰኛል ፡-(ኢያ፫ ፡-፰)። ዳን የውነተኛው ዳኛ፤ የውነተኛው መጥምቅ የመሲሕ ምሳሌ ጸዋሬ ስሙ ስለ ኾነ፤ የዮርዳኖስ ነቅ ሥሉስ ቅዱስ ምንጩ አውራጃውና ቀበሌው ገና ነገደ ዳን ሳይወርሱት ከሙሴና ከአብርሃም በፊት አስቀድሞ ባምላካዊ ትንቢት ዳን ተብሏል። ወሐዊርየ ነበርኩ ዲቢ ማያተ ዳን በዳን፤ እንተ ይእቲ እምየማነ ዐረበ ሔርሞን። ተለዎሙ እስከ ዳን። ወአርአዮ ኵሉ ምድረ ገለዓድ እስከ ዳን ፡-(ሔኖ፲፫። ዘፍ፲፬ ፡-፲፬። ዘዳ፴፬ ፡-፩)። ትርጓሜ ወንጌልም ዘአምነ ወዘተጠምቀ ይድኅን፤ ወዘሰ ኢአምነ ይዴየን ያለውን ሲፈታ፤ ዳንን ደያኒ ደያን መደይን ብሎ ዮርዳኖስን ፈለገ ደይን ይላል፤ ፍርዱን እንደ ውሃው ከሰዶምና ከገሞራ ከባሕረ ጼው ጋራ ለማያያዝ ፡-(ማር፲፮ ፡-፲፮። ማቴ፲፩ ፡-፳፫ ፡-፳፬)። የዮርዳኖስ ራስ ነቁና ስሙ በሥላሴ አምሳል ሦስት ነው፤ ያውም አብ ወልድ መንፈስ እንደ ማለት ሐስባኒ፤ ተለልጋዲ፤ ባንያሲ ይባላል። ጣዕሙና ሕብሩም እንደ ስሙ ልዩ ልዩ ነው፤ መጠኑም በላይና በታች ትክክል ነው፤ ርሕቀቱም ካንዱ ነቅ እስካንዱ ሩብ ሩብ ሰዓት ያስኬድል፤ ወደ ታች ደግሞ መካከለኛው በቀጥታ ግራና ቀኙ በማሰየፍ፤ ኹሉም በየፊቱ አንዳንድ ሩብ ወይም እኩል ሰዓት ብቻ ብቻውን ይወርድና ሦስቱ ነቅዐ ማይ ካንድ ቦታ ላይ ይገናኛል። ከተገናኘም በኋላ ፩ ወንዝ በመኾን ወደ ታች ፩ ሰዓት ወርዶ፤ ማየ ሜሮም ወይም ባሕረ ሖሊ ከሚሏት ከታናሽቱ ሐይቅ ይገባና ርሷን እንደ መርከብ ማኽል ለማኽል ሠንጥቆ ዐልፎ፤ ከርሷ በታች ደግሞ ፪ ሰዓት ጐርፎ ኪኔሬትና ጌንሴሬጥ ባሕረ ገሊላ ወይም ጥብርያዶስ ከሚባለው ከታላቁ ሐይቅ ይገባል። ጥብርያዶስንም፤ አባይ በጣና ላይ እንደሚያልፈው ማኽል ለማኽል ሠንጥቆ ዐልፎ፤ ከግራና ከቀኝ ብዙ አፍላጋት እየጨመረ፤ ሮቤልን ጋድን መንፈቀ ምናሴን ወደ ግራ፤ የቀሩትን ነገድ ወደ ቀኝ ትቶ፤ ማኽል ለማኽል አቅንቶ የሦስት ቀን ጐዳና ተጐትቶ ከባሕረ ጼው አፍ ይገባና ተውጦና ሰምጦ ይቀራል፤ የባሕረ ጼው ዙሪያ ተራራና ገደል የቈላ ቈላ መቀራቅርት መትሕተ ታሕቲት ስለ ኾነ ከዚያ ሲወጣ አይታይም። የጥምቀትን ውሃ የንዋየ ቅድሳትን ዕጣቢ የተቀደሰን ፈሳሽ ነገር ኹሉ ከመሬት መቅበር የትም አለማፍሰስ የዚህ ምሳሌ ነው ይባላል። ቀድሞ በኢያሱ እስራኤል የተሻገሩበት ኋላም በዮሐንስ ጌታችን የተጠመቀበት ወደቡ ፩ ነው፤ ከዚያ በታች እስከ ባሕረ ጼው እኩል ሰዓት ወይም ፫ ሩብ ያስኬዳል። «ጌታም በዚህ ወደብ በዮርዳኖስ እግር መጠመቁ ስለ ሦስት ነገር ነው ይባላል። ፩ኛው፤ ግራዝማች ዲያብሎስ ያዳምን ዘር ኹሉ የላሜ ልጅ ያውራዬ ውላጅ ለማለት አዳም ገብሩ ሔዋን አመቱ ብሎ በደንጊያ የጣፈው ደብዳቤ ከዚያ ነበረና፤ ያነን ለማጥፋት፤ ለመደምሰስ። ፪ኛው፤ ጥምቀት የሞቱ አርኣያ የመቃብሩ አምሳል ነውና፤ ከኃጥኣን ጋራ ተቈጥሮ እንዲጠመቅና እንዲሰቀል የተጣፈውን ቃል