~ሀ~

                                 

     -፭ኛ ፊደል በግእዝ አልፍ ቤት በአገደ፤ ስሙ ሆይ ሀውይ ጥሩ ዐምስት፤ አኃዝ ሲኾን ኀምስት ይባላል። ዕብራውያን ግን ምስትን መደብ አድርገው በራሱ ላይ ነቍጣ እየጨመሩ ዐምስት እልፍ ይሉታል ይኸውም ኀምሳ ምእት ወይም ዐምስት ሺሕ ማለት ነው ምስጢሩ ኀሙስንና የኀሙስን ፍጥረት መደብ አድርጎ ምስጢረ ጥምቀትን ያሳያል -(ዘፍ፩ -፳፫)

-ዝርዝር ጠቃሽ፤ ላንዲት ለሩቅ ሴት በሩቅ ሴት አንቀጽ ለሚነገር ኹሉ

- -የግእዝ ወራሽ ለሩቅ ወንድና ሴት ግእዙ ለወንድ ራብዑ ለሴት ራስ እየኾነ በተጸውዖ ስም ሲገባ ወደ ይኾናል ርኢ ዳምሀ ወሔዋንሃ መጣፍ ግን በጣፎች ስሕተት ወንድና ሴት ሳይለይ ለኹሉም ራብዑን ብቻ ያንባል።ዘካርያስሃ ወኤልሳቤጥሃ ሃሌታ ሊጣፍ የሚገባው በግእዝ ሲኾን፤ ሃሌ ተብሎ በራብዕ እንዲጣፍ ይህም እንደዚያ ነው።

- -( ) የግስ መል የራብዕ የሳድስ ሥረይ። የአን ፍች እይ፤ ከዚህ ጋራ አንድ ነው። ኛም -(ዕር፪ -ቍ፲፬)

ሀሀርኤል -ምሥዋዕ፤ የምሥዋዕ ደብረ አምላክ ማለት ነው -(ሕዝ፵፫ -፲፭) አሪኤልንና አርያልን እይ ከዚህ ጋራ አንድ ነው

ሀለወ -ጠበቀኀሊው ኀለወ።

ሀለየ -ዘፈነሐልይ ሐለየ

ሀለደ -ጨረሰኀልዶ ኀለደ

ሀሊል -(ሀለ የሀልል ይህልል ሎል ሄል) ማወደስ ማመስገን፤ መየበብ መዝፈን

ሀላ -ሀሊባ፤ድንኳንኦሆላ ኦሆሊባ

ሀላዊ -(ዊት ውያን ያት) የሚኖር ነዋሪ ነፍስሰ ሀላዊት ይእቲ ወኢትትዌለጥ -(ፈላስ)

ሃሌ -(ሀሌ። ዕብ ሀሌል) ሃሌታ ብሐት ውዳሴ መዝሙር ግናይ፤ ቅኔ ሐዲስ ምስጋና፤ መዘምራን ሃሌ ሃሌ ብለው የሚመሩት፤ በሃሌታ የሚዠምሩት። አንቀጽ ሃሌታ እንዲሉ -(ተረት) መዝሙር በሃሌ ነገር በምሳሌ፤ ጠጅ በብርሌ። ሃሌታና እልልታ በምስጢር አንድ ነው ለለን ተመልከት

ሃሌ ሉያ (ዕብ ሀልሉ ያህ) ብሑ እግዚአ ሀልሉ ብሑ ያህ እግዚእ አምላክ ወርኀ ሃሌ (ዘፀ፲፫ ) አቢብ ተመልከት

()          ሀልዎ ዎት -(ሀለወ ሀሎ ይሄሉ የሀሉ። ዕብ ሀያህ) መኖር መገኘት መኾን መፈጠር ኮነንና መጽአን ተመ የዚህ አግዋር ናቸው እግዚአብሔር አምጻኤ ኵሉ ዓለም ምኀበ ኢሀልዎ ኀበ ሀለ ሀለ ወኢሀለወ። ዘሀሎ ወይሄሉ ወሀሎ አሐዱ ብእሲ አለ ኖረ ነበረ -(ፈላስ ራእ፲፯ -፰። -፬። የሐ፫ -)

ሀሙዒዳ -(ዕብ ሀሞዔድ) ድሜ የተወሰነ ጊዜ ወራት የበዓል የቀጠሮ ቀን። ሄዔኪር ሀሙዒዳ -(ኤር፵፮ -፲፯) ባለብሉዮች ግን ባራ ምቱረ ሥርው ፈሪ ይሉታል

ሀሴቦን -(ጽር ሄሴቦን) ውስጠ ውስጥ ውሳጣዊ ኵሉ ክብራ ለወለተ ንጉሥ ሀሴቦን -(መዝ -፵፬)

ሀረመ -ተወሐሪም ሐረመ

ሀርበደ -(አብደ ዐረ ዐርበደ ከፋ ክፉ ኾነ) አረበደ ቸኰለ ተቈጣ እብድ እብድ ደነገጠ ደነበረ፤ ወገሸ አገረገረ ሸሸ ሮጠ ፈረጠጠ የከብት ከመ ዕጐልት እን ተሀረብድ ርበደ ፍሬም -(ሆሴ፬ -፲፮)

 -ተቀናጣ፤ ተቀማጠለ ልፍጅ አለ የዘመናይ ወለእመ ቀተለ በሀርብዶ ኢይከውን ነኔሁ ከመ ኵነኔ ብዳን -( - -፵፯) አንዳንድ መጣፍ በተሀርብዶ ይላል ስሕተት ነው

ሀበየ -ሾመ ጠበቀሐብይ ሐበየ

ሀቢብ -ወዳጅሐቢብ ሐበ ሐበበ ሐቢብ

ሀቢብ ቦት -(ሀበ ሀበበ የሀብብ ይህብብ ዐረ ሰበ) ማለት መስደብ መንቀፍ ማቃለል መጽሐፍ ግን በሀበበ ፈንታ ተሀበበ ይላል ስሕተት ነው ይትሀበቡኒ ወይዘነጕጐኒ ትትሀበቦ ዘይትጋነይ። በማእከለ ቢጹ ይትሀበብዎ ምታ -(ኤር፳ -፰። ራ፰ -፭። ፳፭ -፲፰)

ሀቢው ዎት -(ሀበወ የሀቡ ይህቡ ወሀበ፤ ሐበበ) መወጨፍ መዝነብ፤ መንፈስ መተገብ። ዝናምና ጠል መስጠት ማጥገብ ወሀበንና ሐበበን እይ የዚህ ጎሮች ናቸው።

ሀባቢ -መሀበቢ መህብብ መስተሀብብ -(ብት ባን ባት) የሚሳደብ ተሳዳቢ ነቃፊ አቃላይ ሀብ ባይ ይኩኑ ነባብያነ ወተናጋርያነ ፅሩዕ ወመስተሀብባነ -(ኪዳ። ሮሜ -)

ሀብ [1]-በል ስጥውሂብ ወሀበ ይውህብ የሀብ

 [2]-»ሀብ -( ) ንኡስ አገባብ) ትእዛዝ አንቀጽ፤ -(ወሀብከ ትውህብ) ስጥ ዐድል አሳልፍ፤ አምጣ እስኪ ና፤ በል ንበል። ሀቡ ንረድ ቡኬ ንግባእ። ሀብኬ ንትኃሠሥ በአይ ፍኖት ተወልደ። ሀባ ናመክሮን ሀባ ንፍትኖን -(ዕዝ፫ -፭። ነገ -፭። ነገ - -፳፫። ቄር -ጰላ። ሄርማ)

ሀብሀብ [1]-ዐስበ ዝሙትውሂብ ወሀበ

 [2]-»ሀብሀብ፤ -(ዕብ ሀብሃብ ጥብስ ሥጋ) የዝሙት ዋጋ ጋለሞታ የሚሰጥ -(ሕዝ፲፮ -፴፪። መጽ -ምስ) ወይም ጋለሞታ ስጥ ስጥ አምጣ ጨምር የምትል

-   ሀብለ ዋሸ ዐበለ ሐቢል ሐብለ።

ሀብለየ -በዘበዘሐብለየ ሕብልያ

»ሀብት -(ታት) በቁሙ፤ አሰጣጥ፤ ስጦታ ዕድል ፈንታ፤ ጸጋ ብዕል ምጽዋት ዳረጎት ርሻ እጅ መንሻ በከንቱ የሚሰጥ ወሀቦሙ ሀብተ ወፈነዎሙ ብትከ ልከ ይኩንከ ኵሉ ሀብ ሠናይ እምላዕሉ ሀብታተ መንፈስ ቅዱስ። በእንተ ሀብታት -(ዘፍ፳፭ -፮። ዳን፭ -፲፯ ያዕ፩ -፲፯ ፊልክ -፻፸፬ - -፳፮) ውበት ውብነት መልክ ደም ግባት፤ የተፈጥሮ ሀብት

ሀብአ -ዐባ ሸሸገኀቢእ ኀብአ

ሀትሒላ -(ዕብራ) መዝሙር ምስጋና መልአከ ሀትሒላ -(ነሐ፲፩ -፲፯)

ሀኖስ -(ጽር አኖስ ያኖስ) ከፊለ የውቅያኖስ ክፋይ ብጥብጥ ባሕር፤ የሚታወክና የሚናወጽ፤ የሚደምፅና የሚደረጽ ይኸውም ከጠፈር በላይ ያለው ሶው ውሃ ነው አንዱ እጅ ጠፈር አንዱ እጅ ውቅያኖስ እንዲባል ይህ ደግሞ ሀኖስ ይባላል -(ዘፍ፯ -፲፩። ኩፋ -፭። ሱቱ -ዕዝ፮ -፵፩) ወበውእቱ መዋዕል ይወፅእ መቅሠፍቱ ለእግዚአ መናፍስት ወይትረኀዉ ኵሎሙ መዛግብተ ማያት ዘመልዕልተ ሰማያት ወዲበ አንቅዕት እለ ትሕተ ሰማያት። ወይዴመሩ ሎሙ ማያት ዘምስለ ማያት ዘመልዕልተ ማያት፤ ማይሰ ዘመልዕልተ ሰማይ ተባዕታይ ውእቱ ወማይ ዘመትሕተ ምድር አንስቲያዊት ይእቲ -(ሔኖ -፵፩) ብዙዎች መተርጕማን ግን ፪ቱን እጅ ውሃ ጠፈር አደረገው ይላሉ እንጂ፤ ከጠፈር በላይ ብጥብጥ ባሕር አለ አይሉም።

ሀዑቢም -(ዕብራ) ወፍራሞች፤ ደንዳኖች ወፍሮች ድንዳኔዎች -(ሕዝ፵፩ -፳፮)

ሀከከ [1]-(ሆከ) አወከ አሸበረ። ሆከንና ዐከወን ተመልከት

[2]-ሀከከዐከከ ፎከተሐኪክ ሐከከ

ሀከክ -ሁክት ሽብር ክርክር ቱማታ ፍጅት። ዕለተ ሀከክ ማየ ሀከክ። በሀከክ ወበትዝልፍት እለ ይገብሩ ሀከከ ስመ በሀከክ ደርክሙ ወበሀከክ ይወድቁ ደቂቅከ -(ኢሳ፳፪ -፭። መዝ -፻፳፫ ግብ፲፱ -፴፮። ሮሜ፲፮ -፲፯። ኩፋ -)

( )         ሀካይ -(ያን ያት) የታከየ ሀኬተኛ ነፍ ታካታ ሥራ ፈት -(ምሳ -፮። -፬። ማቴ፳፭ -፳፮) በሀካይ ፈንታ ተሀካዪ ይላል። ኢትኩን ተሀካዬ -(ምሳ፮ -)

ሀኬት -በቁሙ ስንፍና ቸልታ ንዝህላልነት፤ ተንኰል ክፋት በሀኬት ወበፅርዐተ ዕደው ይወድቅ ናሕስ። እመ ዘረከባ እምሕሠማት ኮነ በሀኬተ ዚኣሁ ሶበ ተሀጕለ ንዋየ አመጋቢ በእደ መጋቢ ዘእንበለ ጽልሑት ወኢሀኬት -(መክ፲ -፲፰ - -፳፰ -)

ሀክይ -(ሀከየ የሀኪ ይህኪ ሀየየ አከየ) መስነፍ መታከት መድከም መሰልቸት ሥራ መተው መጥላት፤ መለገም ቸል ማለት መጽሐፍ ግን በሀየየ ፈንታ ተሀየየ እንዲል ሀከየም ፈንታ ተሀከየ ይላል። ዘይጻሙ በሥጋሁ ወይትሀከይ በነፍሱ። ኢናፅርዕ ቅኔ እደዊነ ወኢንትሀከይ ኢትትሀከዩ ንስሓ። ኢትትሀከይ ገቢረ ሠናይ። ኢይትሀከይ መዊተ -(አርጋ ዲድ -፲፫ ቀሌ ምሳ፫ -፳፯ ግብ፳፭ -፲፩)

ሀወለ -ቀላቀለሐወለ

ሀዊብ -(ሆበ የሀውብ ይሁብ ዕብ አዌህ) መፈለግ መሻት፤ መዞር መንከርተት ለማግኘት፤ የምግብ።

ሀዊክ ኮት -(ሆከ የሀውክ ይሁክ ዐከወ ሀከከ) ማወክ መነቅነቅ ማንቀሳቀስ ማገበር መጐስጐስ ማነሣሣት ማሳዘን ማስጨነቅ ባለመከራ ማድረግ። ሆኮሙ ከመ ማዕበለ ባሕር ተክህሎሙ ከመ ይሁክዋ ለሐመር እመካና ተመሰሎሙ እለ ይለክፉ ምንተኒ በአጽባዕቶሙ ወየሀውኩ ኵለንታሁ ሆከቶ ጸጋ እግዚ ከመ ይሑር ኀበ ገዳመ ስቄጥስ ፈቃድከ ትሁክ ቅድስተ ሲኖዶሰ የሀውኮሙ ለአሕዛብ -(ሢራ፳፱ -፲፰ ንክ -ኅዳ፳፰ አፈ -ድ፪ ስንክ -ጥቅ፳። ተረ -ር፲፪ ኢዮ፲፪ -፳፫) ሖሰንና ኮሶን እይ የዚህ አግዋር ናቸው

ሀዋኪ -(ኪት ክያን ያት) የሚያውክ አዋኪ ሁከተኛ ነቅናቂ በጥባጭ። ሀዋኪ በግዕዙ ሞገድ ዋኪ ጸልዩዪ ውስተ ማኅበርነ ይባእ ሀዋኪ -(መጽ -ምስ ተረ -ቄር ደራሲ)

ሀውል -(ዕብ ሄቤል) ላበት እንፏለት ሞቀ ገላ ካፍ የሚወጣ ከንቱ ነገር ዕብለት፤ ዋዛ ዛዛ ሥላቅ፤ ስድብ ነቀፋ።

ሀውለየ -(ተቀ ) አፌዘ ሣቀ ተሣለቀ ነቀፈ ሰደበ አረከሰ ከንቱ አደረገ ከመ የሀወልይዎ ለእግ ወእለ ጸጋ ትስብእቱ ይመይጡ ውስተ ሀውልዮ ተሀወልዮኑ ለእግዚ ቃል በዘሐመ። ተሀውልዮ ለዐቃቤ ሥራይ እመ በትሕትና አሕየወ የሀውልይዎኬ ክርስቶስ ኃጥኣን ኢተሀውሊኬ ሕማማቶ እመ አረሚ ሀውለይዎ ለምስጢር -(ተረ - ፭። ፲። ፲፰)

ሀውክ -በቁሙ፤ ሁከት እውክታ ንውጽውጽታ መከራ ጭንቅ፤ ሽብር ድብልቅልቅ። ሀውከ ሞገድ። ከመ ያህድእ ኵሎ ውከ ወሐዘነ -(ተረ -ቄር፬ -፲፬ ሔኖ፴፱ - ያዕ፫ -፲፮)

ሀየለ -በረታይሎ ኀየለ።

ሀየል -(ላት። ዕብ አያል ሱር አያላ ዐረ ኢየል) ዋሊያ ዋላ፤ ቀንዳም ቀንደ ገላላ፤ ባለብዙ ዐጽቅ ባለተቀጥላ፤ ነዊኀ ፅም እግረ ሽመላ የፌቆ ወገን የበረሓ እንስሳ። ዘያረትዖን ከመ ሀየል ለእገርየ ወከመ ወሬዛ ሀየል ህየ ተጋብኣ ሀየላት ስመ ሀየል ቀታሊሁ ለከይሲ። ሀየላት ወለዳ በውስተ ገዳም -(መዝ -፲፯ ማሕ፪ -፱። ተረ -ቄር፰ ኤር፲፬ -)