ንስሓና ጥምቀት የሚሻ ፍጹም ኃጥእ መስሎ በዮሐንስ እጅ ለመፈጸምና ከላይ በዮርዳኖስ ነቅ የተከተትውን የጥምቀት ቀሚስ ሽልማትና ጌጥ ምስጢረ ሥላሴን ለመግለጥ። ፫ኛው፤ የአዳም ኀጢአት ካናት የፈሰሰ እስከ እግር ድረስ እንደሚሉት እንደ ታላቅ ወንዝ ነውና፤ እስራኤል ዘሥጋ ከፈርዖን ባርነት ወጥተው ዮርዳኖስን በዚህ ወደብ ዐልፈው ተሻግረው ምድረ ከነዓን እንደ ገቡ፤ እስራኤል ዘነፍስም ከሰይጣን ባርነት ወጥተው ያዳምን ኀጢአት በርሱ ጥምቀትና በኵርነት፤ በጽድቁና በትሩፋቱ በሕማሙና በሞቱ ዐልፈው ተሻግረው ወደ ሰማያዊት ከነዓን እንዲገቡ መጠን ፥ መግባታቸውን ለመስበክ ነው»። ፡-(ሉቃ፬ ፡-፲፮–፳። ፳፬–፳፯። ፬ነገ ፡-፭ ፡-፲፬)። እምአፍላግሂ ወአብሕርት እንዘ ይእቲ ነኣስ፤ ኢይትከሀል በበ ገጹ ኒጊረ ዕበያ ለዮርዳኖስ፤ አምጣነ ዳግማይ አዳም መልክአ ዚኣሃ ክርስቶስ፤ ወከመ ትኩኖ ብእሲተ አልሀቃ መንፈስ ቅዱስ ፡-(ቅኔ)።
ዮቅጣን ፡-የሰው ስም፤–ቀጠነ።
ዮቶር ፡-(ዕብ ዬቴር፤ ይትሮ) የሰው ስም፤ የሙሴ ዐማት። ተረፍ ትራፊ ቅሬታ፤ ወይም ከቍጥር ያልገባ ጭማሪ ማለት ነው፤ ትርፌ እንደ ማለት ፡-(ዘፀ፫ ፡-፩። ፬ ፡-፲፰)።
ዮናኒ ፡-ጽርእ .። የግሬክ ቋንቋ ፥ ከቅብጥ የሚስማማ የቅብጥ ጎረ ቤት ባለ፳፬ ፊደል። ቅብጡ ፯ ፊደሎች ይጨምራል፤ መለዮው ይህ ነው።
ዮናናዊ ፡-ሀዋን ዘር ፥ የግሬክ አገር ሰው።
ዮናን ፡-(ዕብ ያዋን) ፬ኛው የያፌት ልጅ፤ የግሪኮች አባት። የሀገርና የሕዝብ ስም፤ ጽርእ ግሬክ፤ ፍችው አስሓቲ መስሕት። በያዋን ፈንታ ይህያን ይላል፤ ስሕተት ነው ፡-(ዘፍ፲ ፡-፪)።
ዮን ዮና ፡-(ዕብራ) ርግብ፤ ዮን ተባቱ፤ ዮና እንስቲቱ፤ ሲያባዛ ዮኒም ይላል። ፪ኛም ዮና ዮናስ የሰው ስም ይኾናል፤ ስምነቱም እንደ ደስታ ወንድና ሴት ያስተባብራል ፡-(ስንክ ፡-ኅዳ፲፰)።
ዮዳሄ ፡-(ጽር። ዕብ ይሆያዳዕ) የሰው ስም፤ እግዜር ያውቃል ፡-(፬ነገ ፡-፲፩ ፡-፬)። ዳግመኛም በዮዳሄ ፈንታ ኢዮአዳ ይላል፤ ስሕተት ነው ፡-(፪ዜና ፡-፳፬ ፡-፪)።
ዮድ [1]፡-ስመ ፊደል፤–የወድ።
[2]፡-(ዕብ ዩድ) ስመ ፊደል፤ ፲ኛ። ፍችው እጅ ፡-(መዝ፻፲፰ ፡-፸፫–፹። ሰቈ፩ ፡-፲። ፪ ፡-፲። ፫ ፡-፳፬። ፬ ፡-፲)። በመዝሙር ዮድ ፡-(መጽ ፡-ምስ)።
ዮጊ [1]፡-እንሆ ወይ፤–የወጊ።
[2]፡-(ንኡስ አገ) እንሆ፤ አኹን ዛሬ ፡-(ይህ ጊዜ) ወይ፤ ምናልባት። ዮጊ በጽሐት። እምትሡዒ ለአማልክት ወእምዕጣነ ታዕርጊ፤ ተመትሮተ ክሣድ አብደርኪ ወኀረይኪ ዮጎ። መኑ የአምር ዮጊ በዝንቱ መዋዕል ንግሠኪ። ገሥጾ ለዐርክከ፤ ዮጊ ኢገብረ። ኢትፍቅድ ከዊነ መኰንን፤ ዮጊ ኢትክል ተበቅሎቶ ለዘአበሰ፤ ወዮጊ ታደሉ ለገጸ ዐቢይ ፡-(ሉቃ፲፩ ፡-፳። ስንክ ፡-ግን፮። አስቴ፬ ፡-፲፬። ሢራ፯ ፡-፮። ፲፱ ፡-፲፫ ፡-፲፬)። ፡-(ዕር፳ ፡-ቍ፺፮)።
No comments:
Post a Comment