 

 

ሀዪድ ዶት -(ሄደ ሀየደ የሀይድ ይሂድ) መቀማት መንጠቅ በምክንያት መውሰድ እነሥአከ ወአሀይደከ ወየሀይደክሙ ራህተክሙ ትትዐገሉ ወኢትሂዱ መነሂ -(፩ነገ - -፲፪ -፲፬ ሉቃ፫ -፲፬)

 -ማንጸብረቅ፤ መሳብ መበዝበዝ ብሰ ዳዊት ዘየሀይድ ዐይነ አሣእኒ ሀየደ አዕይንቲሁ። ዕበየ ብርሃኑ የሀይድ ዕይንተ -(፪ነገ - -፲፬ ዮዲ፲፮ -፱። ቀሌ)

 -መሄድ መራመድ እግርን ማንሣት መንጠቅ ምስጢሩ ያው መውሰድ ነው፤ ኬደ መርገጥ መደፍጠጥን ሄደ አነሣሥን ያሳያል፤ ኬደ ሖረ የግእዝ ሄደ ያማርኛ። ነጠቅ ነጠቅ አርግ እንዲሉ ቶሎ ሂድ ሲሉ

ሀዪጵ ጶት -(ሄጰ የሀይጵ ይሂጵ ዐረ ሀበ ሀፈ) መነቅነቅ መስበቅ የሾተል የጦር። መሳብ መንደፍ፤ መወርወር ማወንጨፍ መውጋት መግመስ መፈንከት ይጶተ ቀስት ወደርብዮ ኵያንው ደፈ ወሄጶ ለንጉሥ ማእከለ ንብዑ ፈነወ ሐጾ ወሄጶ ጥቦ የሀይጱ ሥዕርተ ወኢይስሕቱ ወፀፎ በእብን ወሄጶ ውስተ ፍጽሙ -(መቃ -፲፬ ፪ዜና -፲፰ -፴፫። ኩፋ -፴፰። መሳ፳ -፲፮ ሢራ፵፯ )

ሀያዪ -(ተሀያዪ) ቸል ባይ ቸልተኛ፤ ጋሽ። ጳውሎስ ሐዋርያ ኮነ ተሀያዬ ስብሐተ፤ ሳረ ወጽዕሰተ -(ፊልክ -፵፮። ፶፬። ፻፩)

ሀያዲ -(ዲት ድያን ያት) የሚቀማ ቀማኛ፤ ነጣቂ ወሳጅ -(ሉቃ፲፰ -፲፩ ፩ቆሮ - - -፲፩። -) ምእደ ሀያዲሁ ሀያዴ ንዋየ ባዕድ። ሰራቂ ወዐማፂ ወሀያዲ ወመሣጢ ሀያድያን -(ኤር፳፪ -፫። ቀሌ - -፲፯ - - -፵፭)

ሀይመነ -(ሱር ሃይሜን ዐረ ሀይመነ) አመነ ታመነ። ንባቡ የማን ፍችው ከአሚን የወጣ ነው፤ የመነንና አይመነን ተመልከት።

ሀይማኒ -(ኒት ንያን ያት) ያመነ የሚያምን፤ የሚታመን፤ አማኒ ተአማኒ

ሃይማኖተ አበው - የሊቃውንት መጽሐፍ ድርሳን መልእክት የኋላ ሰዎች ከየመጣፉና ከየቋንቋው ለቅመው ተርጕመው እንደ ፍትሐ ነገሥት ለብቻው አንድ ክፍል መጣፍ ያደረጉት ታላቅ ምእላድ፤ ቅዳሴ ጊዜ የሚነበብ

ሃይማኖተ ንስጡር -ንስጥሮሳዊ ባህል እንደ አይሁድ እንደ ሙሐመድ ቃል ሥጋ ኮነን የሚነቅፍና የሚያጸይፍ፤ ቃል በሰው ዐደረ እንጂ አልኾነም ሰው ኹኖ አልተቀባም ብሎ የቃልን መኾን መሲሕነቱን የሚክድ -(ቄር)

ሃይማኖተ እስላም -እስላማዊ ባህል፤ ራሽ ትምርት ኦሪት ከወንጌል የማይገጥም -(አቡሻ -)

ሃይማኖት -(ሱር ሃይማኑታ) የዑደት የምሕላ ጸሎት ከቤተ ክሲያን ውጭ በዙሪያው በገረገራው የሚባል፤ እንደ ጥምቀት እንደ ጕዞ ፍታት ያለ ወረብ ለዘብ፤ የታቦት ዘፈን። ሀይመና ሀይመን እንዲል -(ያረርጌ ጨፋሪ)

 -በቁሙ፤ ማመን መታመን፤ እምነት ጽኑ ተስፋ የአምልኮት ባህል በልብ በረቂቅ ሐሳብ የሚሣል ሃይማኖተ ዕቁብ ምስለ ቢጽከ ብእ ዘተአምር ከመ ሃይማኖት። እለ አዕረፉ በሃይኖተ  ክርስቶስ -(ሢራ፳፪ -፳፫ ፳፯ -፲፪ ዲድ -፴፬)

ሃይማኖት ርትዕት -ኦርቶዶክሳዊት የኦርቶዶክስ ባህል -(ቅዳ)

ሃይማኖት ቅድስት -ምስጢረ ሥላሴ ምስጢረ ሥጋዌ -(ይሁ -)

ሀይከል -(ዕብ ካል ሱር ሄካላ ዐረ ሀይከል) ታላቅ ቤት አዳራሽ ሰቀላ ቤተ መቅደስ ከዚያውም ፵ው ክንድ መካከለኛው ክፍል፤ ጽርሕ ሀይከለ ድስ -(ዮሴፍ)

 -መቅደስ ምሥዋዕ መንበረ ታቦት በተገናኝ ማደሪያ ማለት ነው ሲያበዛ ሀይከላት፤ ሀያክል ይላል።

ሀይብ በቁሙ ዐይብ ሔበ ሐይብ።

ሀይወ -ዳነሐዪው ሐይወ

ሀይይ ዮት -(ሀየ ሀየየ የሀይይ ይህየይ ሀከየ) ቸል ማለት፤ መናቅ ማቅለል መተው መጣል። መጽሐፍ ግን በሀየየ ፈንታ ተሀየየ ይላል፤ አያሰኝም ኢትትሀየይ ትእዛዘ ምከ ተሀየዩ ሥርዐተ። አሙንቱ ተሀየዩ ወኀለፉ። ትትሄይ ኀጣይአ ሰበእ ለዕቡያን ይትሄየዮሙ እግዚ -(ምሳ፩ -፯። ቀሌ ማቴ፳፪ -፭። ጥበ፲፩ -፳፬ ያዕ፬ -፮።

ሀይድ -ቅሚያ ንጥቂያ ምክንያት ያለው አውሳሰድ -(መዝ -፷፩። ኢሳ፷፩ -)

ሀደመ -ተረተሐድሞ ሐደመ

ሀደየ -(ዐረ ሀደይ) አበሰለ አሟከከ የሥጋ ያጥነት የሚቀቀል ኹሉ

ሀዲም ሞት -(ሀድመ፤ ሀደመ የሀድም ይህድም። ዕብ ራዳም) ማንቀላፋት በንቅልፍ መያዝ መወሰድ፤ መስነፍ መታከት እንቅልፋም መኾን። መጨለም መክበድ፤ ሌሊት ውድቅት መኾን የጊዜ። መጽሐፍ ግን በሀድመ ፈንታ ተሀድመ ይላል ዘኒ ተሀድሙ። እምቅድመ ይብራህ ብርሃነ መዓልት ወእምቅድመ ይትሀደም ሌሊት -(ዕዝ፮ -፴፩ ቅዳ -አፈ)

ሀዲእ ኦት -(ሀድአ የሀድእ ይህዳእ ዐረ ሀደአ) ዝም ጸጥ ማለት ሁከት ማረፍ፤ መርጋት መጨመት መቆም መገታት ዝኅነን ተመ የዚህ ጎር ነው ወሀድኡ ይሁድ በመዋዕለ ስምዖን ውእቱሰ ኢይትናዘዝ ወኢየሀድእ ሀድአት ልባ ምሐዘን በመዋዕሊሁ ሀድአት ወአርመመት ምድረ ይሁዳ። ዝኅነ ሞገድ ወሀድአ ማዕበል -(ዮሴፍ። ስንክ መስ፳፰ ዜና -፲፬ -፩። መጽ ምስ ዘፀ፬ -፳፰፴፬) ዳታ ዳተኛ ማለት ከዚህ ወጥቷል

ሀገሪታዊ -ዝኒ ከማሁ፤ ጀም አረመኔ። ጽሑፍ አልቦ ውስተ ልበ ንጹሓን ፍልጠት ማእክለ ይሁዳዊ ወሀገሪታዊ ገብር ወአግዓዚ -(ፊልክ -፹፯)

ሀገሪት -ያቀኗት የቈረቈሯት፤ የተወለዱባት ገር ርስት ጕልት ወዳጅ ዘመድ፤ ዐብሮ አደግ ያገር ሰው ተወራራሽ ወንድም በላ ጥበብ እኅትየ አንቲ ወለአእምሮ ሀገሪተከ ረስያ -(ምሳ፯ - )

 -አንባ ኰረብታ ርድ ምሽግ ሀገሪት ይእቲ ለኵሎሙ እለ ይቀርብዋ -(ምሳ፫ -፲፭)

 -ማኅበር ጉባኤ፤ ድርገት እንዘ ሀለዉ በምድር ሀገሪተ ይኩኑ ምስለ ሰማያውያን -(ቀሌ)

 -ባላገር ባለጌ፤ አረመኔ ያልተማረ ያልሠለጠነ ጀም። ሐቃል ወኢሀገሪት -(ቆላ፫ -፲፩)

ሀገራዊ -ያገር ባላገር ባላባት አቅኚ ማግሌ፤ አውራ ቀንድ፤ ወይም ዕድር፤ ልማድ -(ተረት) ያገር ዕድር ለንጉሥ ያስቸግር ምግብና ሀገራዊት -( - -)

ሀገር -( አህጉ() ር፤ ራት) በቁሙ፤ አገር መንደር፤ ከተማ ገጠር ብዙ ቤቶች የተሠሩበት ብዙ ዎች የሚኖሩበት፤ በያቅኝውና በየክፍሉ ገዥ አዛዥ፤ ዳኛ መልከኛ ያለው፤ ታላቁም ታናሹም ኢትክል ተከብቶ ሀገር እንተ ተሐንጸት መልዕልተ ደብር ገር ቅድስት ሀገረ እስራኤል ውስተ አህጕር ወአዕጻዳት -(ማቴ፭ -፲፬ ሢራ፳፬ -፲፬።ኤር፫ -፰። ማር፮ -፴፮)

ሀገየ -ባጀሐግይ ሐገየ ሐጋይ

ሀጕል (ላት) ጥፋት ጕዳት ችግር ጦት ፍኖት እን ትወስድ ውስተ ሀጕል ወልደ ሀጕል። ሀጕ ዐቢይ በሀጕልክሙ እሥሕቅ (ማቴ፯ ፲፫ ዮሐ፲፯ ፲፪ ግብ፳፯ ምሳ፩ ፳፮) አጥፍኦ አህጕሎ በማለት ፈንታ ሀጕል ይላል ጊዜ ለኀሢ ወጊዜ ለሀጕል (መከ፫ )

ሀጕል ሎት -(ሀጕለ ሀጐለ የሀጕል ይሀጐል) ማጣት መቸገር፤ የያዙትን የረዘዙትን፤ ወይም የሹትን የተመኙትን አለማግኘት ከመ ትህጐል ርስተከ ህጐል ወርቀከ ምትህጐል ርከከ ሀጕለ ዕይንቲሁ ጦቢት ሀጕሉ ዕሌቶሙ። የሀጕሉ ተስፋሆሙ -(ሢራ፬ -፮። ፳፱ -፲። ቢ፯ -፯። ማቴ፮ -፪። ዲድ -፳፭)

ህጕሬ -ቀይ ቀለም፤ሕጕሬ

ሀጊር ሮት (ሀገረ የሀግር ይህግር ዕብ ሀጌር) ዲስ ቦታ መሻት መፈለግ መመርመር ማቅናት መቈርቈር ምንጩን መማስ ዱሩን መጣስ መከተም መመንደር መዲና መሥራት

ሀጊናህ -(ዕብራ) የቀና ቀጥ ያለ፤ የተካከለ ባለዕርከን ፍኖተ መዘምራን -(ሕዝ፵፪ -፲፪)

ሀግረተ -(ተቀ -ተጋ ዐሰ ተወዘወዘ በትጋት በሐሳብ ተያዘ በሀግረተ ፈንታ ጋህረተ ይላል፤ የጣፊ ስሕተት ነው። ከመ ትትጋህረቱ ለመፍቅደ ልብየ -(አርጋ -)

ሀፊው ዎት -(ሀፈወ የሀፉ ይህፉ ዐረ ሀውፍ ሁፍ ውዑይ ነፋስ) መውዛት መድከም፤ መሞቅ በላበት መጠመቅ ፈተወት ትትኀፀብ፤ እስመ ሀፈወት። ስከ የሀፍዉ ጾመ ወጸለየ ደክመ ወሀፈወ። በጸዊረ መስቀሉ ፈወ፤ እስመ ክቡድ ውእቱ -(ዳን፩ -፲፭። ሥር -ጳኵ ግንዘ ቅዳ -ግሩ)

ሀፍ -(ዕብ ዚዓህ) ወዝ ላበት፤ ድካም -(ዘፍ፫ -፲፱ ሉቃ፳፪ -፵፬) ብዝኀ ስግደተ እስከ ይውሕዝ ሀፉ ከመ ማይ ዘእንበለ ጻማ ወሀፍ። ፈንዉ ሲሳዮሙ እምንዋይክሙ ወሀፈ ገጽክሙ -(ገድ -ተክ አፈ -ተ፫ ዲድ -፳፭)

 -ሙቀት ሐሩር ቍር ወሀፍ። ብሔረ ጽምእ ወሀፍ ሀፍ ወሞቅ -(ዘፍ፰ - ዘዳ፴፪ -፲። ሔኖ፹፪ -፲፮)

ሀፓሊ -መሀፕል መሀፒል፤ እየመታ የሚያጥብ ዐጣቢ። ገራህተ መሀፒል። ዘኢይክል መሀፒል አጻዕድዎ ከማሁ -(ኢሳ፯ -፫። ፴፮ - ማር፱ -)

ሀፐለ -(ዐረ አበለ፤ ወበለ) ዐጠበ መታ ደበደበ በመርገጥና በመጠቅጠቅ ፈንታ በዱላ እየመቱ የሚያጥቡት ዕጥበት አለና፤ ጥበቱንም። አመታቱንም ባንድነት ያሳያል

[1]-ሁ፤ -() ጥያቄ የጥያቄ ቃል ንኡስ አገባብ ፍችው በቃል መጨረሻ እንደ ዝርዝር ትራስ እየኾነ ይገባል። ኢኮነሁ ምኔሁ ይሴወር። ትስአሉኒሁ መጻእክሙ -(ዓሞ፪ -፲፩። ኢዮ፴፰ -፯። ሕዝ፳ -) ቦሁ አመ ነገሩክሙ። አልቦሁ አንበብክሙ ኮሁ ዘአወልድ እያለም በነባር አንቀጽ ይገባል ደግሞ በገባበት ይገባል አገባቡን በቦታው እይ ንዳንድ ጊዜም ምናልባት ይኾናል። እመሰ ትብሉሁ ሶበሁ የአምር በዓለ ቤት አንተሁ ክርስቶስ -(ኢሳ፷፮ -፯። ማቴ፳፬ -፵፫። ፳፮ -፷፫)

   [2]- -(ውእቱ) ባዕድ ዝርዝር ቃሽ፤ ጸፋ ምእላድ ላንድ ለሩቅ ወንድ በሩቅ ወንድ አንቀጽ ለሚጠራ ኹሉ ርሱ ማለት ነው ብእሲሁ፤ ሰውዮው ሆሙ ሆን እያለ በሩቆች ብቻ ይረባል ኪያ ኪያሁ ለል ለሊሁ ቅድሜሁ ድኅሬሁ ቀደሳሁ ወደሳሁ የመሰለው ኹሉ ዝንቱ ከዘ እንደ ወጣ ውእቱም ከሁ ወጥቷል የርባታ መደቦች የሚባሉ ሥሩ ሰራዊት ሳይቀሩ ኹሉም የሁ ዘር ናቸው።

ሁል ርኵስ ሐዊል ሖለ ሐወለ ሑል

ሁስጱ -(ጽር ሒሶፖስ) የቀነበጥ ችቦ ለባልብ። አዛብን ተመልከት ከዚህ ጋራ ለብሉዮች ግን ለይተው ስምዛ አሸክት ይሉታል ጽለ ሁስጱ ሐምለ ሁስጱ -(ዘሌ፲፬ - -፯። ነገ - -፱። ዮሐ፲፱ -፳፬ ዕብ፱ -፲፱)

ሁከት -(ታት) ቁሙ፤ ማወክ መታወክ፤ መታመስ መተራመስ ብር። ሁከተ ማይ ተሀውኩ ዐቢየ ሁከተ ሁከተ ፍስ። ቃል ወሁከት ሰይጣን መፍቀሬ ሁከት። ከመ በድምፀ ምጽአትከ ይኩን ሁከት -(ዮሐ፭ -፫። ሔኖ፰ -፩። ጥበ፲፯ -፰። አስቴ -፩። ቀሌ ኪዳ)

ሁጅራ -(ዐረ ሂጅረት) ሠግር፤ ቀመር። ዓመተ እልሁጅራ -(አቡሻ -፲፩)

-() ዋዌ ፍችው ደግሞ ግን ስንኳ ወይም እያለ ብቻውንም ከወም ጋራ ይገባል ነኒ ንተሂ ቡየሂ ወአነሂ መሂ ሠርከ ወእመሂ መንፈቀ ሌሊት ከሃሊ ንሰ ተጽናሰሂ ወተደልዎሂ ርኂበሂ ወጸጊበሂ ሐሚመሂ ወተፈሥሖሂ -(ፊልጵ፬ -፲፪) ግንና ስንኳ ሲኾን አገባቡ እንደ ነውና የወን አፈታት ተመልከት

ሂደት -መቀማት -(ጥቀ) መቀማት አቀማም ወሳሰድ ቅሚያ ንጥቂያ -(አርጋ) መሄድ መራመድ አካሄድ አረማመድ፤ እግር አነሣሥ።

ሂጰት -መንደፍ መነደፍ፤ አነዳደፍ ነደፋ ውርወራ ድፊያ ውጊያ ውግታት ግምሳት። አኮ በዘቀስት ሂጰት -(ቄረ -ገ፯)

[1]-ጊዜ ወገን ማእዝን ዙሪያ እየኾነ ከኵል ጋራ ይነገራል ልን ተመ ከአሐቲ በቀር በሌላ እንዳይገኝ ደግሞ ከኵል በቀር በሌላ አይገኝም።

[2]-ሄ፤ -(ዕብ ሄእ) ፊደል ኃምስ ሀ። እንሆ እንካ ማለት ነው -(መዝ፻፲፰ -፴፫፵። ሰቈ -፭። -፭። -፲፪። -) ህና እንደ ሌሎቹ የተለየ ሥራ የላቸውም።

ሄላ -የወይን ዘለላ የበሰለ ደሙ የመላ ጥባትኪ ከመ ሄላ ዘእምኔሆን ይውሕዝ ሐሊብ -(አርጋ። ማሕ፯ -) እኄላን የዚህ መንቲያ ነው ባለብሉዮች ግን ምንጭ የበለስ ቋንጣ የሰሌን ፍሬ ይሉታል። ንባቡ ሀየላዊ፤ ምስጢሩ መስተፍሥሒ ከመ ሀየል። አስካል ሄላ መባሉ በምላሴ እንጂ ቃል በቃል አይዶለም

ሄላንሳን -ክቡር ልብስቂላኖስ

ሄሴፎት -(ዕብ ሀአሲፎት) የጥራጊ የጕድፍ መጣያ፤ ያዛባ የፍግ መቈለያ ባለብሉዮች ግን ግናይ ይሉታል ንቀጸ ሴፎ -(ነሐ፲፪ -፴፩)

ሄርማ -የመጽሐፍ ስም፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የጣፈው እንደ ሣልስ ቆሮንቶስ ያለ ከቍጥር ያልገባ ትርፍ፤ ወሪድየ ብሔረ ሮሜ ብሎ የሚዠምር ስምነቱ ርሜን ከማለት የወጣ ነው ሄርሜናዊ ያሰኛል ጸሓፊው ሄርሜን ስለ ተባለ መጽሐፉም ሄርማ ተብሏል

ሄርሜን -(ጽር ርሚን) ጣዖ ስመ ጣዖት በመንታ መንገድ ላይ የሚያቆሙት መሪ አስተማሪ፤ ትርጁማን አፈ በሃማን ማለት -(ግብ፲፬ -፲፪)

ሄሮድስ -(ዕብ ሆርዶስ) የሰው ኤዶማዊ የእስራኤል ንጉሥ፤ በዘመነ ልደት የነበረ -(ማቴ፪ -)

ሄሮድያኖስ -(ጽር ሄሮዲዎስ) ያሞራ ስም ሽመላ ሽመላዊ እግረ ሽመል ዐንገተ ግመል እግሩ ሽመል የሚያካክል። -(ተረት) ካህንና መላ ያልዘራውን ይበላ ሄሮድያኖስ በሰማይ የአምር ድሜሁ -(ኤር፰ -፯። ዘሌ፲፩ -፲፱ መዝ -፻፫ ዘካ፭ -)

ሄዔኪር -(ዕብ ሄዔቢር) አሳለፈ አሻገረ፤ አስተላለፈ የጊዜ የወራት ሐተታውን በቢዶን ፍች እይ፤ ባለብሉዮች ግን ደካማ ዘበጽሐ ጊዜሁ ኅሱር ይሉታል -(ኤር፵፮ -፲፯)

ሄከ -አላመጠሐዪከ ሔከ

ሄጠ -ሸነገለኀዪጥ ኄጠ።

ሄጰ -ወጋ ገመሰሀዪጵ።

ሄጶዲያቆን -(ጽር ሂፖዲያኮኖስ) የዲያቆን ተወራጅ፤ ንፍቀ ዲያቆን -(መጽ -ምስ)

ሄጶዴጤን -(ጽር ሂፖዲቲስ። ዕብ ምዒል) ልብሰ ክህኖ የላይ ልብስ ታላቅ ሚስ እጀ ሰፊ ቋረፊያ ጶዴሬን እይ ከዚህ ጋራ ነው -(ዘፀ፴፮ -፴። ዘሌ፰ -)

ሄጶጳ -(ጽር ሄፖፓ ሄፖፕስ) ንኡስ፤ መጠኑ የርግብ የዋኖስ ቍንጯም

ረዥም የሾለቅ ዐይነት ዝንጕርጕር ኰሳኵስ። ባለብሉዮች ግን ዐቢይ ሞራ ይሉታል -(ዘሌ፲፩ -፲፱ ዘዳ፲፬ -፲፰)

ህሉና ህልውና -ነዋሪነት አነዋወር ኑሮ። ህሉና ሥላሴ። ህሉና መለኮት -(ቅዳ)

ህላሊ -ሠርቃዊ ወርኃዊ የጨረቃ ወር ውራኀ ህላል ህላሊ -(አቡሻ -፳፭)

ህላል -(ዐረ ሂላል) ርቀ ወርኅ፤ ልደተ ወርኅ ሐዲስ ለጋ ጨረቃ

ህላዌ -(ውያት) መኖር መኾን አናዎር ኑሮ ንዜኑ ህላዌሁ ለአብ ምስለ ወልዱ ወህላዌሁ ወልድ ምስለ አቡሁ። ሠለስቱ ህላዌ በአካላት ወአሐዱ ህላዌ በመለኮት -(ቅዳ -ግሩ አበ ባለ) ይህ ቃል ለሦስቱ ኹሉ የተለየ የአካል ህላዌና ግብር እንዳላቸው ያሳያል ትርጓሜውም ይህ ነው። ወላዲ የአብ አካል መውለድ ማሥረጽ ግብሩ ከዊነ ወላዲ ወይም ወላዲነት ህላዌው፤ ባማርኛ ባሕርይ ይባላል ልዩነት ያለው ገጽ ቁመት አቋቋም መልክ ማለት ነው። ተወላዲ የወልድ አካል መወለድ ግብሩ፤ ተወላዲነት ህላዌው። ሠራጺ የመንፈስ ቅዱስ አካል፤ መሥረጽ ግብሩ፤ ሠራጺነት ህላዌው ለስቱ ህላዌ ይህ ነው ወአሐዱ ህላዌ ያለውም መውለድና ማሥረጽ መወለድ መሥረጽ በዚያው ባንዱ ባሕርይ ባን መለኮት ነውና፤ ባሕርይ የሦስቱ መሣሪያ መኾኑንና ንድነቱን መደብ ድርጎ እንደ አካላት ወላዲ ተወላዲ ሠራጺ አለመባሉን ያሳያል ምስጢሩ፤ ባሕርይ ሳይከፋፈል አካል ሳይቀላቀል ስምና ግብር ሳይፋለስ የአካል ህላዌ ሳይፈርስ ባንድነትና በሦስትነት ጸንቶ መኖር ነው መለኮት የሚሉ ግን ወላዲ ባሕርይ ተወላዲ ባሕርይ ሠራጺ ባሕርይ እያ የአካላትን ስምና ግብር ለባሕርይ ሰጥተው ይፈታሉ

 [1]-አካል ገጽ፤ አቋቋም ቁሙት፤ ኳኾን ኹነታ አካል ማለት ባሕርይና ግብርን መልክንና ስምን ኹሉን ብስቦ የሚይዝ ብሳቢ ገዥ አዛዥ ባለቤት ማለት ነው፤ የአካልን ፍች ተመልከት። እግዚአብሔር በዓለ ሠለስቱ ህላዌ ሐዱ በባሕርይሁ ወሥልጣኑ ወመለኮቱ እስመ አበዊነ መይዎ በዝንቱ ገጸ መካን -(በአንቀጸ ተዋሕዶ) ለህላውያት አካላተ ትናቴዎስኒ ረሰየ ህላዌ አሐደ አካለ ዘእግዚአብሔር ቃል ዘተሠገወ ስመ ህላዌ ይትበሀል በእንተ ክዋኔ ወአካል ወክዋኔሂ ይትበሀል ከመ ውእቱ ህላዌ ዘያስተጋብእ ኵሎ፤ ወአካልሰ ዘአሐዱ ህላዌ ውእቱ ተውሕዶ አንድ የኾነ አካል ማለት ነው ገጽ አቋቋም ቁመት ያልነው አካል ባሕርይ ይባላል፤ አካል ያለገጽ ያላቋቋም አይገኝምና። እስመ በዝየ ይሰመይ አካል ህላዌ ካሉ ወልድ ወአኮ ውእቱ ህላዌ ያስተጋብኦሙ ሥሉስ ቅዱስ፤ ወበእንተ ተሠገወ እግ ቃል -(አክሲ ሃይ -አበ -ብን ዲዮ መቃር) ላዌን የአካል ባሕርይ ማለት አካልን አቋቋም ብሎ ነው

[2]-ባሕርይ ጠባይ ብሕረንና ጠብዐን ተመልከት ኅቡረ ህላዌ ምስለ በመለኮቱ ኅቡረ ህላዌ ምስሌነ በትስብእቱ። ወኢተወለጠ ህላዌ ቃል ኀበ ህላዌ ሥጋ ወህላዌ ሥጋ ኀበ ህላዌ ቃል ዳእሙ ይሄልዉ ክልኤቱ ህላውያት በበ ህላዌሆሙ እንበለ ውላጤ -(ተረ -ቄር ሃይ -አበ መጠሊ)  ህላዌ በአንቀጸ ተዋሕዶ አካል ስለ ኾነ አሐዱ እንዲባል በአንቀጸ ተዐቅቦም ባሕርይ ስለ ኾነ ክልኤቱ ይባላል፤ እውነተኛው የሊቃውንት ዐዋጅ ይህ ነው ወኢተዋሐደ በመንፈቀ ህላዌ ወኢኮነ ካልኦ እንስሳ በአንትጎ አላ ምሉእ ወፍዱም በአሐዱ ህላዌ ይገብር ዘክልኤቱ ህላውያት -(ሃይ -አበ -ኤፍ) አሐዱ ያለው አካል ክልኤቱ ያለው ባሕርይ እንደ ኾነ አስተውል።ባሕርያት እንደ ሆኑ የባሕርያት ፍሬ ግብራትም ናቸው ተወላዲው አካል ሲኾን ልደቱ እንዲባል ግብሩም ሠሪው አንድ ሲኾን እንደ መሣሪያው እንደ ባሕርይ ይባላል። ግብርን አሐዱ ማለት ልደትንም አሐዱ ያሰኛል፤ ልደት ቅሉ ግብር ነውና መባሉ ስለዚህ ነው ግብር ባሕርይን፤ ገቢር አካልን ይከተላል ቦቱ መንክራት ወዓዲ ቦቱ ሕማማት ወውእቱ ሐዱ ህላዌ፤ በመለኮቱ ይገብር መንክራተ ወበትስብእቱ ይትዌከፍ ሕማማተ ርኢከኑ ዘከመ እፎ ሎቱ ክልኤቱ ግብራት ኅቡረ ወዐቀበ እሎንተ ክልኤተ ብራተ በኵሉ ዘመን ወኢንቤ ከመ መንክራት ለአሐዱ ወሕማማት ለካልኡ አላ ሙንቱ ለዝንቱ ሐዱ ባሕቲቱ ከመ አምላክነ ወእግዚእነ የሱስ ክርስቶስ ሐዱ አካል ሥግው ወአሐዱ ህላዌ ዘኀብረ ኵለንታሁ ወልድ ዘውእቱ ቃል ወነፍስ ወሥጋ ወልቡና ወምግባር ህላዌ ዘኀብረ ኵለንታሁ ያለውን ቃል ሥጋ ነፍሰ ልቡና ምግባር ብሎ ቈጠረ፤ ልቡና ምግባር የሌለው ሌላ ህላዌ ይኾናል እንጂ የሰው ህላዌ አይባልምና -(ሃይ -አበ -ጎር ኤጲ መቃር)

[3]-ቅላይ ስም፤ ኵላዊ አስተጋባኢ ስምነቱ ካቶሊክ እንደ ማለት ነው ፈጣሪ ሳይቀር በሰማይ በምድር ላለ ፍጥረት ኹሉ ይነገራል ወአእአምሩ እስመ ስመ ህላዌ ይትበሀል በገጸ መካን ህየንተ ህላዌ ኵሉ ዘመድ -(ሃይ -አበ -ዲዮ) አስተጋባኢ ስም ስለ ኾነ እንደ ጠባይዕ ለአካል በሚመችበት ካል ለባሕርይ በሚመችበት ባሕርይ ይባላል። ባማርኛ ሌላ ታጥቶለት እንጂ በአካልና በባሕርይ መካከል ሌላ የተለየ ማእከላዊ ስም ያስፈልገው ነበር። በምድር ያለ የፍጥረት ኹሉ ሥር አራቱ ባሕርያት ናቸው ማይ መሬት ነፋስ እሳት እሊህ አራቱ እየተዋሐዱ ሌላ ይነት ባሕርይ፤ ሥጋን ዕንጨት ያስገኛሉ የተለየ የባሕርይ ሥጋ ዕንጨት ነው ራቱ ባሕርያት ተውሕዶ ሥጋ ኹኖ ዕንጨት ኹኖ የቆመበት ውሳጣዊ አስተጋባኢ ስሙ ህላዌ ተብሏል «ጽርኣውያን ህላዌን ወስያ፤ ባሕርይን ፊሲስ ይሉታል። ላቲናውያንም ህላዌን ሱብስታንስያ ባሕርይን ናቱራ ይሉታል» አካል ለባሕርይ አይነገርም ባሕርይም ለአካል አይነገርም ህላዌ ግን ኹለቱ ንድ ኹነው የቆሙበት አስተጋባኢ ስም ስለ ኾነ ለኹለቱ ኹሉ ይነገራል የወጣበት የስምነቱ ምስጢር ግን አጥብቆ አጥልቆ ሲመረመር አኳዃንንና አቋቋምን የተዋሕዶውን ጽናትና አናዎር ያሳያል እንጂ አካልን ብቻ ባሕርይንም ብቻ አያሳይም። የንጨት ኹሉ ባሕርይ አንድ ሲኾን ህላዌው እየቅል ነው ብርቱ አለ ግብዝ አለ ካራቱ ባሕርያት የተፈጠረ ኹሉ እንዲህ ነው የመላእክትና የነፍስ ባሕርይ ግን መሠረት የለውም እምኀበ አልቦ ነው፤ መላእክትን ዘይሬስዮሙ መንፈሰ ወነደ እሳት ቢላቸው የሚራቀቁ የሚማወቁ ተለኣክያን ማለት ነው እንጂ እኛ ከምናውቀው ነፋስና እሳት ማለት አይዶለም፤ ከዚህስ ቢኾን እንደ መጠኑ ባየናቸው በሰማናቸው ነበር። አካላውያን ኹነው ተፈጥረዋል ባሕርያቸው ከአካላቸው አይቀድምም የአካላቸው አኳኾን ህላ ይባላል፤ የነፍስም እንደ መላእክት ነው። የነፍስ ባሕርይ ወደ ሥጋ ባሕርይ ወደ ግዘፍ ሳይሳብ፤ የሥጋም ባሕርይ ወደ ነፍስ ባሕርይ ወደ ርቀት ሳይሳብ፤ ነፍስና ሥጋ ተውሕደው አካል ህላዌ ይገኛል። እስመ ክዋኔሁ ለሰብእ ውእቱ ግብር እለ ይትማሰሉ በበይናቲሆሙ ወኢየኀብሩ ወቃልኒ የተኀር ምስለ ሥጋ በከመ ኢተኀብር ፍስ ምስለ ሥጋ እንዘ ብእሲሁ አሐዱ እምነፍስ ወሥጋ ወአሐዱ ገጽ እምዘኢየኀብሩ ግብራት። ነፍስና ሥጋ ተውሕደው አንድ ኹነው የቆሙበት አካል ህላዌ ይባላል ለቃልም በተለየ አካሉ የተለየ ህላዌ አለው አስቀድመን እንደ ተናገርነ

 [4] መኖሪያ መኗሪያ። ምስጢሩ አናዎር ለው ይገባል። ኀበ ህላዌሁ ተመይጠ ሳኑ ውቁይ፤ ህላዌሁ አግብኦ -(ስንክ -ጥር፭) ዳግመኛም ባሕርይ ያላካል አካል ያለባሕርይ ብቻ ብቻውን አይኖርምና አንዱ ላንዱ ቦታ መኾኑን ያሳያል

[5]-ሥራ ግብር ህላዌ  ፍዕ፤ የግፍ ሥራ ግዙፍ ግፍ -(ሔኖ፺፩ -) እንዲህ ከኾነ የህላዌንና የጠባይዕን ፍች በየስልቱ ማስተዋል ይገባል፤ ኹለቱ ኹሉ ናቸውና

ህልው -(ዋን ዋት ሉት) ያለ የኖረ የነበረ፤ የሚኖር ነባር ቀዋሚ እውነት። ፈጠረ ፍጥረተ ይኩን ህልወ መድኀኒነ ዘህልው እምቅድመ ዓለም ብዕል ህልው። ርአይ ለእ ነገሩ ህልው። ህልወ ቃለ ማን ህልወ እብለክሙ -(ጥበ፪ -፲፯ ዲድ -፴፮። ዮሴፍ ምሳ፳፪ -፳፩ ዮሐ፲፮ -)

ህርብድና መቀማጠል ቅምጥልነት የቅንጦት ሥራ። ወለእመ ኮንከ ዘመነንካሁ ለህርብድና ጉዳይ እምእለ ይንዕውዎ -(ማር -ይሥ፪ -፲፪)

ህቦ -ወጨፎ እንዳሸዋና እንደ ጠጠር ያለ የዝናብ ቅንጣት፤ ጠል ጤዛ ጠፈጠፍ ከዝናም በኋላ በሣር በቅጠል ላይ የሚታቈር የሚንቈረዘዝ ሕንባበ ማዶ -(ግጥም) የተንቈረዘዘው ደምኸ እንደ ጤዛ የስብስቴ ግንቡል ጊዮርጊስ ሬዛ ንዘ ይትኀደግ ህቦ እምነቅዐ ቅዳሴከ ርወይ ወእሰቀይ ህቦ -(ዘፀ፲፮ -፲፫ ደራሲ)

ህኩክ -(ካን ካት ክክት) ህዉክ ወጪ ወራጅ ወላዋይ ኅሲና ህክክት -(ፊልክ -፶፬)

ህዉክ (ካን ውክት) የታወከ ሁከታም ከተኛ ርጋታ ጸጥታ የሌለው ዘክልኤ ልቡ ህዉክ ውአቱ በኵሉ ፍኖቱ። ህዉካን ወጽሩዓን እለ አልቦሙ ምግባረ ሠናይ (ያዕ፩ ፰። ቀሌ)

ህየ [1]-የቦታ ጸፋ፤ በዚያ ከዚያ ወደዚያ ሩቅን ያሳያል እንደ ከሃ ነው ተከለ ገነተ ወሤሞ ህየ ህየ ይሠየማ ወህየ ይትዐቀባ ነፍሳቲሆሙ ጻድቃን ዘይወፅእ እምሥራቅ ወየሐውር ምዕራብ ከመ ይስቂ በህየ። ተንሥእ ወፃእ ሐቅለ ወበህየ እንግረከ -(ዘፍ፪ -፰። ቅዳ ግሩ አት ሕዝ፫ -፲፱)

[2]:-በዚያ ከዚያሀይይ ሀየ ሀየየ

()           ህየት -ቸል ማለት ልታ ንፍና። እምህየት ወእምፅርዐት -(ሊጦን)

ህየንተ -ስለ ፈንታሀየየ ሀየ

የንተ (ህየ እንተ) ዐቢይና ደቂቅ አገባብ ህየና እንተ ተጋጥሞ አንድ ኅርመት ኹኗል ስለ ተጐረደ መጋጠሚያው አያስታውቅም ይህን የመሰለ ብዙ አለ ፈንታ እንደ ይኾናል ስለና ፈንታ አንድ ወገን ናቸው ምስጢሩ እንደ ፍዳ ነው ለውጥ ሤጥ ቤዛ ካሳ ዕዳ ብድር ያሳያል። በአንቀጽ ሲገባ ዘን በር ከፋች ያደርጋል አንዳንድ ጊዜም ብቻውን ይገባል ምንተ ተዐስዮሙ ህየንተ ዘገብሩ ህየንተ ዘትረድኦ ቅበጽካሁ። ህየንተ ተቀንዩ ህየንተ ጻመወ (ሢራ፯ ፳፰ ቀሌ ኵፋ   ፵፰ ስንክ ጥቅ፬) በዘርና በስም ሲገባ ደዩኒ እኪተ ህየንተ ሠናይት። ህየንተ አበውኪ ወልዱ ለኪ ደቂቅ ተቀንየ ያዕቆብ ህየንተ ራሔል ይላል። እንደ ኾን ህየንተ ቈፅለ ዕፅ ማሁ ሕመልምል ሊተ ፍስየ ህየንተ ዕፅ ትክልት ማእከለ ገነት ይላል (አርጋ) ህየንቴሁ ብሎ ሲዘረዝር ርሱ ፈንታ በርሱ ፈንታ እንደ ርሱ ያሰኛል። ሀቦሙ ህየንቴየ ወህየንቴከ (ማቴ፲፯ ፳፯) (ዕር፲፱ ቍ፷፱)

ህዩይ -(ያን ያት ይይት) ቸል የተባለ የተናቀ ቸል ያለ ቸልተኛ፤ ነፍ መንዘህልልሰ ወህዩይ ፍናዊሆሙ ለህዩያን -(ፊልክ ፶፬ ምሳ፲፫ -፲፭)

ህዩድ -(ዳን ዳት ይድ) የተቀማ የተነጠቀ፤ ገንዘብ ሰው

ህዱኣዊ -ዝምተኛ ጸጥተኛ፤ ጭምት ልብ ህዱአዊ -(ፊልክ -፻፩)

ህዱእ -(ኣን ኣት ድእት) ዝም ጸጥ ያለ ያረፈ የረጋ ከት የሌለው፤ በከመ መንግሥትየ ህዱእ ህዱኣን ወዕሩፋን ይኩን  ህዱአ ዕይንት ዘኢኮነ ህዱአ በቃሉ ወበምግባሩ። ከመ በህዱእ ወበጽምው ይኩን ንብረትነ -(አስቴ -፫። መሳ፲፰ -፯። - -፳፮ -፰። ቀሌ ድጓ)

ህዳር -በቁሙ፤ኅዳር።

ህድመት -ህድመት ማንቀላፋት ክቡድ እንቅልፍ እንደ ሞት ያለ። ወደየ እግዚ ህድመተ ላዕሌሁ ወኖመ ሞት ውእቱ ህድመት ወንዋም ከመ ሞት በህድመት ክቡድ ኢወሀቡ ለአዕይንቲሆሙ ምንተጊ ህድመተ -(ኩፋ -፫። አፈ -ተ፬ አርጋ። ስንክ -ኅዳ፲፯)

ህድአት ዝም ጸጥ ማለት ዝምታ ጸጥታ ረፍት ርጋታ ዳታ ቀስታ ዝግታ ጭምትነት ህድአት ወአርምሞ። መፍቀሬ ህድአት መፍትው ለነ ንሑር በህድአት። መፍትው ለአንስት ይትርአያ በአርኣያ ህድአት። ፈታሒ ዘአጥረየ ህድአት ወትዕግሥት (ጥበ፲፰ ፲፬ ዮሴፍ አፈ ተ፴፬።  ፴፬። ፵፪ )

ህጉል -(ላን ላት ጕልት) የታጐለ የተጓጐለ፤ መና የቀረ። የጠፋ ጥፋ ብልሹ፤ ከንቱ ከቦታው የታጣ፤ የኰበለለ ሕዝብ ህጕላነ ምክር ከመ ኢይኩን ህጉለ ዕሴትከ ዘይትአመን በብዕሉ ህጉል መድኀኒሆሙ ለህጉላን ህጉላነ ሚጥ -(ዘዳ፴፪ -፳፰ ራ፰ -፲፱ ኖዶ ዮዲ፱ -፲፩ ኪዳ)

ህጕለት -መታጐል፤ መቅረት። መጥፋት አጠፋፍ ጥፋት -(ሔኖ፰ -፬። ፳፪ -፲፪) ህጕለተ ነፍስ -(ሲኖዶ)

ህጕሬ -ቀይ ቀለም፤ሕጕሬ

ህግሩት -የተጋ ትጉ ዐሳ ተቈርቋሪ -(አርጋ)

ህግርትና -ትጋት ሐሳብ፤ ጉህነእት ዐሳቢነት -(መጽ -ምስ)

ሆሄ [1]-(ሆይ ) ስመ ፊደል መልከአ ደል ሆይ የግእዝ የዕብራይስጥ ነው

[2]-ሆሄ -(ዐረ ሁወ ) ውእቱ ማለት ነው የኦሪትን ክፍልና ብሔር ከዘፍ እስከ ዘዳ በፊደል ጥር ሲቈጥር ወለመጻሕፍተ ሪትኒ -(ትእምርታቲሆሙ) በክልኤቱ ፊደላት እሙንቱ ወፊደለ ትእምርተ ኦሪት ቀዳማዊ ትአ ወዳግማዊ ትቤ፤ ወሣልስ ትጋ፤ ወራብዕ ትዳ፤ ወኃምስ ትሄ ካለ ኋላ ውእቱ እንደ ማለት ወሆሄ ልቈ መጻሕፍት ይላል -( - -መቅ) ይህም -ፊደል ነውና ብቻውን ያ፭ቱ መጻሕፍት ጥር ነው ያሰኛል። አይሁድም ቱን መጻሕፍት በዝርዝር ሖማሽ በአኃዝ ይሏቸዋል ማለት ነው

ሆህያት -ፊደሎች፤ የፊደል ስሞችና መልኮች ከሀ እስከ ወይም እስከ ያሉት ላው ባንድነት። ፊደላተ ዔቦር በኵራቸውና መክብባቸው አሌፍ ስለ ኾነ በመክብባቸው ስም አሌፋት ተብለው እንዲጠሩ፤ ፊደላተ ግእዝም ከሰላማ ወዲህ መክብባቸው ሆሄ -(ሆይ ) ስለ ኾነ በሆሄ ሆህያት ይባላሉ ቃሉ የብዙ ሲኾን ላንድም ለብዙም ይነገራል ንድ ሲነገር ሰባትነቱን ለብዙ ሲነገር መላዉን ያሳያል። ሆህያተ ፊደል እስመ ሆህያተ ቤት ወዋዌ አሐዱ ውእቱ። በከመ ሆህያተ ልፋ ትከውን ኀበ ሎሙ ሆህያት ወለለ ማኅደር ስምዮሙ በሆህያተ ጽርእ እምልፋ ወቤጣ ወጋማ -(አፈ -ድ፰ -፱። ሥር -ጳኵ) ወይቤ ጠቢብ ቀሪጦን፤ እስመ ሴት ቀዲሙ ዘከሠተ ሆህያተ ጽሕፈት ወአዖቀ ልሳነ ዕብራዊ -( - - -ገ፮)

ሆሙ -() የሩቅ ወንደች ዝርዝር ቃሽ የሁን አፈታት እይ

ሆሜር -መስፈሪያሖሜር።

ሆሳዕና -(ዕብ ሆሺዓህናእ) አንቀጽና ጥሬ ድኅነነአ አድነና፤ አድነንኮ እባክኸ ድነን፤ የአን ፍች ተመልከት -(ማር፲፩ - ዮሐ፲፪ -፲፫)

 -መድኀኒትነት፤ መድኀኒት መኾን፤ ወይም መባል። ሆሳዕና ወልደ ዳዊት። እምሆሳዕናሁ ርአየ ተኣምረ ወመንክረ -(ማቴ፳፩ -፬። ቅዳ -ጎር)

 -የበዓል ስም፤ የሰሌን በዓል ሌን ይዘው እያመሰግኑ የሚያውዱበት ብሉዩ የመጸለት ፯ኛ ቀን ለሐዲሱ ግን ከትንሣኤ በፊት ያለ እሑድ -(የዶሮች ዘፈን) በሆሳዕና ተሰበሰብና፤ በሳምንቱ አለብነ ሞቱ ዋዜማ ዘሆሳዕና በሳኒታ ሆሳዕና ሰኑይ ዕለት -(ድጓ ዲድ -፳፱)

 -ሌን የሰሌን ቅጠል ጽለ ዘይት ባርሰነት የመሰለው ኹሉ፤ የሆሳዕና ለት የሚያዝ ዘይቶን ወሆሳዕና ብሱ እምልሕጸ ሆሳዕና ወቈጽሉ ሌን -(ስንክ -መስ፫)

ሆሴዕ -(ዕብ ሆሼዕ) የሰው ም፤ ነቢይ ጉሥ። አድኀነ ባልሐ፤ ረድአ አውፅአ እመሥገርት ማለት ነው -(ሆሴ፩ -፩። ነገ -፲፭ -)

ሆባይ -(ያት አህቡይ) አንጨት አሞራ ሳቢሳ ጭላት፤ ጥንብ ፈላጊ -(ዘሌ፩ -፲፬ ዘዳ፲፬ -፲፫። ኢዮ፴፱ -፳፮ ሔኖ፹፱ - - - -፲፩ -፲፫) ስምንቱ አስተጋባኢ ነው ለሚከንፍና ለሚረብ ለሚያንዣብብ ኹሉ ይኾናል

 -(ዕብ ቆፍ ሱር ቁፋ ዐረ ቂርድ) ዝንጀሮ ጨላዳ በብዙ ወገን ሰው የሚመስል ነጨና ጥቍሬ ዐይነት ያለው በአምሳለ ሆባይ ሆባያት አጽዐቅዎሙ ወይጠለ ስገድከ ወሆባየ አክነስከ ብፁዕ አንተ ዮሐኒ ወአህቡየ -(ገድ -ተክ ዋሥ ፪ዜና - -፳፩)

 -(ዐማርኛ) ቁሙ ባይ አሆ የሚል ጨፋሪ እንደ ዝንጀሮ የሚያወካ።

ሆን -( ሆሙ) የሩቅ ቶች ዝርዝር ጠቃሽ

ሆይ -(ዐማራ ወዕብራ) ቁሙ የጥሪ ቃል በቅርብ ላለ አቤቱ ንጉሥ ሆይ። ፍችው በጭራሽ እንደ ነውና፤ ኦንና ኦኦን ተመልከት

ሆይ ሀውይ -(ዕብ ሆዌ ውስጠ ) ስመ ፊደል ኃምስ ሀ። ሀላዊ ህልው ዘሀሎ ወይም ከዋኒ ክዉን ዘኮነ ማለት ነው ሀለወና ኮነ በዕብራይስጥ አን ወገን ናቸው ሀያህ ይህዬህ ብሎ ሀለወ ይሄሉ ኮነ ይከውን ያሰኛልና ሆይ ውይ አህያ ይሆዋ ከዚህ የወጣ ነው

ሆድ -(ዕብ ጸዳል ውበት፤ ክብር ምስጋና) ቁሙ፤ ከርሥ -(ዐማርኛ)

No comments:

Post a Comment

ማውጫ

ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